የትራፊክ አደጋ መረጃዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመሰብሰብ የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈረመ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና የመንገድ ደኅንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት የመንገድ ትራፊክ አደጋ መረጃ አያያዝ ሥርዓትን ለመተግበር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ። በሀገራችን የሚደርሱ የመንገድ ትራፊክ አደጋዎች ዳታ አያያዝን በቴክኖሎጂ ለማገዝ ጥናትና ሶፍትዌር የማበልፀግ ሂደቱ አልቆ በተግባር ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል። ቴክኖሎጂው መረጃዎች በአግባቡ ተሰብስበው ፖሊሲዎች እንዲዘጋጁ እና አደጋን ለመከላከል የሚያስችሉ መፍትሄዎችንም ለማስቀመጥ እድል ይፈጥራል ተብሏል። @TikvahethMagazine 28.6K views17:35