#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን በ10 ወራት ለ29 ሺሕ 942 ገንቢዎች የግንባታ ፈቃድ መስጠቱን አስታውቋል።
ከባለስልጣኑ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በበጀት ዓመቱ አስር ወራት፦
- 10 ሺሕ 783 የፕላን ስምምነት፤
- 3 ሺሕ 985 አዲስ ግንባታ ፈቃድ፤
- 968 የማሻሻያ የግንባታ ፈቃድ፤
- 174 ቀደም ብለው ለተገነቡ ህንፃዎች የግንባታ ፈቃድ፤
- 1 ሺሕ 27 ህንፃዎች የማራዘሚያ ፈቃድ፤
- 11 ሺሕ 418 ግንባታዎች የእድሳት ፈቃድ ተሰጥቷል።
@tikvahethmagazine