#እናመሰግናለን የሁለተኛው ዙር የመማሪያ መፅሀፍት እና ቁሳቁስ የማሰባሰብ ስራን ተከትሎ ፖሊኪዩር መድሃኒት ቤት 10 ሺህ ብር የወጣባቸውን መፅሀፍት ገዝቷል። በቀጣይ ቀናትም ያስረክባል። ሌላ አንድ የቤተሰባችን አባል 5 ሺህ ብር የወጣበት መፅሀፍ ልብወለዶችን ጨምሮ አስረክቧል (ለህዝብ ቤተመፅሀፍ)። ውድ ቤተሰቦቻችን በጦርነት የተጎዱ ትምህርት ቤቶችን ለማገዝ ፦ - በቤታችሁ ውስጥ ያለ የማትጠቀሙበት / ያገለገለ ዴስክቶፕ / ላፕቶፕ ኮምፒዩተር፣ - ነጭ ወረቀት - ፕሪነተር - የፕሪንተር ቀለም - ከ9 - 12 ማንኛውም መፅሀፍ - ከ1-8 አጋዥ መፅሀፍ አበርክቱ። አዲስ አበባ ያላችሁ #ቅዳሜ እና #እሁድ በየአካባቢያችሁ የምንመጣ ይሆናል ፦ 0919743630 በሀዋሳ ከቀናት በኃላ ይጀምራል። @tikvahethiopia 12.6K views06:46