ትውልደ ኢትዮጵያዊው ሼፍ ማርከስ ሳሙኤልሰንና ባለቤቱ ሞዴል ማያ ሀይሌ
በሜት ጋላ ደምቀው አምሽቷዋል
ትውልደ ኢትዮጵያዊው ሼፍ ማርከስ ሳሙኤልሰንና ባለቤቱ ሞዴል ማያ ሀይሌ
ትላንት ምሽት በአሜሪካ በተካሄደው ሜት ጋላ የፋሽን ፕሮግራም ላይ እጅግ በጣም ቆንጆ ከሆኑ ጥንዶች አንዱ ተብለውም ተሰይመዋል።
በእለቱ ጥንዶቹ በኢትዮጵያዊያን የክብር አልባሳት (ንግሥት ሳባ ቀሚስ እና ካባ) የደመቁ ሲሆን ከኢትዮጵያውያንም ሙገሳ ተችሯቸዋል።
ዘ ሜት ጋላ የተሰኘው ፕሮግራም በኒውዮርክ ከተማ ለሚገኘው የሜትሮፖሊታን ሙዚየም የስነጥበብ አልባሳት ተቋም ጥቅም የሚውል ዓመታዊ የገንዘብ ማሰባሰብያ ዝግጅት ነው። በዓለም ላይ በጣም ታዋቂው የፋሽን ዝግጅት ተብሎ በሰፊው የሚታወቅ ሲሆን በእለቱ እንደ ፋሽን፣ ፊልም፣ ቴሌቪዥን፣ ሙዚቃ፣ ስፖርት እና ማህበራዊ ሚዲያ ያሉ ታዋቂ ሰዎች በዚህ የፋሽን ዝግጅት ላይ ይጋበዛሉ።
ትውልደ ኢትዮጵያዊው ሼፍ ማርከስ ሳሙኤልሰንና ባለቤቱ ሞዴል ማያ ሀይሌ ኢትዮጵያን በትልቅ መድረክ ሲያስጠሩ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ አይደለም። ከዚህ ቀደምም በአባይ ጉዳይ ለአለም እውነታው ለማሳየት በብዙ ሲጥሩም ነበር።
• @ThinkAbyssinia •