በሁለተኛው ዙር የመፅሀፍት እና የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ማሰባሰብ ስራ ፦ - አንድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል (ስሙ እንዲገለፅ ያልፈለገ) አንድ Hp ላፕቶፕ ኮምፒዩተር አበርክቷል። - አንድ የቤተሰባችን አባል 3000 ብር ወጪ የተደረገባቸውን አጋዥ መፅሀፍት ገዝቶ አበርክቷል። በዚሁ አጋጣሚ ጃፋር መፅሀፍት ቤትን እናመሰግናለን። ውድ ቤተሰቦቻችን የሁለተኛው ዙር የማሰባሰብ ስራ ጦርነት ለጎዳቸው ት/ቤቶች የሚውል ሲሆን ፦ - ከ9-12 ክፍል ያሉ ማንኛውም መፅሀፍት - ከ1-8 ያሉ አጋዥ መፅሀፍት - ቤት ውስጥ ያገለገለ ኮምፒዩተር - ፕሪንተር - የፕሪንተር ቀለም - ነጭ ወረቀት በተጨማሪ ለአንድ የህዝብ ቤተ መፅሀፍ ትውልድን የሚያንፁ ልብወልደ ሆነ ማንኛውም መፅሀፍ ማበርከት ትችላላችሁ። አዲስ አበባ ያላችሁ ነገ ቅዳሜ እና እሁድ ያላችሁበት ድረስ መምጣት እንችላለን ደውሉልን ፦ 0919743630 ከሰሞኑን በሀዋሳ ያሉ አስተባባሪዎችን እናሳውቃለን። #TikvahFamily @tikvahethiopia 10.7K views18:14