Get Mystery Box with random crypto!

ፍቅርና ተስፋ

የቴሌግራም ቻናል አርማ tloveandhope — ፍቅርና ተስፋ
የቴሌግራም ቻናል አርማ tloveandhope — ፍቅርና ተስፋ
የሰርጥ አድራሻ: @tloveandhope
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 247
የሰርጥ መግለጫ

ተስፋ ማለት በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ብርሃን አለ ብሎ ማመን ነው።
ተስፋ ማለት ወደ ባህር እየተወረወሩ በሆነ ተአምር እንደ ሚድኑ ማመን ነው
ፍቅር ማለት ፍፃሜው የሚያምር ቅርብ ማንነትንና ግልፅነትን የሚያስተምር...ርህራሄና ለሰው ማዘንን በልብ የሚያኖር ከፈጣሪ የሚገኝ ፀጋ ነው።
ፍቅር ያለ እምነት ነፋስ ላይ እንደ ተቀመጠ ሻማ ነው።

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-09 07:24:51 #ሰላም_ለኢትዮጵያ



አ ፈ ቅ ር ሻ ለ ሁ





አ = አንድ ነገር ቀረኝ ከጥፋት መታቀብ
ፈ = ፈልጌው አደለም አላበዛም ሰበብ
ቅ = ቅንነትሽ ደስታ ስሜትን ይስባል
ር = ርሀብን ያስታግሳል ጥምንም ያስቆማል
ሻ = ሻማ ሁነሽኛል በጨለመው ጎኔ
ለ = ለማንም አልፈቅድም እንዲለዩሽ ከ #እኔ
ሁ = ሁሌም ወድሻለሁ ትናፍቂኛለሽ እስከማይሽ በ #አይኔ
.......... .............
Join us||➠ @tloveandhope
40 viewsChristyan, 04:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 07:20:49 የዘር ግንድ አቆጣጠር ከልጅ እስከ ደረባቴ ድረስ


ልጅ፣ አባት፣ አያት፣ ቅድመ አያት፣ ቅም አያት፣ ቅማንት፣ ሽማት፣ ምንዥላት፣ እንጁላት፣ ፍናጅ፣ ቅናጅ፣ አስልጥ፣ አመለጥ፣ ማንትቤ፣ ደረባቴ በመባል ይታወቃሉ።

@tloveandhope
37 viewsChristyan, 04:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 07:10:49 ​​ መልካሙ ዶክተር

ክፍል ሁለት


ምግቡን ጨርሼ እማማ አመሰግናለሁ ብዬ ልሄድ ስል.. ልጄ የበሉበትን እቃ ማጠብ የጨዋ ሰው ተግባር ነው እቃውን ብታጥቢ ደስ ይለኛል አሉ እማማ ኧረ ችግር የለም እርስዎ ምግብ ሰጥተውኝ እኔ እቃ ማጠብ እንዴት ያቅተኛል እንደውም ቤት ውስጥ ያሉትን በሙሉ አምጡ አልኳቸው ተባረኪ ልጄ ብለው ትንሽ እቃ አምጥተው ሰጡኝ እኔም እቃውን ማጠብ ጀመርኩኝ...
እቃውን ጨርሼ ልሄድ ስል ልጄ አሁን ፀሐዩ በጣም ከባድ ነው ፀሐይ ትንሽ በረድ እስኪል ቁጭ ብለሽ ቴሌቭዥን መመልከት ትችያለሽ አሉኝ የዚህች መልካም እናት ሁኔታ ትንሽ ቢገርመኝም ቁጭ ብዬ ቴሌቭዥን ማየት ጀመርኩኝ በዚህ መሃል ከተቀመጡበት ተነስተው ቡና ማፍላት ጀመሩ...
ይህ ሁሉ ክብር ለኔ? ምን የሚሉት ነገር ነው? ቡናው ተፈልቶ ደረሰ በዚህ ሁሉ ሰዓታት ተጫወቺ ከማለት ውጭ ምንም ጥያቄ እየጠየቁኝ አይደለም እኔ ደግሞ ጥያቄ የማይጠይቅ ሰው ስወድ! በቃ ቤተሰብ ቤት ምናምን ስለሌለኝ ስለ ኑሮ ስለ ቤተሰብ ታሪክ ምናምን የሚጠይቁኝ ሰዎች ያስጠሉኛል፣ ነገር ግን እሳቸውን ለመጠየቅ ምክንያት የሆነኝ ነገር ቡናው ነበረ... እማማ ለምን ቤተሰብ እስኪመጣ ትንሽ አንጠብቅም አልኳቸው ትንሽ ከሳቁ በኋላ ቤተሰብ ነው ያልሽው? ብለው ጠየቁኝ እኔም አዎ ቤተሰብ ባይኖረኝም ቡና ከቤተሰብ ጋር ሲሆን ደስ ይላል ብዬ ነው አልኳቸው አይይይይ ልጄ የሉም አሉኝ አይመጡም ለማለት መስሎኝ ዝም አልኩኝ አብረን ቡናውን ጠጥተን በድጋሚ ለመሄድ ተነሳሁ ትልቅ ቀጠሮ ያለኝ ሰው አልመስልም? ልጄ ገበያ ለመሄድ አስቤ ነበረ ግን አቅም አጣሁ ብለው ዝም አሉ ታዲያ የሚልኩት ሰው የለም? በዚህ ጊዜ ሰው ከየት ይመጣል ብለሽ ነው የምትሄጅበት ከሌለ ለምን አንቺ ሮጥ ብለሽ አትመጪም አሉኝ ማን? እኔ ገበያ? እኔ እቃውን እንዴት ገዝቼ እንደሚመጣ እንኩዋን አላውቅም አልኳቸው በልቤ ደግሞ ለኔ ብር ሰጥቶ መላክ ውሻ ላይ አጥንት እንደመላክ ነው እስከአሁን ዝም ያልኩት ራሱ ምስኪን ስለሆንሽ ነው እንጂ ሌላ ሰው ቤት ገብቼ ቢሆን ኖሮ መቼ ምን ይዤ እንደወጣሁ ማወቅ አትችይም እያልኩ ሴትዮዋን በአግርሞት ማየቱን ቀጠልኩኝ... ቀላል እኮ ነው ልጄ ሮጥ ብለሽ ደርሰሽ ነይ ብለው 300ብር ሰጡኝ እኔም ብሩን ይዤ ከቤት ወጣሁኝ.... ልክ ከቤት እንደወጣሁ አእምሮዬ ላይ ብዙ ሃሳቦች መምጣት ጀምሩ፣ አንዴ ብሩን ይዤ ዛሬ ዘና ማለት አለብኝ የሚል ሃሳብ ነው ሌላኛው ልቤ ደግሞ ከዚህች ምስኪን እናት ብር ይዞ መጥፋት ከክህደት ሁሉ ትልቁ ክህደት ነው እያለ መውቀስ ጀመረ ቆይ እሺ በዚህ 300ብር እቃ ገዝቼ ስሄድ ትንሽ ብር ብቻ ብሰጠኝስ ብዬም ሐሳብ ውስጥ ገባሁ ልቤ ግን አሁንም ምንም ባይሰጡሽ እንኩዋን እቃውን ገዝተሽ መሄድ አለብሽ ብሎ ትእዛዝ ሰጠኝ እኔም የልቤን ትእዛዝ ተቀብዬ እቃውን ገዝቼ ወደ ቤታቸው ተመለስኩኝ ተመልሼ በመምጣቴ ደስታ ብቻ ሳይሆን ግራ የተጋቡ የሚመስሉት እናት እንዴት መጣሽ? እእእእ ማለቴ ቶሎ መጣሽ ቤት ገብተሽ ቁጭ በይ አሉኝ አይይይ አሁን እሄዳለሁ አልኳቸው ለምን? የት? ብለው ተጣድፈው ከተናገሩ በኋላ ግን አንድ ሁለት ቀን እዚህ ብትቀመጪ ደስ ይለኛል ብለው በትህትና ተናገሩ ኧረ ማዙካ አግኝቼ ነው ሲጀመር እኔ ምን መሄጃ አለኝ በደስታ ነው ቁጭ የምለው ብዬ ቁጭ አልኩኝ ለምሳ ብዬ የገባሁት ቤት የአራት ወር መኖርያ ቤት ሆኖ አገኘሁት። ከአራት ወር በኃላ ሱቅ ተልኬ ስሄድ በአጋጣሚ የሆነ ልጅ መጥቶ ሀይ ሀረግ ብሎ ሰላም አለኝ ሀረግ? እዚህ ሰፈር የኔን ስም ማንም አያውቅም እሱ እንዴት አወቀ እያልኩ ትንሽ በዝምታ ተዋጥኩኝ ምነው ሀረግ አላስታወሽኝም እንዴ? እዩኤል እኮ ነኝ ከጥቂት ወራት በፊት ከመንገድ ላይ አንስተሽ ሃኪም ቤት የወሰድሺኝ ልጅ ብሎ በድጋሚ ሰላም አለኝ ይቅርታ ወንድም ልቤ ሌላ ቦታ ስለነበረ ነው ታዲያ አሁን እንዴት ነህ አልኩት እግዚአብሔር ይመስገን አሁን ደህና ነኝ፣ ሻይ ቡና ማለት እንችላለን ብሎ ጠየቀኝ አሁን አልችልም ተልኬ ነው የመጣውት አልኩት እና እዚህ ሰፈር ነሽ ማለት ነዋ አለኝ አዎ እዚህ ሰፈር ነኝ አልኩት እኔም እኮ እዚሁ ሰፈር ነኝ አለኝ በቃ ቻው ብዬ ወደ ቤት መጣሁኝ ገበያ ተልኬ ታማኝ በመሆኔ አራት ወር በሙሉ ቁርስ ምሳ እራት ጠግቤ መብላት ጀመርኩኝ ጥሩ አልጋ ላይ ተኝቼ ማደር ጀመርኩኝ ጥሩ ልብስ መልበስ ጀመርኩኝ እነዚህ አሁን ያልኩት ነገሮች ታማኝ በመሆኔ ካገኘውት ነገሮች ጥቂቶቹ ናቸው። ከቀኑ ስድስት ሰአት አካባቢ የግቢው በር ተንኳኳ... እኔ እዚህ ቤት ከገባሁበት ቀን እስከዛሬ እዚህ ቤት ሰው መጥቶ አያውቅም ምስኪኗ እናት ደግሞ ቤት ውስጥ ናት ማነው ብዬ በር ለመክፈት ሄድኩኝ በሩን ስከፍት.

ማነው ብዬ ሄጄ በሩን ስከፍት.. እዩኤል? እንዴት መጣህ አልኩት እእእእእእ ታምራት የለም አለኝ ታምራት ታምራት? ማነው ደግሞ ታምራት አልኩት ኦኦኦኦኦ ለካ ቤት ተሳስቼ ነው የመጣሁት ብሎ በተረፈ እንዴት ነሽ አለኝ ደህና ነኝ አልኩት እንዲህ እንዲህ እያለን ከእዩኤል ጋር ጥሩ ጓደኛሞች ሆንን.. ቤት ተሳስቼ ነው የመጣውት ያለኝ ቀን ለካ ውሸቱን ነው ሱቅ የተገናኘን ቀን ተከትሎኝ መጥቶ ነው ቤቱን አይቶ ተመልሶ የሄደው እዩኤል በጣም የዋሀ መልካም ልጅ ነው በጓደኝነት ብዙ መቆየት አልቻልንም ጓደኝታችን ቶሎ ወደ ፍቅር ተቀየረ... የእዩኤል እናት በህመም መሰቃየት ከጀመሩ ብዙ አመታትን አስቆጥረዋሉ የእናቱን ሙሉ ኃላፊነት ከልጅነቱ ጀምሮ በእጁ ላይ ይዞ ያደገ ምስኪን ልጅ ነው ህይወቱ ከእኔ ህይወት ጋር ብዙ ተመሳሳይ ነገሮች ያሉት እዩኤል ከራሱ እድገት አንጻር ለኔ ያለው ክብር እጅግ በጣም ደስ ይለኛል አንድአንድ ጊዜ የልቤን ሃሳብ ሁሉ የሚያውቅ ይመስለኛል እኔም ህይወቴን ከመንገድ ላይ አንስተው ዛሬ እንደዚህ በደስታ እንድኖር ካደረጉኝ እናቴ ጋር አብሬ በደስታ እየኖርኩኝ ነው ለዚህች ምስኪን እናት ልጅ ይሁን ዘመድ የሚባል ነገር የላቸውም አሁን ግን እሳቸውም ልጅ እኔም እናት አግኝተን በደስታ እየኖርን ነው። እዩኤል አልፎ አልፎ ልክ እንደ እናቱ ሁሉ በህመም እየተሰቃየ ነው ጥሩ ሃኪም ቤት ሄደው ጥሩ ህክምና የማግኘት እድል ግን አልነበረውም፣ አንድ ቀን ቤት ውስጥ ቁጭ ብዬ ቴሌቭዥን በማየት ላይ እያለሁ ስልክ ተደወለልኝ የእዩኤል ስልክ ነው እኔም በደስታ ሀይ ፍቅር አልኩት እዩኤል አይደለም እናቱ ነኝ ቶሎ ብለሽ ድረሽ ታውቂያለሽ እኔ እንደሆንኩ አቅም የለኝም አሉኝ እማማ እዩኤል ምን ሆነ ስላቸው አሁን ጥያቄው ምንም አያደርግም ቶሎ ብለሽ ቤት ነይ አሉኝ እኔም በፍጥነት ቤታቸው ሄድኩኝ፣ እዩኤል እራሱን ስቶ ወድቆ ነበረ.... ቶሎ ብዬ ታክሲ ጠርቼ ወደ ሃኪም ቤት ወሰድኩት ከብዙ የፀጥታ ሰአታት በኋላ እዩኤል በድጋሚ ማውራት ጀመረ... እዚህ አለም ላይ አለኝ የምለው እዩኤል እንደዚህ ሆኖ ከማየት በላይ ተስፋ የሚያስቆርጥ ነገር ምን አለ? ሀረግ አሁን እኮ ደህና ነኝ ይላል የሆዱን በሆዱ ይዞት ሁሉም ሰው የፍቅረኛውን ደስታ ይፈልጋል አይደል እሱም ለኔ ደስታ ብሎ ህመሙን ቀላል ለማድረግ እየሞከረ ነው ህመሙ በጣም ከባድ እንደሆነ ግን ሃኪሙ ነግሮኛል ዛሬ መልካሙን ዶክተር የተገናኘውበት ቀን ናት ለህክምናው የጠየቀኝ ብር በጣም ብዙ ብር ነው በኪሴ ውስጥ የነበረኝ ብር ደግሞ በጣም ጥቂት ብር ነው ይቅርታ አድርግልኝ ለጊዜው ሙሉ ብር የለኝም ልጁ እዚሁ ይቀመጥ እኔ ብሩን ይዤ እመጣለሁ አልኩት አይይይይ ችግር የለም ባይሆን ልጁ ክትትል ይፈልጋል ክትትል

ይቀጥላል ...
43 viewsChristyan, 04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 23:12:18
#የደም_አይነታችሁን_ታውቁ_ይሆን?

በዓለማችን ላይ ያለውን ህዝብ በደም አይነት ብንመድበው አብዛኛው ሰው ያለው የደም አይነት እንዲህ ሆኖ ቀርቧል።
የደም አይነት የህዝብ ብዛት በ%
O+ 37%
O- 6%
A+ 34%
A- 6%
B+ 10%
B- 2%
AB+ 4%
AB- 1%


Share join
48 viewsChristyan, 20:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 22:33:02 ​​ መልካሙ ዶክተር

ክፍል አንድ ➊



ስሜ ሀረግ ነው፣ ሀረግ የሚለውን ስም ማን እንዳወጣልኝ እንኳን አላውቅም ሀረግ የሚለው ስም ለኔ ብዙ ትርጉም ይሰጠኛል አንድ አንድ ጊዜ የሆነ ሰው ጥሎኝ ልሄድ ተክሎኝ የሄደ ዛፍ እንደሆንኩ ይሰማኛል ፍሬ የሌላ ዛፍ! የብቸኝነት ህይወት እንደዚህ ከባድ ነው ብሎ ለሌላ ሰው ለማስረዳት እንደዚህ ነው ብሎ ምሳሌ የሚሰጡት ነገር እንኳን ሊኖር አይችልም። ሁሉ ሰው ወደዚህች አለም ሲመጣ ተመሳሳይ ነገር ነው ይዞ የሚመጣው ከዚህ አለም ሲሄድም ተመሳሳይ ነገር ነው ይዞ የሚሄደው ነገር ግን በዚህች አለም ላይ ሁሉም ሰው የተለየያ ህይወት ይኖራል አንዱ የአንዱን ህይወት መኖር በፍጹም አይችልም ምክንያቱም የዚህች አለም ኑሮ መሪዋ እድል በምንለው ነገር የተያዘች ናትና፣ እሱ ወደፈለገበት እንጂ እኛ መሄድ የምንፈልግበትን ቦታ መሄድ አንችልም። ማንም ሰው ከእናቱ/ከአባቱ ተለይቶ መኖር አይፈልግም ግን ብቸኛ ሆኖ ይኖራል፣ ማንም ሰው አካለ ስንኩል ሆኖ መኖር አይፈልግም ግን በግድ ሆኖ ይኖራል፣ ማንም ሰው ድሃ ሆኖ መኖር አይፈልግም ግን ድሃ ሆኖ ይኖራል፣ ማንም ሰው በህመም እየተሰቃየ መኖርን አይፈልግም ግን ብዙ ሰዎች በህመም እየተሰቃዩ ይኖራሉ ፣ ለዚህም ነው ህይወት የምርጫ ጉዳይ ሳትሆን እድል ላይ የተሰራች ቤት ነው ያልኩት በዚህ አለም ላይ አብዛኛው ነገር ለሰዎች በተናጥል ተሰጥቷል ለሁሉም ሰው እኩል የተሰጠ ነገር ቢኖር " ፍቅር " ብቻ ነው! በዚህ ምድር ላይ ለሁሉም እኩል የተሰጠ ስጦታ ፍቅር ብቻ ነው ህጻን ይሁን ሽማግሌ፥ ሴት ይሁን ወንድ፥ ቆንጆ ይሁን አስጠሊታ ፥ሁሉም ሰው የፍቅር ስጦታውን ተቀብሏል፣ ምንም እንኳን ስጦታውን በአግበቡ የሚጠቀሙ ሰዎች በጣም ጥቂቶች ቢሆኑም ቅድም እንዳልኩት ሁሉም ሰው የፍቅር ስጦታን ከፈጣሪ ዘንድ ተቀብሏል።
የኔ የፍቅር ታሪክ የሚጀምረው በአንድ መጥፎ አጋጣሚ ቢሆንም አጋጣሚው ግን በድንገት ህይወቴን ቀይሮ አየሁት
ፈጣሪ ህይወትህን ለመቀየር ሲፈልግ ሰው ይልካል እንጂ እሱ አይመጣም ሰይጣንም ቢሆን ህይወትህን ለማበላሸት ሲፈልግ ሰው ይልካል እንጂ እሱ በተግባር አይመጣም ልዩነቱ ፈጣሪ መልካም ሰው ይልካል ሰይጣን ደግሞ ክፉ ሰው ይልካል እንደ አጋጣሚ ሆኖ ለኔ የተላከው ሰው መልካም ሰው ነበረ እዩኤል እኔ እንደዚህ ነው ብዬ ከምነግራችው በላይ መልካም ልጅ ነው ከምንም በላይ ለኔ ለብቸኛዋ ምስኪን ልጅ ወንድም እናት አባትም ጭምር ነው እዩኤልን የተዋወኩት ድሮ ድሮ የጎዳና ልጅ እያለሁ ነበረ አንድ ቀን መንገድ ላይ መሬት ላይ ወድቆ ሰው ሁሉ ዝም ብሎት እያለፈ አይቼ ኪሴ ውስጥ ለምሳ ሰርቄ በያዝኩት ብር ሃኪም ቤት ወሰድኩት ሃኪም ቤት ውስጥ የካርድ ብር አጥቼ ወዲህ ወዲያ ስል............

ሃኪም ቤት የካርድ ብር አጥቼ ወዲህ ወዲያ ስል አንዲት
መልካም እናት ልጄ ሰው ጠፍቶብሽ ነው ወይ ብለው ጠየቁኝ እኔም የሆነውን ነገር ሁሉ በትህትና ነገርኳቸው፣ እርሳቸውም አይዞሽ ልጄ አንቺ መልካም ልጅ ነሽ የካርዱን ብር እኔ እሰጣችኋለሁ ግን የህክምና ብር አለሽ ወይ ብለው ጠየቁኝ
ማዘር እኔጋ ምንም ብር የለም ምናልባትም ልጁ ቀድሞ
እራሱን ቢያውቅ ስልክ ቁጥር ተቀብለን ለቤተሰቦቹ መደወል
እንችል ነበረ አልኳቸው
መልካም ብለው እርሳቸውም ከእኔ ጋር አብረው የልጁን ሁኔታ
ለማየት ቁጭ አሉ
ዶክተሩ የመጀመሪያ እርዳታ ከሰጠ በኋላ ለጊዜው ብዙ
አሳሳቢ ችግር እንደሌለበት ነገር ግን እራሱን ከጭንቀት ነጻ
ማድረግ እንዳለበት ነግሮት አንድአንድ መድሃኒቶችን ሰጥቶ
ትንሽ ብር ሲጠይቅ እኔ ቶሎ ብዬ ቤተሰብ ጋር ልደውል ስልክ
ቁጥር ስጠኝ አልኩት
ከዝምታ ሌላ ምንም መልስ መስጠት አልቻለም
በዚህን ጊዜ ከልጁ ዝምታ የሆነ ነገር መረዳት የቻሉት እናት
ከቦርሳ ውስጥ አውጥተው ሃኪሙ የጠየቀውን ብር ሰጡ
በጣም ደስ አለኝ ግን ምን አይነት መልካም እናት ናቸው?
ከዛም ልጄ እኔ አሁን ወደ ቤት ልሄድ ነው እናንተም ወደ
ቤታችሁ ተመለሱ ይሄ የታክሲ ብር ነው ብለው ብዙ ብር ሊሰጡ
ሲሉ እማማ እኔ ምን ቤት አለኝ ብለው ነው ለኔ የሄድኩበት ሁሉ
ቤቴ ነው የትም ሰፈር ብሄድ መኖር እችላለሁ ብሩን ለሱ
ስጡት አልኳቸው ልጄ ምን እያልሽ ነው ቤት የለኝም ማለት ምን ማለት ነው?
ቤተሰብ አለሽ አይደል ብሎ ጠየቁኝ እማማ ለካ እርስዎም ቀልደኛ ኖት ቤተሰብ ቢኖረኝ ይሄን
እመስላለሁ ብዬ ጥዬ ልሄድ ሲል ታዲያ ወዴት ነሽ ብለው ጠየቁኝ
ወዴት ነኝ? እኔን ከየት ነሽ ብሎ እንጂ ወዴት ነሽ ብሎ ሰው
ጠይቆ አያውቅም ምክንያቱም እኔ እግሬ ወደ መራኝ መሄድ
እንጂ እዛ እሄዳለሁ ብዬ መንገድ አልጀምርም አልኳቸው
ታዲያ ለምን ዛሬ ከእኔ ጋር አትሄጅም አሉኝ ቡሌ ይስጡኝ እንጂ የትም እሄዳለሁ አልኳቸው
ቡሌ ደግሞ ምንድነው ሲሉኝ
እማማ ምሳ አልበላሁም አልኳቸው
ልጁን አንተስ አትሄድም አሉት
እማማ እርሶ በጣም መልካም እናት ኖት ስለ ሁሉም ነገር
በጣም አመሰግናለሁ እግዚአብሔር ያክብሮት እኔ አሁን ቤት መሄድ እፈልጋለሁ እናቴ ትጠብቀኛለች ብሎ ልሄድ ሲል
ታዲያ ምስጋናው እኮ ከእኔ በላይ አጠገብህ ለቆመች ልጅቷ
ነው መሆን ያለበት እሷ እኮ ናት ከመንገድ ላይ አንስታ ሃኪም
ቤት የወሰደችህ አሉት
እሱም ወደ እኔ መጥቶ በመጀመሪያ ይቅርታ አድርግልኝ
ሃኪም ቤት የወሰድሽኝ አንቺ እንደሆንሽ አላወኩም ነበረ
በመቀጠል ደግሞ በጣም አመሰግናለሁ ስሜ እዩኤል ነው
ብሎ እጄን ጨበጠ
እኔም ሀረግ አልኩትና ለትንሽ ሴኬንዶች ሁለታችንም ፍዝዝ
ብለን ቀረን
በዚህ መሃል በይ አሁን እንሂድ እሱም ወደቤት ይሂድ ብሎ
እኔን ወደቤታቸው ይዘውኝ ሄዱ
ቤታቸው ደረስን፣ ቤት ውስጥ ለጊዜው ሌላ ሰው አልነበረም
ልክ ቤት እንደገባን የእጅ ውሃ ሰጥተውኝ ተሰርቶ ከተቀመጠው ምግብ አምጥተው ሰጡኝ
እኔም ተገኘ ብዬ ልጀምር ስል ቆይ ልጄ ምግብ ከመብላትሽ በፊት የሰጠሽን አምላክ ማመስገን አለብሽ ብለው አመስግነው
ሰጡኝ ምግቡን ግማሽ ካደረኩ በኋላ የእሳቸው ነገር ትዝ አለኝ
እማማ እርስዎ አይበሉም አልኳቸው እሺ መጣሁ አሉና ሌላ ምግብ አምጥተው ጨምረው ከእኔጋ አብሮ መብላት ጀመሩ
ይህች ቀን በህይወቴ ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ ሰዎች ክብር
የሰጡኝ ቀን ነበራች
ምግቡን ጨርሼ እማማ አመሰግናለሁ ብዬ ልሄድ ስል......

ይቀጥላል!


​​​​​​​@tloveandhope
60 viewsChristyan, 19:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 18:49:33 ጠቃሚ የህይወት መርሆዎች!
*

❖ ደግ ሁን፡፡
የምትችል ከሆነ ከማንም የበለጠ ደግ ሁን፤ ቢሆንም ደግነትህን አትናገር፡፡ ስለተረፈህ ሳይሆን ሰብአዊነት ኖሮህ ላንተ ከሚያስፈልግህ ሳትሰስት ለሌሎች አካፍለህ ኑር፡፡ "መስጠት የማያውቁ ሰዎች ሌሎች ሲሰጡ ይታመማሉ!!"

❖ ቀና ብለህ ተጓዝ፡፡
ዘወትር ቀና ብለህ ተጓዝ ምክንያቱም ራሱን ያጎበጠ ሰው መቼም ሌሎችን አቅንቶ አያውቅምና፡፡ ችግሮችህን አስብ፡፡ የገጠሙህን ችግሮች ችላ አትበላቸው ምክንያቱም ችግርን በጥቅም ላይ እንደማዋል ጣፋጭ ነገር የለምና፡፡

❖ እውቀትን የምትሻ ሁን፡፡
ከሌሎች ሰዎች ለማወቅ የተዘጋጀህ ሁን ምክንያቱም የእብደት የመጀመሪያ ምልክት እራስን አዋቂ አድርጎ ማሰብ ነውና፡፡

❖ መልካም አሳቢ ሁን፡፡
ሁሉም ሰው ራሱን የሚያገኘው በየእለቱ በሚፈጥረው አስተሳሰብ መሠረት ነው፡፡ መጥፎ ቀን የምንለው መጥፎ ሃሳብ ያሰብንበት ቀን ነው፡፡ ስለሆነም ሁሌም መልካም ነገር እንዲገጥምህ መልካም የሆነውን ብቻ ተመልከት፡፡

❖ የቁሳዊ ድህነትን አትፈርበት፡፡
የቁሳዊ ድህነትን አትፈርበት ምክንያቱም ምድር ላይ እጅግ የሚያሳፍረው ነገር ቢኖር የአዕምሮ ድህነት ነውና፡፡

❖ ለገባኸው ቃል ታመን፡፡
ቃል ለመግባት የዘገየህ፤ ከገባህ ደግሞ የፈጠንክ ሁን፡፡ ራስህን አሻሽል፡፡ "የአንተን ውድቀት ለሚመኙ ስትል ራስህን አሻሽል" መጀመሪያ ራስህን እወቅ፡፡ ጠንካራ ጎኖችህን ይበልጥ አጠንክርህ በድክመትህ ላይ
ፈጥነህ ዝመትባቸው፡፡

❖ ህሊናህን አድምጥ፡፡
የተፃፈውን ሁሉ አንብበህ በህሊና መዝገብህ ከመፃፍህ በፊት በህሊናህ ሚዛንህ አብጠርጥር፡፡ ሁሌም ለሕሊናህ እንጂ ለሰው አትገዛ ምክንያቱም የሰው ልጅ ዛሬ ወዳጅ
መስሎ ቀርቦ ነገ ሊሸሽህ ይችላል ህሊናህ ግን በፀፀት እየወቀሰህ ዘወትር አብሮህ ይኖራልና፡፡

❖ አንደበተ ርቱህ ሁን፡፡
"ምላስህን ካልጠበካት እስዋ አትጠብቅህም" ጨዋ አንደበት የተዘጉ በሮችን ይከፍታል፡፡

❖ ብልህ ሁን፡፡
መከራን እና የተወረወረ ድንጋይን ዝቅ ብሎ ማለፍ ብልህነት ነው፡፡ ምክንያቱም ምድር ላይ ስትኖር ለመኖር መፈተን ለማለፍ መታገስ ግድ ነውና፡፡

❖ ሁልጊዜ ራስህን ሁን፡፡
ራሱን ያወቀ ሰው ሁልጊዜ በኑሮው ደስተኛ ነው፡፡ ሌላውን ለመምሰል ስትሞክር ማንነትህን ታጣና ህይወት ጣእሟን ታጣለች፡፡

❖ ሞራል ይኑርህ፡፡
የማይዋዥቅ የህይወት ሞራል ይኑርህ ምክንያቱም ጠንካራ ሞራል የህይወት ተስፋ ነውና፡፡

❖ ባለህ ነገር ተደሰት፡፡
ዛሬን ስለነገ በመጨነቅ ካሳለፍከው ዛሬን በቅጡ መኖር ይሳንሃል፡፡ ስላለህ ነገር እንጂ ስለሌለህ ነገር አታስብ ምክንያቱም ነገ የፈጣሪህ ነውና፡፡

❖ እውነታን ተቀበል፡፡
ተፈጥሮ የቸረችህን ማንነትህን አምነህ መቀበልን ትተህ ለማማረር ወይም ለመሸማቀቅ አትሞክር ምክንያቱም በተሰጠህ ተፈጥሮሯዊ ማንነትህ ላይ ያንተ ሚና የለበትምና፡፡ በማይለወጥ አንተነትህ ተደሰት ምክንያቱም
ቁርጡን ያወቀ ሰው ምርጫ ይኖረዋልና፡፡
ትክክለኛና ፍጹም ቀናውን መንገድ አግኝተን እንኖር ዘንድ ፈጣሪ ይርዳን!

መልካም ቀን!



@tloveandhope
58 viewsChristyan, 15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 18:49:33 ተቀማጭን ምድር
የቆመን ለሰማይ
ያደረገው ማነው
ይብዛም ይነስ እንጂ
ሁሉም የአዳም ዘር ነው
ሴትም ትሁን ሄዋን
ወንዱም የአዳም መንጋ
በቀለም በመልኩ
አልያም በስጋ
ተለያይቶ ገፁ
ድንበሩን ቢያናጋ
ሁሉም የሰው ዘር ነው
የፈጣሪ ፀጋ



@tloveandhope
40 viewsChristyan, 15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 18:49:33 ...

.....ራስህን ለሚመጡት አሳልፈህ አትስጥ ለሚሄዱትም አብዝተህ አትጨነቅ ነገር ግን በሁለቱ መሃል ሚዛናዊ ሁኖ መኖርን ልመድ




@loveandhope
40 viewsChristyan, 15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 18:49:33 #የት_አባቱ



ስትቀርበው ከራቀ፤
ስትሰጠው ከሰረቀ፤
ስትይዘው ከለቀቀ፤
ስትክበው ካፈረሰ፤
ስታፀድቀው ካረከሰ፤
ስታለብሰው ካራቆተ፤
ስታርመው ካሳሳተ፤
.
.
.
አትለምነው እንዲ አይነቱን፤
ይብቃ እሰረው ቀረጢቱን።
ገመድክን የዝምድና፤
አትቋጥረው በልመና።
ያቀረብከው ካልሆነልክ የሰው ብርቱ፤
ፍታው ተወው ጥንቅር ይበል የት አባቱ።


@tloveandhope
38 viewsChristyan, 15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 21:47:19 ለምንድነው_መኖር_የደከመህ??
.
ለምን መኖር ደከመህ? ለምን ህይወት ድግግሞሽ ሆነብህ? ለምን ራስህን ለማጥፋት ወሰንክ? በስደት ስላለህ? በህመም ስለሆንክ? ያሰብከው ስላልተሳካ? ያመንከው ስለከዳህ? አበቦች ሲፈኩ እንደሚደርቁ ያውቃሉ፡፡ ግን እደርቃለሁ ብለው ሳይፈኩ አይቀሩም፡፡ ሰውም ሟች ነው ግን ሟች ነኝ ብሎ መተው የለበትም፡፡ ሁሉም ሰው በየመስኩ ያብብ፡፡ አንተ አላስፈልግም ትላለህ እንጂ ያላንተ የማይሆኑ ብዙ ነገር አለ

☞ያላንተ የማይሞቅ ቤት አለ፡፡
☞ያላንተ የማይሳካ ህልም አለ፡፡
☞ያላንተ የማያምር ጨዋታ አለ፡፡
☞ያላንተ የማይደምቅ ቤት አለ፡፡

የቻልከውን ያህል ሞክር አንተ ከነገሮች በላይ ነህ፡፡ በነገሮች አትረበሽ፡፡ አሁንም እልሀለው ህይወት በደመነፍስ አትሄድም ስልቷን እወቀው፡

፡ በህይወትህ ትላንት ያለፈውን መጥፎ ህይወትህን መቀየር ማስተካከል መሰረዝ አትችልም፡፡ የምትችለው አምኖ መቀበልና ለተሻለ ነገ መስራት ነው፡፡ "መቀየር የማንችለውን ነገር መቀበል ማለት ተስፋ መቁረጥ ወይም መሸነፍ ማለት ሳይሆን አቅማችንን የምንችለው ነገር ላይ ማዋል ማለት ነው::"
በፍፁም ተስፋ አትቁረጥ ግን አቅምህን የምትችለው ነገር ላይ አውለው፡፡ ሳትኖር ለመሞት አትቸኩል ይሄ ማለት ሳትፅፍ ለማጥፋት መሞክር ማለት ነው፡፡

#ለፈጣን እና ታማኝ መረጃ



#share
#share


@tloveandhope
71 viewsChristyan, 18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ