Get Mystery Box with random crypto!

#AddisAbaba በአዲስ አበባ ከተማ ከፖሊስ አባላት ጋር ቶክስ በመክፈታቸው የተነገረላቸው የፋ | TIKVAH-ETHIOPIA

#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ ከፖሊስ አባላት ጋር ቶክስ በመክፈታቸው የተነገረላቸው የፋኖ መሪዎችና አባላት መገደላቸውን ፖሊስ ገልጿል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ባወጣው መግለጫ ፤
- ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ ፣
- አቤኔዜር ጋሻው አባተ
- ሀብታሙ አንድአርጌ ተሰማ የተባሉት " ፋኖ " ቡድን አባላት በከተማው " የሽበር ጥቃት ለመፈፀም እየተንቃሰቀሱ " መሆኑን የፀጥታ አካላት ባደረጉ ክትትል እንደደረሱባቸው ገልጿል።

ዛሬ " ሚሊኒየም አዳራሽ " አካባቢ ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር ለማዋል የፖሊስ አባላት እንቅስቃሴ እያደረጉ ባለበት ሁኔታ " እጃቸውን እንዲሰጡ ቢጠየቁም ፍቃደኛ ባለመሆን በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2C 14373 አ/አ አይነቷ ሱዙኪ ዲዛዬር መኪናን በመጠቀም ተኩስ መክፈታቸውን " አመልክቷል።

በዚም ናሁሰናይ አንዳርጌ ታረቀኝ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ ሲሞት ሀብታሙ አንዳርጌ ተሰማ በተኩስ ልውውጡ መሃል  መገደሉን ገልጿል።

አቤኔዘር ጋሻው ሳይቆስል በቁጥጥር ስር መዋሉን አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በነበረው የተኩስ ልውውጥ ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ቆስለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የፈኖ አባለቱ አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ግለሰብ በመኪናቸው እንዲጭኗቸው ቢያስገድዷቸውም ግለሰቡ አልተባበርም በማለታቸው  እንደገደሏቸው አመልክቷል።

አቶ እንደሻው ሲያሽከርክሯት የነበረቸው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 አ/አ  80457 በጥይት ጉዳት እንደረሰባት አዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

@tikvahethiopia