Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-ETH

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikfahethiopia — TIKVAH-ETH T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tikfahethiopia — TIKVAH-ETH
የሰርጥ አድራሻ: @tikfahethiopia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.20K
የሰርጥ መግለጫ

ትኩስ ዜና በ tikvah ከማንም በፊት ያገኛሉ።
#share በማድረግ ይተባበሩን
Contact @Beki_Boy
Buy ads: https://telega.io/c/tikfahethiopia

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-02 07:53:38 #መረጃ በራያ ግንባር!

ትናንት አመሻሹን ከጎብዬ ተነስቶ የአልውሀን ወንዝ እሻገራለሁ ብሎ የሞከረው መንጋ አልውሀ ሜዳ ላይ የእሳት እራት ሆኗል! ታቹን በወርቄ የገባው ሀይል በቆርኬ በኩል ሰብሬ አልፋለሁ ብሎ ቢሞክርም በትንታጉ የወሎ ፋኖ ተጋድሎ እና በሀገር መከላከያ ሰራዊታችን ልዩ ብቃት አፈር ድሜ በልቷል! በዚህ አቅጣጫ የመጣው መንጋ አላማው የባቡር መስመሩን መሿለኪያ በመጠቀም ወደ ሀራ ከተማ ሰብሮ መግባት ነበር! ነገር ግን አልተሳካለትም! የአልውሀ ሜዳ ለወራሪው ሀይል ገሀነም ሆኖበታል ።

በጀነራል ሀሰን ከረሙ፡በሞገስ ከበዴ እና በሻለቃ ደምሌ አራጋው የሚመራው ሽርጣሙ ኮማንዶ የሚል የክብር ስም ከመከላከያ ሰራዊታችን የተቸረው የወሎ ፋኖ ወያኔን ወርቄ ላይ፡ቂልጡ ላይ፡አልውሀ ሜዳው ላይ እንድሁም ጎብዬ ላይ መፈናፈኛ አሳጥቷታል! የአማራ ልዩ ሀይል እና ባለ ቀይ ቦኔቱ የመከላከያ ኮማንዶ በሌላ በኩል ገብቶ ወያኔን ሌላ ታሪክ እየሰራት ነው!
@tikfahethiopia
321 views04:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 19:58:02
አሁናዊ መረጃ ከስፍራው!

በወልቃይት በረከት እና ሉግዲ መሃከል ትናንት በረድ ብሎ የነበረው ጦርነት ዛሬ ሌሊት 9 ሰዓት በድጋሚ ጀምሮ እስከ ረፋዱ 3 ሰዓት ድረስ በከባድ መሳሪያ የታገዝ ጦርነት ተካሂዷል።

የትህነግ ጦር አስቀድሞ ከሰራቸው 5 ባለ ሶስት ደረጃ ምሽጎች ውስጥ ሶስቱ ተሰብረዋል። የተቀሩትም በቀጣይ 24 ሰዓታት ውስጥ እንደሚሰበሩ አሁን ያለው ጦርነት ምስክር ነው። መከላከያ ሰራዊቱ እና ልዮ ኃይሉ በጥምር እያጠቁ ነው። ከሁመራ ከተማ 25 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ነው ጦርነቱ በማይካድራ አቅጣጫ እየተካሄደ ያለው።

ፋኖ፣ሚሊሻውና የአካባቢው ታጣቂ በቅርብ እርቀት ላይ ቢሰፍርም እስካሁን እንዲገባ አልተፈቀደም። ማይካድራን ጨምሮ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ከተማ ሁመራ በፋፁም መረጋጋት እና ሰላም ትገኛለች።

@Tikfahethiopia
692 views16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 19:13:52
ሰበር ዜና!

በራያ ግምባር አሁን #ጎብየ በጀግናው የመከላከያ፤የአማራ ልዩ ኃይልና ፋኖ ጥምር ጦር ነጻ ሁናለች! ይቀጥላል ...!

@Tikfahethiopia
725 views16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 10:08:13
የህወሓት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ኃይሎች ጥቃት ከፍተዋል ብለዋል። በጉዳዩ ላይ የኤርትራም ሆነ የኢትዮጵያ መንግስታት ዛሬ ያሉት ነገር የለም።

@Tikfahethiopia
@Tikfahethiopia
49 views07:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 09:45:28
ቪዲዮ - በጦርነቱ የተማረኩት ህፃናት ልጆች ምን ይላሉ?

"... ለአንድ ባለስልጣን ተብሎ፣ ለአንድ ሰው ብሎ የሞተውን ሰው እናንተ አላያችሁም የሞተው እንደኔ ቢማረክ ጥሩ ነበር"

"... የትግራይ ህዝብ ይሄን ጁንታ አትመኑት ፣ አትውጡ"

"...አንድ የሀብታም ልጅ እኮ አታገኙም፣ የደሀው ልጅ ነው ፣ የደብረፂዮን ልጅ የለም፣ የጌታቸው ረዳ ልጅ የለም... የትግሬ የደሀ ልጅ ግን አለ፣ የሞተም አለ። የአለም ህዝብ ቢያየን ጥሩ ነው። ዝም ብሎ እየሞትን እያየን ነው"

@tikfahethiopia
123 views06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 19:24:23 ሰበር ዜና

በዋግ ኽምራ ዞን በዝቋላ ወረዳ ስር የነበረና ጁንታው ይተማመንበት የነበረው የቅዳሚት ማዕከል ምሽግ በጥምር ሃይሉ ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል:: በዚህም ምክንያት ጁንታው ወደ አብርገሌ ከተማ እየሸሸ ነው አብርገሌ ማለት ለሰቆጣ 65 ኪሎ ሜትር ይርቃል ለመቀሌ ደግሞ 45 ኪሎ ሜትር ይርቃል

@Tikfahethiopia
719 views16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 15:58:14 ሸኔ

ከወራሪው የህወሓት ኃይል ጋር የተሰለፉ በርካታ የሸኔ ታጣቂዎች ተማረኩ

የህወሓት ወራሪ ኃይል ሰሞኑን ጥቃት በከፈተባቸው የአማራና የአፋር ግንባሮች ከቡድኑ ጋር ተሰልፈው ሲዋጉ የነበሩ በርካታ የሸኔ ታጣቂዎች መማረካቸው ታወቀ፡፡

የህወሓት ወራሪ ኃይል በአማራና በአፋር ግንባሮች ጥቃት ከመክፈት ጎን ለጎን በተለያዩ አካባቢዎች ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ጋር በመነቀናጀት ሽብር ለመፍጠር እየሠራ እንደሚገኝ የጠቆሙት ምንጮች፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአሸባሪነት ከተፈረጀው የሸኔ ቡድን ጋር በገባው ስምምነት መሠረትም በተለያዩ ግንባሮች የቡድኑን ታጣቂዎች አሰልፏል፡፡

በተለይ በቆቦ ከተማ ወረራ የፈጸመው ህወሓት የሸኔ ታጣቂዎችን ከፊት በማሰለፍ ወደ ፊት ለመግፋት ቢሞክርም በሀገር መከላከያ ሠራዊትና በጥምር ጦር በተሰነዘረበት መልሶ ማጥቃት ከፍተኛ ኪሳራ እንደደረሰበት የተገለጸ ሲሆን፤ በርካቶችም ተማርከዋል፡፡ ከምርኮኞችም መካከልም በርካታ የሸኔ ታጣቂዎች መኖራቸው ታውቋል፡፡

ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶችና ከውስጥ ባንዳዎች ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ  ቀውስ ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ህወሓት በተለያዩ ግንባሮች ጥቃት ከመክፈት ጎን ለጎን  በየክልሎች የሚገኙ ታጣቂዎች የሎጀስቲክስ፣ የፋይናንስና የመሣሪያ ድጋፍ እንዲደርሳቸው እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡

@Tikfahethiopia
859 views12:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 15:57:04
በመቀሌ ከተማ የአየር ድብደባ መፈፀሙ ተገለፀ!!

የህወሓት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ በትዊተር ገፃቸው እንዳስታወቁት በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ትናንት እኩለ ሌሊት በሰው አልቫ አውሮፕላን ድብደባ ተፈፅሟል።ድብደባው ያደረሰዉ ጉዳት ስለመኖር-አለመኖሩ ግን ቃል አቀባዩ አልገለፁም።

በፌደራል መንግሥት እና በሕወሃት መካከል በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ግጭት ካገረሸ ወዲህ፣ በመቀሌ የአየር ድብደባ እንደተፈጸመ ሕወሃት ሲገልጽ የአሁኑ ሁለተኛው ነው።

@Tikfahethiopia
@Tikfahethiopia
826 views12:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 12:25:26
ሕወሓት በዋግ፣ በወልቃይት አቅጣጫና በሱዳን ድንበር አካባቢ ወረራ ከፍቷል” የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት

@Tikfahethiopia
@Tikfahethiopia
394 viewsedited  09:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 09:16:43 ህ_ወሓት በሁመራ በኩል ጦርነት ከፍታለች!

ነሐሴ 25/2014 ዓ.ም  ህወሓት በሁመራ በኩል ጦርነት ከፍቷል። ከሁመራ....20 ኪሎ ሜትር "ዝጓላ" ከሚባለው አካባቢ ነው ጦርነት ከፍቶ ያደረው፤ አሁንም ውጊያ እንደቀጠለ ነው። የሁመራ ህዝብም ወደ ቦታው እየተመመ ይገኛል።

ፍልሚያውን ራሱ ትህነግ/ህወሓት  ጀምሮቷል። ህዝባችን ከመከላከያ ሰራዊት፣ ከአማራ ልዩ ኃይል ፣ ከአማራ ፋኖ እና ማሊሻ ጋር በመሆን የተለመደውን አኩሪ ጀብደ በወራሪ ቡድን ላይ ይፈፅማል!!

ቢትወደድ ብርሃኔ ከወልቃይት

@tikfahethiopia
@tikfahethiopia
583 views06:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ