Get Mystery Box with random crypto!

#Update: በሳዑዲ አረቢያ በማቆያ ጣቢያ  ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን የመመለሱ ሥራ ነገ ይጀመራል ተ | TIKVAH-MAGAZINE

#Update: በሳዑዲ አረቢያ በማቆያ ጣቢያ  ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን የመመለሱ ሥራ ነገ ይጀመራል ተባለ

በሳዑዲ አረቢያ በማቆያ ጣቢያ የሚገኙ ዜጎችን በተቀናጀ መንገድ የመመለሱ ሥራ ነገ እንደሚጀመር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስታውቋል።

በሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ የተመራው የመንግሥት ልዑክ በሳዑዲ አረቢያ ሪያድ የኢትዮጵያ ኢምባሲ እና የጂዳ ቆንስላ ጀነራል ሰራተኞች እና የኮሙኒቲ አስተባባሪዎች ጋር በመወያየት በተመላሾች መለየት እና መመለስ ላይ የስራ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

በመሆኑም ሪያድ እና ጂዳ አካባቢ በማቆያ ጣቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያውንን ወደ ሀገር ቤት የመመለሱ ስራ ነገ አርብ ሚያዚያ 04 ቀን 2016ዓ.ም እንደሚጀመር አቅጣጫ ተቀምጦ ዝግጅቱ መጠናቀቁም ነው የተገለፀው።

@TikvahethMagazine