Get Mystery Box with random crypto!

በ11 ወራት ከተሞከሩ የሳይበር ጥቃቶች ከ97 በመቶ ከሽፏል ተባለ በኢትዮጵያ በ11 ወራት ከተሞከ | TIKVAH-MAGAZINE

በ11 ወራት ከተሞከሩ የሳይበር ጥቃቶች ከ97 በመቶ ከሽፏል ተባለ

በኢትዮጵያ በ11 ወራት ከተሞከሩ የሳይበር ጥቃቶች ከ97 በመቶ የሚልቀውን በማክሸፍ የ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ኪሳራ ማዳን መቻሉ ተነግሯል።

የሳይበር ጥቃቱ በፋይናንስ እና የሚዲያ ተቋማት ላይ በብዛት ኢላማ ያደረገ መሆኑም ታውቋል።

የሳይበር ምሕዳር በባህሪው ድንበር የለሽና ኢ-ተገማች በመሆኑ ዓለም በዚህ መጠነ ሰፊና ተለዋዋጭ ወንጀል በየቀኑ በአማካይ 16 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር ሀብት ታጣለችም ተብሏል።

የሳይበር ወንጀል በአውፓዊያኑ 2015 በዓለም ላይ 3 ትሪሊየን ዶላር ካደረሰው ኪሳራ በእጅጉ እያንሰራራ መጥቶ በ2021 ደግሞ 6 ትሪሊየን ዶላር አሳጥቷል።

ከኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር ያገኘነው መረጃ እንዳመላከተው በየዓመቱ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣው ዓለም ዐቀፍ የሳይበር ወንጀል በ2025 ከ10 ነጥብ 5 ትሪሊየን ዶላር በላይ ሊያሳጣ እንደሚችል ተገምቷል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot