Get Mystery Box with random crypto!

#AddisAbaba በአዲስ አበባ የተማሪዎችን አጠቃላይ መረጃ የሚይዝና ጥራት አመላካች አሃዶችን | TIKVAH-MAGAZINE

#AddisAbaba

በአዲስ አበባ የተማሪዎችን አጠቃላይ መረጃ የሚይዝና ጥራት አመላካች አሃዶችን የሚተነትን ኢ ስኩል ሶፍትዌር በትምህርት ቤቶች ተግባራዊ ሊሆን ነው።

ሥርዓቱ በሁሉም አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ እንደሚሆን ሲጠቆም በትምህርት ቤቶች ከመረጃ አያያዝና ትንተና ጋር የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለመሙላት እንዲሁም ለተማሪዎች ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት ለማቅረብ እድል ይፈጥራል ተብሏል።

ሥርዓቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ግብዓቶች ሙሉ በሙሉ በሁሉም ትምህርት ቤቶች መሟላታቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ ገልፀዋል ሲል የዘገበው ኢዜአ ነው።

@TikvahethMagazine