Get Mystery Box with random crypto!

#AddisAbeba - በመዲናዋ 703ሺህ የተመዘገበ ተሽከርካሪ ይገኛል፤ - በአዲስ አበባ | TIKVAH-MAGAZINE

#AddisAbeba

- በመዲናዋ 703ሺህ የተመዘገበ ተሽከርካሪ ይገኛል፤

- በአዲስ አበባ በበጀት ዓመቱ 6 ወራት 211 ሰዎች ህይወት በመኪና አደጋ ሲያልፍ 991 ከባድና 749 ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።

- ከሟቾች ዉስጥም አብዛኛዉ ከ20 እስከ 49 ዕድሜ ክልል ያሉት ናቸው፤

- ከሚያጋጥሙ የሞት አደጋዎች 78 በመቶ ወንድ ሲሆን 22 በመቶ የሚሆነዉ የሞት አደጋ ሴቶች ላይ የሚያጋጥም ነው፤

- በከተማዋ ከሚፈፀሙ የመኪና አደጋዎች 80 በመቶ የሚሆነዉ ደግሞ እግረኞች ላይ ነዉ፤

በስድስት ወራት ውስጥ በተለያዩ የመዲናዋ መንገዶች ላይ በተደረገ ክትትል፦

- 17ሺህ 759 ተሽከርካሪዎች ከፍጥነት በላይ በማሽከርከር፤

- 2698 የደህንነት ቀበቶ ያላደረጉ፤

- 294 ጠጥተው የሚያሽከረክሩ፤

- 4818 ስልክ እያወሩ በሚያሽከረክሩ የትራንስፖርት አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደተወሰደ ተገልጿል።

ይህ የተነገረው የመንገድ ደህንነት ምክር ቤት የስድስት ወራት አፈፃፀም ግምገማና ውይይት ባካሄደበት መድረክ ነው።

#በተጨማሪ

በ2015 ዓ.ም ባለፉት ዘጠኝ ወራት በጥናት በተለዩ 20 የትራፊክ መብራቶችና አደባባዮች ላይ ግብይት የፈፀሙ እና በልመና ለተሰማሩ ሰዎች ምጽዋት ሲሰጡ የተገኙ አንድ ሺህ 463 አሽከርካሪዎች ላይ ቅጣት ተጥሏል ተብሏል።

@tikvahethmagazine