ኢትዮጵያውያኑ ሰዓልያን በጀርመን በተካሄደ የስዕል ውድድር አሸነፉ በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስነ ጥበብ ትምህርት ክፍል ሠልጣኝ የሆኑት ፍሬወይኒ እንድሪያስ እና ኢዮብ እሸቱ በጀርመን ሌፕዥግ ከተማ በተካሄደ የስዕል ውድድር ላይ አንደኛና ሁለተኛ ደረጀን ይዘው ማሸነፋቸውን የአዲስ አበባ ቴክኒክ ሙያ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታውቋል፡፡ በውድድሩ አሸናፊ የሆነው ኪነ ቅርፅም የአዲስ አበባ እህት ከተማ በሆነችው የጀርመኗ ሌፕዥግ ከተማ በሚገኘው የአዲስ አበባ አደባባይ ተብሎ በተሰየመው ቦታ ላይ የሚተከል ይሆናል ነው የተባለው። መልካም ደመራ በዓል • @ThinkAbyssinia • 2.2K views13:47