2023-05-26 20:28:27
የቀሲስ አክሊል ዳምጠው ክስ ጉዳይ...!
ቀሲስ አክሊል ዳምጠው ከወራት በፊት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ላይ ተፈጥረው የነበሩ ወቅታዊ ችግሮችን ለመፍታት በጠቅላይ ቤተክህነት ፅ/ቤት የተቋቋመ አቢይ ኮሚቴን በሰብሳቢነት እንዲመሩ የተመረጡ እጅግ የተከበሩ አባት ናቸው። ከሰኞ ግንቦት 14 ጀምሮ በቁጥጥር ስር ውለው ይገኛሉ።
ቀሲስ አክሊል ዳምጠው ተጠርጥረው የተያዙበትን የወንጀል ክስ የያዘ ወረቀት ተመለከትኩ፣ እንዲህ ይላል:
- የራሱን የፖለቲካ አላማ በማራመድ ህዝብ በመንግስት ላይ እምነት እንዳይኖረው በማድረግ
- ህገ-መንግስቱን እና ህገ-መንግስታዊ ስርአቱን በሀይል ለመቀየር
- ህዝብን አሳምፆ መንገድ እንዲዘጋ በማድረግ
- የስራ ማቆም አድማ በመቀስቀስ
- በተቀናጀ መልኩ የፖለቲካ ቅስቀሳ በማድረግ
- ተከታታይ እና ቀጣይነት ያለው አመፅ በማድረግ እና
- ለሁከት እና ብጥብጥ ድርጊት ማስፈፀሚያ የሚሆን በውጭ ሀገር እና በሀገር ውስጥ ገቢ እንዲሰባሰብ በማድረግ
- ህዝብ ለአመፅ እንዲነሳሳ በማድረግ
- ፅንፈኝነትን በማስተጋባት
- የፖለቲካ ተከታዮችን መመልመል እና ማደራጀት
- (ይቺ ታስቃለች...) ወታደራዊ ስልጠና እንዲሰለጥኑ በማድረግ
- የጦር መሳርያ በማስታጠቅ
- የታጠቁ ፅንፈኛ ሀይሎችን በተለያዩ መንገድ በመገናኘት ተልዕኮ መስጠት
- ወደ አዲስ አበባ ከተማ እና ሌሎች ቦታዎች ሁከት እና ብጥብጥ ለመፍጠር መንቀሳቀስ።
@EliasMeseret
67 views17:28