ከንቲባ አዳነች አቤቤ የመስቀል በዓልን ምክንያት በማድረግ በጦር ሃይሎች ሆስፒታል ተገኝተው የምሳ ግብዣ አደረጉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአሉን ምክንያት በማድረግ በጦር ሃይሎች ሆስፒታል ተገኝተው የሰራዊቱ አባላት በመጎብኘት የተለያዩ ድጋፎችንና የምሳ ግብዣ ያደረጉ ሲሆን በዚህ ወቅት ባደረጉት ንግግር ‹‹በእናንተ መሃል ተገኝቶ በዓልን ማሳለፍ ከክብርም በላይ ክብር ነው፤ እናንተ የአገራችን ጀግኖች የአገራችን አርማ ናችሁ"ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በገጠማት ፈተናዎች ሁሉ ፀንታ መሻገር እንድትችል ከስጦታ ሁሉ በላይ የሆነውን ስጦታ በመስጠት ሃገራችሁን ያፀናችሁ በመሆናችሁ ከእናንተ ጋር መሆን በእጅጉ ያስደስተናል ሲሉም ጨምረዋል፡፡ መልካም በአል • @ThinkAbyssinia • 8.0K views09:50