ለእንስሳት ዘርፍ ባለሙያዎች የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን እንስሳት ዘርፍ ባለሙያዎችን በተመረጡ 43 ከተሞች ተደራጅተው የእንስሳት ዘርፍ ልማቱን የሚያሳድጉ ፓይለት ፕሮጀክቶች ላይ ድጋፍ ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን አስታውቀዋል። በዚህም በእንስሳት ዘርፍ የተማሩ እና የሰለጠኑ ባለሙያዎችን በኅብረት ስራ ማኅበራት በማደራጀት በዶሮ ሥጋ፣ በእንቁላል፣ በወተት ምርት፣ በግመል ወተት፣ በበግ ሥጋ እና በፍየል ሥጋ ምርት እንደሚሰማሩ ይደረጋል ተብሏል። በመሆኑም በእንስሳት ዘርፍ ላይ የተማሩ ባለሞያዎች በቅድሚያ በየከተሞቹ ባሉ ኅብረት ሥራ ማዳራጃ ባለሥልጣን መደራጀትና በእነሱ በኩል የሚሰጠውን መመሪያ ተከትላችሁ አስፈላጊ በሆነው ሂደት ውስጥ ማለፍ እንደሚገባ ተገልጿል። @tikvahethmagazine 16.4K viewsedited 09:11