Get Mystery Box with random crypto!

Isaiah 48 Apologetics

የቴሌግራም ቻናል አርማ thetriune — Isaiah 48 Apologetics I
የቴሌግራም ቻናል አርማ thetriune — Isaiah 48 Apologetics
የሰርጥ አድራሻ: @thetriune
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.97K
የሰርጥ መግለጫ

✟ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ✟
"14 The grace of the Lord Jesus Christ, and the love of God, and the communion of the Holy Ghost, be with you all. Amen."
(2Corinthians 13:14)
📌 ሌላኛው ቻናላችን:- @ovadiah

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-06-11 11:53:21 የሐዋርያት ሥራና የእግዚአብሔር መልአክ (ክፍል 3)

ባለፉት ተከታታይ ክፍሎች ተቃዋሚዎች የሐዋርያት ሥራ 7 ተመርኩዘው ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ይገለጥ የነበረው የእግዚአብሔር መልአክ አይደለም ለማለት የሚያነሱትን ተቃውሞ እየመለስን ነበር

እስጢፋኖስ እንዴት በአንድ አውድ የክርስቶስንም የመልአኩንም አምላክነት በመናገር እንዴት ያ መልአክ/መልእክተኛ ራሱ ጌታ ኢየሱስ መሆኑን እንደመሰከረ አይተናል። መልአኩ ራሱ ጌታ ኢየሱስ ስለሆነ፥ በተመሳሳይ አውድ አምላክነቱንና ጌትነቱን መሰከረ። ይህ እስጢፋኖስ ጌታ ኢየሱስ ያ የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን እንደሚያምን በግልፅ ያሳያል።

ዛሬም ጌታ ቢፈቅድ እንዴት እስጢፋኖስ ያ ለሙሴ የተገለጠው መልአክ ራሱ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን እንደመሰከረ እንመለከታለን

ባለፈው ክፍል እንዳየነው፥ እስጢፋኖስ ክርስቶስ አምላክ እንደሆነ በተግባር የመሰከረ የቤተክርስቲያን ሰማዕት ነው። ለእስጢፋኖስ ጌታ ኢየሱስ በሰማይ የሚኖር፥ ጸሎትን የሚሰማ፥ በሞትና በጭንቅ ሰአት ስሙ የሚጠራ፥ ነፍስን የሚቀበል፥ ኀጢአትን የመቁጠርና ያለመቁጠር ስልጣን ያለው ጌታ ነው። ይህ የእግዚአብሔር ብቸኛ ባህርይ ሲሆን፥ ክርስቶስ የእነዚህ ባህሪያት ባለቤት መሆኑ፥ አምላክ መሆኑን ያረጋግጣል። እስጢፋኖስም ክርስቶስ እነዚህ ባህሪያትና ስልጣናት እንዳሉት መመስከሩ፥ ኢየሱስ አምላክ መሆኑን እንደሚያምን ያረጋግጣል

ነገር ግን ሐዋርያት ሥራ 7 በጥልቀት ስናጠና፥ እስጢፋኖስ ያመለከው ይህ ጌታ ኢየሱስ እግዚአብሔር አብን እንዳልሆነ እንረዳለን፦

“እነሆ፤ ሰማያት ተከፍተው፣ #የሰው_ልጅም #በእግዚአብሔር #ቀኝ ቆሞ አያለሁ” አለ።”
ሐዋርያት 7፥56 (አዲሱ መ.ት)

ከአብርሃም አንስቶ እስከ ክርስቶስ መምጣት ድረስ ያለውን ወንጌል ከሰበከላቸው በኋሃ፥ በሸንጎው ስብሰባ የነበሩት ሁሉ ጥርሳቸውን አፋጩበት። እርሱ ግን በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ፥ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ ተመለከተ

እስጢፋኖስ ኢየሱስን በእግዚአብሔር አብ ቀኝ ቆሞ ማየቱ፥ ክርስቶስ አብ እንዳልሆነ የሚያረጋግጥ ነው። ይህ እርሱ የተመለከተው ነገር ራዕይ ነው። ራዕይ ደግሞ አንድ የሆነ መልእክትን ለማስተላለፍ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚሰጥ መገለጥ ነው። ለምሳሌ፦

“ከዚያም በዙፋኑና በአራቱ ሕያዋን ፍጡራን፣ በሽማግሌዎቹም መካከል የታረደ የሚመስል #በግ ቆሞ አየሁ፤ በጉም #ሰባት_ቀንዶችና ሰባት ዐይኖች ነበሩት፤ እነርሱም ወደ ምድር ሁሉ የተላኩት ሰባቱ የእግዚአብሔር መናፍስት ናቸው።”
ራእይ 5፥6 (አዲሱ መ.ት)

➣ በዚህ ስፍራ ሐዋርያው ዮሐንስ ክርስቶስን በሰማይ ሲመለከተው እናያለን። ሐዋሪያው ዮሐንስ በመላው መጽሐፍ የሚመለከተው ራዕይ ነው (ራዕ 1:1) ስለዚህ የሚያያቸው ነገሮች በሙሉ የሚያስተላልፉት መልእክት አላቸው። በዚህ ቦታም ክርስቶስን ሰባት አይኖችና ሰባት ቀንዶች እንዳሉት በግ ተመስሎ ያየዋል። በበግ መመሰሉ፥ ለሰው ልጆች መተላለፍ ኀጢአት መስዋዕት የሆነው፥ በደሙም የሰዎች ኃጢአት ያጠበው እርሱ መሆኑን ያመልክታል (ዮሐ 1:29) ቀንዶች እንዳሉት መመሰሉ፥ ፍጹም ኀይልና ስልጣን እንዳለው የሚያመለክት ነው። ቀንድ የሀይልና የጉልበት ምልክት ነውና (1 ሳሙ 2:1) እነዚህ ምሳሌዎች በራዕይ ሲታዩ፥ የሚያስተላልፉት መልእክት አለ። እነዚያን ጽንሰ ሀሳቦች ለማመልከት ነው ጥቅም ላይ የዋሉት

በሐዋ 7ም እስጢፋኖስ ኢየሱስን በአብ ቀኝ ማየቱ፥ የአካል (person) ልዩነት እንዳለ ያሳያል። በቀኙ ቆሞ ማየቱ የሚያስተላልፈው መልእክት ይህ ነው። አብና ኢየሱስ የተለያዩ ማንነቶች መሆናቸውን። የተለያዩ ማንነቶች በመሆናቸው አንዱ በሌላው ቀኝ ቆሞ ታየው

እግዚአብሔር መንፈስ ነው (ዮሐ 4:24 ኢሳ 31:3) ሰማይንና ምድርን የሞላ ረቂቅ ባህርይ ነው (ኤር 23:24 መዝ 139:7) በመለኮቱ ቅርጽና መልክ የሚታይ ገጽታ የለውም (ዘዳ 4:11-12) ስለዚህ በምድራዊው አለም እንዳለው ቀኝና ግራ የለውም። ነገር ግን በራዕዩ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ ታየው። ግራና ቀኝ የሌለው እግዚአብሔር በቀኙ ልጁ ኢየሱስ ቆሞ የታየበት ምክንያት፥ የተለያዩ ማንነቶች መሆናቸውን ለማመልከት ነው። ከላይ እንዳልነው፥ በራዕይ የሚታዩ ነገሮች በሙሉ የሚያስተላልፉት መልእክት አለ። አንዱ በሌላው ቀኝ ቆሞ መታየቱ፥ የሚያስተላልፈው አንዱ መልእክት አብና ልጁ ክርስቶስ የተለያዩ አካላት መሆናቸውን ለማሳየት ነው።

ከአብ የተለየ ማንነት ካልሆነ ለምን አንዱ በሌላው ቀኝ ቆሞ ይታያል?

የተለያዩ ማንነቶች ባይሆኑ ኖሮ፥ በፍጹም አንዱ በሌላው ቀኝ ቆሞ ባልታየ ነበር። ሁሌም በራዕይ አጠገብ ለአጠገብ፥ ወይንም አንዱ ከሌላው ፊት ወይንም በቀኙ ቆመው የሚታዩት የተለያዩ አካላት ናቸው። አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ፥ አንድ አካል በሌላ አካል ቀኝ እንደቆመ ወይንም በፊቱ እንደቆመ ሆኖ የተገለጠ አካል የለም። በራዕይም ሆነ በሕልም አንዱ በሌላው ቀኝ ቆሞ የሚታዩት የተለያዩ አካላት ናቸው። ምክንያቱም ሊተላለፍ የተፈለገው መልእክት ያ ነውና። በራዕይ የታዩና የተገለጹ ነገሮች የሚያስተላልፉት መልእክት አለና። እርሱም፥ ሁሌም ቢሆን በቀኝ ወይንም በፊቱ ቆመው የሚታዩ አካላት የተለያዩ አካላት ናቸው። በዚህ መልኩ መቆማቸው የሚያስላልፈው አንዱ መልእክት ይህ ነው።

➣ ይህም በሐዋርያት ስራ ጸሐፊም የተረጋገጠ እውነት ነው

“እስጢፋኖስ ግን በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት፣ የእግዚአብሔርን ክብር፣ እንዲሁም #ኢየሱስ በእግዚአብሔር #ቀኝ #ቆሞ #አየና፣”
ሐዋርያት 7፥55 (አዲሱ መ.ት)

የሐዋርያት ስራ ጸሐፊ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ እንዳየ ሲመሰክር እንመለከታለን። ይህ የምርም ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ እንደነበር የሚያረጋግጥ ነው። የሐዋርያት ስራ ጸሐፊ፥ ኢየሱስ በአብ ቀኝ ቆሞ ማየቱ እስጢፋኖስ ሁለት የተለያዩ አካላትን ለማየቱ ተጨማሪ ምስክርነት ነው። እስጢፋኖስ ጌታን በእግዚአብሔር ቆሞ ማየቱ እርሱና አብ የተለያዩ አካላት መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ነው። ጸሐፊውም ልክ እንደ እስጢፋኖስ ጌታ ኢየሱስና እግዚአብሔር አብ የተለያዩ አካላት መሆናቸውን ለማመኑ ምክስርነት ነው።

ይህ እንዴት ለሙሴ የተገለጠው መልአክ ክርስቶስ መሆኑን ያረጋግጣል?

ባለፈው ክፍል በብዙ ማስረጃ እንዳየነው፥ እስጢፋኖስ ለሙሴ የተገለጠው መልአክ/መልእክተኛ አምላክ መሆኑን መስክሯል። በሲና ተራራ የተናገረው ጌታ መሆኑን፥ ጫማውን እንዲወልቅ ያዘዘው ጌታ መሆኑን፥ የአባቶቹ አምላክ መሆኑን የነገረው እርሱ መሆኑን፥ ሙሴን የጠራው አምላክ መሆኑን፥ ሙሴም ለማየት የፈራው እግዚአብሔር እርሱ መሆኑን መስክሯል። ይህ እስጢፋኖስ ለመልአኩ አምላክነት የሰጠው ምስክርነት ነው

ነገር ግን፥ ይህ አምላክ መሆኑን የመሰከረለት መልአክ፥ ከላኪው (ከአብ) የተለየ አካል መሆኑን እስጢፋኖስ አረጋግጧል፦

“እንግዲህ እነዚያ፣ ‘ገዥና ፈራጅ አድርጎ የሾመህ ማን ነው?’ ብለው የናቁትን ይህንን ሙሴ #እግዚአብሔር በቊጥቋጦው ውስጥ በታየው #መልአክ #አማካይነት ገዥና ታዳጊ አድርጎ ወደ እነርሱ ላከው።”
ሐዋርያት 7፥35 (አዲሱ መ.ት)

ከላይ መልአኩ እንዴት ለሙሴ እንደተገለጠለት ከተናገረ በኋላ፥ እግዚአብሔር በመልአኩ አማካኝነት ገዢና ታዲጊ አድርጎ እንደላከው ይናገራል። ይህ ማለት እግዚአብሔር ሙሴን በመልአኩ አማካኝነት ገዢና ታዳጊ አድርጎ ሾሞት ነበር ማለት ነው
382 views08:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 18:03:40 ከላይ ባለው ቁ.59 ላይ ጌታ ብሎ የጠራው የኢየሱስን በመሆኑ፥ በዚህም ስፍራ ጌታ ብሎ የሚጠራው እርሱን መሆኑን እናረጋግጣለን። በዚህ ቦታ ላይ፥ ጌታ የሚሰሩትን ኀጢአት እንዳይቆጥርባቸው ይለምነዋል

እስጢፋኖስ በሚሞትበት ሰአት ወደ ኢየሱስ ጸልዮ፥ የሰዎቹን ኀጢአት እንዳይቆጥር መጸለዩ፥ ክርስቶስ አምላክ መሆኑን እንደሚያምን ያረጋግጣል። ምክንያቱም፥ በሰማይ ሆኖ የሰዎችን ኀጢአት የመቁጠርና ያለመቁጠር ስልጣን ያለው እግዚአብሔር ብቻ ነውና

“እግዚአብሔር #ኀጢአቱን #የማይቈጥርበት፣ በመንፈሱም ሽንገላ የሌለበት ሰው፣ እርሱ ቡሩክ ነው።”
መዝሙር 32፥2 (አዲሱ መ.ት)

“ #ኀጢአቱን፣ ጌታ ከቶ #የማይቈጥርበት ሰው ብፁዕ ነው።”
ሮሜ 4፥8 (አዲሱ መ.ት)

“ኢየሱስም፣ “አባት ሆይ፤ የሚያደርጉትን አያውቁምና #ይቅር #በላቸው” አለ። እነርሱም ልብሱን በዕጣ ተከፋፈሉት።”
ሉቃስ 23፥34 (አዲሱ መ.ት)

እስጢፋኖስ ይህን ልመና ወደ ክርስቶስ ማቅረቡ፤ ክርስቶስ በኀጢአት ጉዳይ ላይ ስልጣን ያለው አምላክ መሆኑን ለማመኑ ማረጋገጫ ነው። በኀጢአት ጉዳይ ላይ ስልጣን አለው ብሎ ስለሚያምን፥ ኀጢአታቸውን አትቁጠርባቸው አለ። ይህ ክርስቶስ አምላክ መሆኑን እንደሚያምንና ይህንንም ሀቅ እንደመሰከረ ያረጋግጣል።

ነገር ግን የክርስቶስን አምላክነት በመሰከረበት በዚሁ በራሱ አውድ፥ ለሙሴ የተገለጠው መልአክ እግዚአብሔር መሆኑን መስክሯል። ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ??

ለሙሴ የተገለጠለት መልአክ ራሱ ክርስቶስ ነውና!

እስጢፋኖስ በአንድ አውድ፥ የክርስቶስንም ለሙሴ የተገለጠው መልአክንም አምላክነት ሊመሰክር የቻለው፥ ያ ለሙሴ የተገለጠለት መልአክ ራሱ ክርስቶስ በመሆኑ ነው። እየተናገረ የነበረው ስለ ሁለት አካላት አልነበረም። ስለ አንዱ ስለ እግዚአብሔር ልጅ ነውና። ለዚህ ነው የክርስቶስንም የመልአኩንም መለኮትነት የመሰከረው። ያ መልአክ ራሱ ክርስቶስ ነውና

ለዚያም ነው በቁ.31-33 ላይ መልአኩን ጌታ ብሎ ጠርቶት፥ በቁ.59-60 ላይ ደግሞ ኢየሱስን ጌታ በማለት የጠራው። ያ መልአክ/መልእክተኛ ክርስቶስ መሆኑን ስለሚያምን ነው። ከላይ በማስረጃ እንዳየነው፥ በሁለቱም ሥፍራ "ጌታ" የሚለው ቃል የገባው መለኮትነትን ለማመልከት ነው። እስጢፋኖስ ለመለኮት ብቻ በሚገባ አውድ መልአኩንም ክርስቶስንም ጌታ ያለው፥ ያ መልአክ ራሱ ክርስቶስ ነው ብሎ በማመኑ ነው። ይህ ለዚህ እምነቱ ግልፅ ማሳያ ነው

ይቀጥላል
401 views15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 18:03:40 “ሙሴ ሁኔታውን ለመመልከት መቅረቡን እግዚአብሔር (ያህዌ) ባየ ጊዜ፣ ከቍጥቋጦው ውስጥ #እግዚአብሔር (ኤሎሂም) “ሙሴ፣ ሙሴ” #ብሎ #ጠራው፤ ሙሴም “አቤት እነሆኝ” አለው።”
ዘጸአት 3፥4 (አዲሱ መ.ት)

ይህ ከቁጥቋጦው ውስጥ ሙሴን ጠርቶ ያነጋገረው እግዚአብሔር፥ መልአኩ መሆኑን ያረጋግጣል።

➣ እስጢፋኖስ ለመልአኩ መለኮትነት የሰጠው ምስክርነት በዚህ አያበቃም። ሙሴ በቁጥቋጦው ያየው ነገር አስደንቆት ነገሩን ለማጣራት ቀርቦ ሳለ፥ የጌታ ድምፅ የአባቶቹ አምላክ እርሱ መሆኑን ሲነግረው፥ ለመመልከት እንዳልደፈረ እስጢፋኖስ ይናገራል

“እኔ የአባቶችህ አምላክ፣ የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ አምላክ ነኝ’ ሲል ሰማ። ሙሴም በፍርሀት ተዋጠ፤ #ለመመልከትም #አልደፈረም።”
ሐዋርያት 7፥32 (አዲሱ መ.ት)

ሙሴ ለምንድነው ለመመልከት ያልደፈረው? ለምንስ ነው ማየትን የፈራው? የዚህ ጥያቄ መልስ በዋናው የዘጽአት ታሪክ ላይ የሚገኝ ነው። ሙሴ ለማየት የፈራው፥ የታየው እግዚአብሔር ስለነበር ነው፦

“ቀጥሎም፣ “እኔ የአባቶችህ የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ አምላክ (ኤሎሂም) ነኝ” አለው። በዚህ ጊዜ #ሙሴ #እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) ፊት ለፊት #ማየት ስለ #ፈራ ፊቱን ሸፈነ።”
ዘጸአት 3፥6 (አዲሱ መ.ት)

ሙሴ ለማየት የፈራው፥ የተገለጠለት እግዚአብሔር በመሆኑ ነው። እግዚአብሔር ስለሆነ የታየው፥ እርሱን ፊት ለፊት ለማየት ፈራ። ይህ እጅግ ብዙ የሚያስብል ሀሳብ ነው

ሙሴን እግዚአብሔርን ለማየት ሊፈራ የቻለው፥ እግዚአብሔር ሊታይ በሚችል መንገድ ስለተገለጠለት ነው። በሚታይ አኳሃን ስለተገለጠ፥ እርሱን ማየት ፈራ። ይህ አምላክ ለሙሴ በትክክለኛ ሊታይ በሚችል አገላለጥ እንደተገለጠለት ያሳያል።

ነገር ግን በዘጽ 3 ላይ ለሙሴ የተገለጠለት መልአኩ ነው (ዘጽ 3:2) እርሱ ነው በእሳት አምሳል የታየው። ነገር ግን ሙሴ ለማየት የፈራው እግዚአብሔርን እንደሆነ ቁ.6 ግልፅ ያደርጋል። ይህ በግልፅና በማያሻማ መልአኩ ለሙሴ የተገለጠው እግዚአብሔር መልአኩ መሆኑን ያሳያል። እርሱ ነው ሙሴ ለማየት የፈራው አምላክ። ይህ የእግዚአብሔር መልአክ አምላክ ለመሆኑ የማይቀለበስ ማስረጃ ነው

እስጢፋኖስም ሙሴ ለማየት መፍራቱን መጥቀሱ፥ የእግዚአብሔር መልአክ መለኮት መሆኑን እንደሚያምን ያረጋግጣል። ምክንያቱም እርሱ የጠቀሰው ጥቅስ፥ መልአኩ አምላክ መሆኑን የሚናገር ጥቅስ ነውና

ይህ እንዴት እስጢፋኖስ ያ መልአክ ራሱ ክርስቶስ መሆኑን እንደሰከረ ያሳያል?

እስጢፋኖስ መልአኩ መለኮት መሆኑን መግለጹ፥ ያ መልአክ ራሱ ክርስቶስ እንደሆነ መመስከሩን ያሳያል። ምክንያቱም እስጢፋኖስ ክርስቶስ አምላክ መሆኑን መስክሯልና። የእግዚአብሔር መልአክ አምላክ መሆኑን በመሰከረበት በዚያው አውድ፥ ክርስቶስ አምላክ መሆኑን መመስከሩ፥ ያ የእግዚአብሔር መልአክ ራሱ ክርስቶስ መሆኑን ለመመስከሩ ተጨባጭ ማስረጃ ነው።

እንዴት ነው እስጢፋኖስ ክርስቶስ አምላክ መሆኑን የመሰከረው?

“እስጢፋኖስም እየወገሩት ሳለ፣ “ጌታ #ኢየሱስ ሆይ፤ #ነፍሴን ተቀበላት” ብሎ ጸለየ፤”
ሐዋርያት 7፥59 (አዲሱ መ.ት)

እስጢፋኖስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ጌታ ኢየሱስን በእግዚአብሔር ቀኝ ካየው በኋላ፥ አይሁዳውያን ሲወግሩት እንመለከታለን። እስጢፋኖስም እየወገሩት በነበሩበት በዚህ ሰአት፥ ጌታ ኢየሱስ ነፍሱን እንዲቀበል ወደ እርሱ ይጸልያል

ይህ አምላክ መሆኑን ለመመስከሩ ትልቅ ማስረጃ ነው። በመጀመሪያ፥ እስጢፋኖስ ተወግሮ እየሞተ በነበረበት በዚህ ሰአት የተጣራው ኢየሱስን ነው። ሰዎች በሚሞቱበት ሰአት የሚጣሩት አምላካቸውን ብቻ ነው። እስጢፋኖስ በሞቱ ሰአት ክርስቶስ ነፍሱን እንዲቀበለው መጣራቱ፥ አምላክ ነው ብሎ እንደሚያምን ያረጋግጣል

"እንዲሁም ንጉሡ ኢዮአስ ዮዳሄ ያደረገለትን ቸርነት አላሰበም፥ ልጁንም ዘካርያስን አስገደለው፤ እርሱም #ሲሞት። #እግዚአብሔር ይየው፥ ይፈልገውም አለ።"
(መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 24:22)

እግዚአብሔርን የሚያመልኩ እስራኤላውያን በጭንቅና በመከራ ጊዜያቸው የሚጣሩት አምላካቸው እግዚአብሔርን ነው። በሰማይ ያለውን እርሱን ነው ተጣርተው የሚያስፈልጋቸውን ነገር የሚጠይቁት

"2፤ ጆሮውን ወደ እኔ አዘንብሎአልና በዘመኔ ሁሉ #እጠራዋለሁ። 3፤ #የሞት ጣር ያዘኝ፥ የሲኦልም ሕማም አገኘኝ፤ ጭንቀትንና መከራን አገኘሁ።"
(መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ 116:2-3)

"ልቤ ተስፋ በቈረጠ ጊዜ ከምድር ዳርቻ ወደ #አንተ #እጮኻለሁ፤ በድንጋይ ላይ ከፍ ከፍ አደረግኸኝ።"
(መዝሙረ ዳዊት 61:2)

"በቃሌ ወደ #እግዚአብሔር #እጮሃለሁ ከተቀደሰ ተራራውም ይሰማኛል።"
(መዝሙረ ዳዊት 3:4)

እስጢፋኖስ በሰማይ ወዳለው ወደ ክርስቶስ ነፍሱን እንዲቀበለው መጣራቱ፥ አምላክ መሆኑን እንደሚያምን ያሳያል። ምክንያቱም በሰማይ ያለ የትኛውም ፍጡር በሞት ሰአት አይጠራምና። እግዚአብሔር ብቻ ነው በሰማይ ሆኖ በመከራና ሰአት የሚጠራው

ይህ ክርስቶስ ራሱ ያስተማረው ትምህርት ነው። ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ በስሙ የሚለምኑትን ነገር እርሱ ራሱ እንደሚያደርገው ለደቀመዛሙርቱ በመናገር፥ ሰዎች እርሱን እንዲጣሩና ቀጥታ ወደ እርሱ እንዲፀልዩ አስተምሯል፦

"13፤ እኔ ወደ አብ #እሄዳለሁና፤ አብም ስለ ወልድ እንዲከበር በስሜ የምትለምኑትን #ሁሉ #አደርገዋለሁ። 14፤ ማናቸውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ #እኔ #አደርገዋለሁ።"
(የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 14:13-14)

ክርስቶስ ወደ አብ ከሄደ በኋላ የሚሆነውን ነገር እየተናገረ ነው። ወደ አባቱ ከሄደ በኋላ፥ ሰዎች በስሙ የሚለምኑትን እንደሚያደርግ እየተናገረ ነው። ማለትም፥ በሰማይ ሆኖ ሰዎች የሚለምንላቸውን ይፈፍምላቸዋል ማለት ነው። ይህ አምላክ ለመሆኑ በራሱ የተሰጠ ምስክርነት ነው።

እስጢፋኖስም ይህን የጌታን ትዕዛዝ በመከተል፥ በአባቱ ቀኝ ያለውን ኢየሱስን ነፍሱን እንዲቀበለው በመጸለይ፥ ወደ እርሱ ጸልይዋል። የትኛውም ፍጡር በሰማይ ሆኖ ጸሎትን ስለማይመልስ፥ እስጢፋኖስ ወደ ጌታ ክርስቶስ መጸለዩ፥ እርሱ አምላክ መሆኑን እንደመሰከረ ያረጋግጣል

ሌላው እጅግ አስፈላጊና ዋና ነጥብ፥ እስጢፋኖስ ክርስቶስን የጠየቀው ነገር ነው። ነፍሱን እንዲቀበለው ጠይቆታል። በመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ፥ በሰማይ ሆኖ የሰዎችን ነፍስ የሚቀበለው እግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ እንረዳለን፦

"አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ፥ #ነፍስም ወደ ሰጠው ወደ #እግዚአብሔር #ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ።"
(መጽሐፈ መክብብ 12:7)

" #በእጅህ #ነፍሴን #እሰጣለሁ፤ የእውነት አምላክ አቤቱ፥ ተቤዥተኸኛል።"
(መዝሙረ ዳዊት 31:5)

"ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኾ። አባት ሆይ፥ #ነፍሴን #በእጅህ #አደራ #እሰጣለሁ አለ። ይህንም ብሎ ነፍሱን ሰጠ።"
(የሉቃስ ወንጌል 23:46)

የትኛውም ፍጡር የሰውን ነፍስ ሊቀበል አይችልም። አይደለም በሰማይ ሆኖ፥ በየትኛውም ስፍራ ፍጡር ይህ ስልጣን የለውም። እስጢፋኖስ፥ ክርስቶስ ነፍሱን እንዲቀበል መጸለዩ፥ አምላክ መሆኑን እንደሚያምን ያረጋግጣል።

እስጢፋኖስ፥ ክርስቶስ ነፍሱን እንዲቀበለው በመጠየቅ ብቻ አላበቃም። ክርስቶስ ኃጢአታቸውንም እንዳይቆጥርባቸው ይለምነዋል

“ከዚያም ተንበርክኮ፤ በታላቅ ድምፅ፣ “#ጌታ ሆይ! ይህን #ኀጢአት #አትቍጠርባቸው” ብሎ ጮኸ፤ ይህን ካለ በኋላም አንቀላፋ።”
ሐዋርያት 7፥60 (አዲሱ መ.ት)
308 viewsedited  15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 18:03:40 የሐዋርያት ሥራና የእግዚአብሔር መልአክ (ክፍል 2)

ባለፈው ክፍል የክርስቶስን አምላክነትና አስተምህሮተ ሥላሴን የሚቃወሙ ወገኖች፥ በሐዋርያት ሥራ 7 ላይ ተንተርሰው ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ይገለጥ የነበረው መለኮታዊው የእግዚአብሔር መልአክ አለመሆኑን ለማሳየት የሚያነሷቸውን ተቃውሞዎች መመለስ ጀምረን ነበር።

የክፍሉን አውድና የሰማዕቱን የእስጢፋኖስን የንግግር አላማ ካየን በኋላ፥ የመጀመሪያውን ተቃውሞ (objection) ለመመለስ ሞክረናል። እርሱም "መልአክ" ወይንም በግሪክ "ἄγγελος/አንጌሎስ" የሚለው ቃል መልእክተኛ ማለት ሲሆን፥ የተላከ ማለት ብቻ እንደሆነና አንድ አካል በዚህ ስያሜ ስለተጠራ ብቻ ፍጡር መንፈስ እንዳልሆነ አይተናል። ቃሉ አሰራርን እንጂ ባህርይን የሚገልጽ ቃል ስላልሆነ፥ ለየትኛውም አይነት አካል ጥቅም ላይ ሊውል ይችላል። የተላከ መሆኑን ብቻ እንደሚያመለክት ተመልክተናል

በተጨማሪም ለምን እስጢፋኖስ ቃል በቃል "መልአኩ ክርስቶስ ነው" እንዳላለም ለማየት ሞክረናል።

ዛሬም እግዚአብሔር ቢፈቅድ፥ እንዴት እስጢፋኖስ ያ ለሙሴ የተገለጠለው መልአክ ክርስቶስ መሆኑን እንደመሰከረ ለመመልከት እንሞክራለን

እስጢፋኖስ በፊቱ ለነበሩት ካህናት ከአብርሃም አንስቶ እግዚአብሔር ለእስራኤል ሕዝብ ያደረገውን ነገር ከተናገረ በኋላ፥ ከሐዋ 7:20 አንስቶ ስለ ሙሴ ታሪክ መናገር ይጀምራል። ከተወለደ በኋላ የፈርዖን ልጅ እንዳነሳችው፥ የግብፆችን ጥበብ እንደተማረ፥ ነገር ግን ግብጻዊውን በመግደሉ ወደ ምድያም ምጻተኛ ሆኖ ለመኖር እንደሸሸ ተረከላቸው

ከዚያም፥ አርባ አመት ሲሞላው በሲና ተራራ በምድረ በዳ በቁጥቋጦው ውስጥ በእሳት ነበልባል መልአክ እንደተገለጠለት በቁ.30 ላይ ነገራቸው።

አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ሐዋ 7:30 ሲተረጉሙት "የጌታ መልአክ ታየው" ቢሉም፥ ግሪኩ ግን "መልአክ ታየው" ነው የሚለው።

"Καὶ πληρωθέντων ἐτῶν τεσσεράκοντα ὤφθη αὐτῷ ἐν τῇ ἐρήμῳ τοῦ ὄρους Σινᾶ #ἄγγελος ἐν φλογὶ πυρὸς βάτου"

[Acts 7:30 Greek]

አዲሱ መደበኛ ትርጉምና ሌሎች ኢንግሊዘኛ ትርጉሞችም ከግሪኩ ጋር በሚስማማ መልኩ "መልአክ ታየው" ወይንም "an angel appeared to him" በማለት በትክክል ተርጉመውታል፦

“ከአርባ ዓመት በኋላ፣ በሲና ተራራ አካባቢ ባለው ምድረ በዳ፣ በሚነድ ቍጥቋጦ ነበልባል ውስጥ #መልአክ #ተገለጠለት።”
ሐዋርያት 7፥30 (አዲሱ መ.ት)

“After forty years had passed, an #angel #appeared to Moses in the flames of a burning bush in the desert near Mount Sinai.”
Acts 7:30 (NIV)

“And when forty years had gone by, there #appeared to him in the wilderness (desert) of Mount Sinai an #angel, in the flame of a burning bramblebush.”
Acts 7:30 (AMP)

“After 40 years had passed, an #angel #appeared to him in the desert of Mount Sinai, in the flame of a burning bush.”
Acts 7:30 (HCSB)

“When forty years had passed, an #angel #appeared to him in the flames of a burning bush in the desert near Mount Sinai.”
Acts 7:30 (ISVN)

እስጢፋኖስ የተናገረው ታሪክ በዘጽ 3:1-2 ተረጋግጦ ይገኛል። ዘጽ 3:1-2 እንደሚለው ሙሴ በእግዚአብሔር ተራራ በኮሬብ የአማቱን የዮቶርን በጎች ሲጠብቅ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለት። ኮሬብ የሲና ሌላ ስም ሲሆን፥ በዘጽ 19-24 እግዚአብሔር በእሳት የወረደበት ተራራ ነው። በዚያው ተራራ ነው የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ነበልባል ለሙሴ የተገለጠለት። ለዚህ ነው እስጢፋኖስ ኮሬብንና ሲናን በተቀያያሪነት የተጠቀመው። የአንዱ ተራራ ስሞች ናቸውና

ይህን ከተናገረ በኋላ፥ ሙሴ ባየው ነገር ተደንቆ ነገሩን ለማጣት ሲቀርብ፥ የጌታን ድምፅ እንደሰማ ይናገራል

ሐዋርያት 7 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³¹ ሙሴም ባየው ነገር #ተደነቀ፤ ነገሩን ለማጣራት ወደዚያ ሲቀርብ #የጌታ_ድምፅ፤ ³² እኔ የአባቶችህ አምላክ፣ የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ አምላክ ነኝ’ #ሲል_ሰማ። ሙሴም በፍርሀት ተዋጠ፤ ለመመልከትም አልደፈረም።

ይህ ማለት ሙሴ የሰማው፥ ያነጋገረው ጌታን ነው ማለት ነው። በቁጥቋጦው ውስጥ ሆኖ ሙሴን ያነጋገረው ጌታ ነው ማለት ነው። ነገር ግን የተገለጠለት መልአኩ ነበር

ሙሴን በዚህ ስፍራ ያነጋገረው ጌታ መሆኑ፥ በቀጣዩ ጥቅስም ተረጋግጧል፦

“ #ጌታም እንዲህ #አለው፤ ‘የእግርህን ጫማ አውልቅ፤ የቆምህባት ስፍራ የተቀደሰች ምድር ናትና።”
ሐዋርያት 7፥33 (አዲሱ መ.ት)

ሙሴን ጫማውን እንዲያወልቅ ያዘዘው ጌታ እንደሆነ በቁ.33 ላይ በግልፅ እስጢፋኖስ ተናግሯል። ይህ ማለት ሙሴ በሲና ተራራ ላይ ሲነጋገር የነበረው ከእግዚአብሔር ጋር ነበር ማለት ነው። በቁ.32 ላይ የአባቶቹ አምላክ መሆኑን የነገረው ጌታ ነው በቁ.33 ላይ ጫማውን እንዲያወልቅ ያዘዘው። ይህ ሙሴ ከአምላክ ጋር ሲነጋገር እንደነበር የሚያረጋግጥ ነው

ነገር ግን ለሙሴ የተገለጠው መልአኩ ነበር!

በቁጥቋጦው በእሳት ነበልባል ለሙሴ የተገለጠው መልአኩ ነበር። ይህ ማለት ሙሴን ሲያነጋግረው የነበረው ጌታ መልአኩ ነበር ማለት ነው። የተገለጠለትና የታየው እርሱ በመሆኑ፥ አነጋገረው የተባለውም ጌታ እርሱ ነው። ይህ እስጢፋኖስ መልአኩ አምላክ እንደሆነ ለማመኑ ማስረጃ ነው።

እስጢፋኖስ፥ ሙሴን በሲና ተራራ ያነጋገረው መልአኩ መሆኑን በማያሻማ መልኩ እንዲህ ግልፅ አድርጎታል፦

“እርሱም #በሲና_ተራራ_ከተናገረው_መልአክና ከአባቶቻችን ጋር በምድረ በዳ በሕዝቡ ጉባኤ መካከል ነበር፤ የሕይወትንም ቃል ወደ እኛ ለማስተላለፍ ተቀበለ።”
ሐዋርያት 7፥38 (አዲሱ መ.ት)

በቁ.37 ግልፅ እንዳደረገው፥ ሙሴን በሲና ተራራ የተናገረው መልአኩ ነበር። በቁ.33 ግን ጫማህን አውልቅ ብሎ የተናገረው ጌታ መሆኑን ግልጽ አድርጓል። በቁ.32ም እንዲሁ ወደ ሙሴ የመጣው ድምፅ የጌታ ድምፅ መሆኑን ተናግሯል። ነገር ግን በቁ.37 ሙሴን ያነጋገረው መልአኩ ነው አለ

ይህ ሙሴን በሲና ተራራ ያነጋገረው ጌታ፥ መልአኩ መሆኑን በማያሻማ መልኩ ያረጋግጣል። ሙሴን ያነጋገረው አምላክ በቁጥቋጦው የተገለጠለት መልአክ ነው።

ለዚህም ነው በቁ.30 ላይ "የጌታ መልአክ" በማለት ፈንታ "መልአክ" ተገለጠለት ያለው። ቀጥሎ ሙሴን ያነጋገረው ጌታ መልአኩ ነውና። ሙሴን ያነጋገረው ጌታ መልአኩ መሆኑን ለመግለጽ "መልአክ" አለ። ይህ እስጢፋኖስ፥ መልአኩ መለኮት መሆኑን እንደሚያምን ያሳያል

እስጢፋኖስ ስለ መልአኩ የተናገረው ነገር፥ በዋናው የዘጽአት ታሪክ ላይ ተረጋግጦ እናገኘዋለን። ለሙሴ የተገለጠው/የታየው፥ በቁጥቋጦው ውስጥም የነበረው፥ መልአኩ ነበር

“እዚያም የእግዚአብሔር (ያህዌ) #መልአክ በቍጥቋጦው ውስጥ በሚንቀለቀል የእሳት ነበልባል መካከል #ተገለጠለት። ሙሴም ቍጥቋጦው በእሳት ቢያያዝም እንኳ፣ አለ መቃጠሉን አየ።”
ዘጸአት 3፥2 (አዲሱ መ.ት)

ነገር ግን ቁጥቋጦው ውስጥ ሆኖ፥ ጠርቶት ያነጋገረው እግዚአብሔር ነበር
316 views15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-08 19:32:04 ስለዚህ ቃል በቃል "ኢየሱስ ነው" ያላለበት ምክንያት ይህ ነው።

ነገር ግን የሐዋርያት ሥራ 7ን አውድ በጥንቃቄ ስናጠና፥ እስጢፋኖስ ክርስቶስ ያ ለሙሴ የተገለጠው የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን እንደመሰከረ እንረዳለን። ቀጥታ "ያ መልአክ ኢየሱስ ነው" ባይልም እንኳ፥ እርሱ መሆኑን በማያሻማ መንገድ መስክሯል። ማስረጃው እነሆ፦

ለዚህ እውነት የመጀመሪያው ማሳያ፥ በግሪክ ቋንቋ (ፅርዕ) መልአክ የሚለው ቃል መልእክተኛ መሆኑ ነው። ከላይ እንደተነጋገርነው "መልአክ" የሚለው ቃል በዕብራይስጥ መልእክተኛ ማለት ነው። አሰራርን እንጂ ባህርይን የሚያመለክት ቃል አይደለም። የተላከ ማንኛውም አካል መልእክተኛ ተብሎ ይጠራል። ተላኪው ምን አይነት ባህርይ እንዳለው የሚታወቀው በአውዱ ነው።

ልክ እንደ ዕብራይስጡ፥ በግሪክም መልአክ የሚለው ቃል መልእክተኛ ማለት ነው። ቃሉ "ἄγγελος/አንጌሎስ" ሲሆን መልእክተኛ ማለት ነው። የተላከ ማንኛውም አካል የሚጠራበት የአሰራር ስያሜ ነው። መልአክ ከተባለ መልእክተኛ እንደሆነ እንረዳለን እንጂ፥ ምን አይነት ባህርይ እንዳለው አናውቅም። ምን አይነት ባህርይ እንዳለው የሚታወቀው በአውዱ ነው። ቃሉ ለሰዎች፥ ለፍጡራን መናፍስት ደግሞም ለመለኮት ጥቅም ላይ ውሏል።

ለምሳሌ፦

"እንደዚሁም ጋለሞታይቱ ረዓብ ደግሞ #መልእክተኞቹን ተቀብላ በሌላ መንገድ በሰደደቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቀችምን?"
(የያዕቆብ መልእክት 2:25)

በዚህ ሥፍራ ሐዋርያው ያዕቆብ በኢያሱ 2 ላይ ያለውን ታሪክ ሲጠቅስ እንመለከታለን። ኢያሱ የላካቸውን መልእክተኞች ተቀብላ በሌላ መንገድ በሰደደቻቸው ጊዜ በስራ እንደጸደቀች ይናገራል። በዚህ ስፍራ "መልእክተኞች" ተብሎ የተተረጎመው ቃል "አንጌሎን/መላእክት" የሚለው ቃል ነው። በሐዋ 7:30 ላይ ጥቅም ላይ የዋለው ቃል ነው። በቀጥታ ሲተረጎም "..መላእክቱን በተቀበለች ጊዜ" ነው የሚለው። በኢያሱ የተላኩት ግን ሰዎች ነበሩ (ኢያ 2:4) ይህ መልአክ የሚለው ቃል በግሪክም አሰራርን እንጂ ባህርይን እንደማያመለክት ግልፅ ያደርጋል።

ሌላ ምሳሌ፦

"19፤ #ዮሐንስም ከደቀ መዛሙርቱ ሁለት ወደ እርሱ ጠርቶ። የሚመጣው አንተ ነህን ወይስ ሌላውን እንጠብቅ? ብሎ ወደ ኢየሱስ #ላከ። 20፤ #ሰዎቹም ወደ እርሱ መጥተው። መጥምቁ ዮሐንስ። የሚመጣው አንተ ነህን ወይስ ሌላውን እንጠብቅ? ብሎ ወደ አንተ ላከን አሉት። ...24፤ #የዮሐንስ_መልክተኞችም ከሄዱ በኋላ፥ ለሕዝቡ ስለ ዮሐንስ ይናገር ጀመር እንዲህም አለ። ምን ልታዩ ወደ ምድረ በዳ ወጣችሁ? ነፋስ የሚወዘውዘውን ሸምበቆን? ወይስ ምን ልታዩ ወጣችሁ?"
(የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 7:19-24)

በዚሁ ስፍራም መጥምቁ ዮሐንስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትክክለኛው መሢሕ መሆኑን ለማረጋገጥ ሰዎችን ወደ እርሱ ሲልክ እንመለከታለን። ሰዎቹ በዮሐንስ ተልከው ወደ ክርስቶስ መጥተዋል። ከዚያም ጌታ እውነተኛው መሲህ እርሱ መሆኑን ከነገራቸው በኋላ፥ እንደሄዱ እናነባለን

በቁ.24 ላይ "መልእክተኞች" ተብሎ የተተረጎመው ቃል በሐዋ 7:3ዐ ላይ ያለው ራሱ ቃል ነው። ሉቃ 7:24 በቀጥታ ሲተረጎም "የዮሐንስ መላእክት..." ነው የሚለው። ነገር ግን ወደ ክርስቶስ የተላኩት ሰዎች ነበሩ (ቁ.20) ነገር ግን መላእክት ተብለው ተጠርተዋል። መላእክት የተባሉትም በዮሐንስ ስለተላኩ ነው (ቁ.19) ይህ በግሪክም መልአክ የሚለው ቃል፥ አሰራርን እንጂ ባህርይን እንደማያመለክት ያሳያል።

ሌላ ምሳሌ፦

"በፊቱም #መልክተኞችን ሰደደ። ሄደውም ሊያሰናዱለት ወደ አንድ ወደ ሳምራውያን መንደር ገቡ፤"
(የሉቃስ ወንጌል 9:52)

በዚህ ቦታም እንዲሁ ክርስቶስ በፊቱ መልእክተኞችን ወደ አንድ ሳምራውያን መንደር ሲልክ እንመለከታለን። "መልእክተኞች" የሚለው ቃል፥ በሐዋ 7:30 ላይ ጥቅም ላይ የዋለው ቃል ነው። ቃሉ በቀጥታ የተረጎም "በፊቱም መላእክትን ላከ" ነው የሚለው። የተላኩት ሰዎች ሆነው ሳለ፥ መላእክት ተብለው መጠራታቸው "አንጌሎስ/መልአክ" የሚለው የግሪክ ቃል አሰራርን እንጂ ባህርይን እንደማያመለክት ማረጋገጫ ነው።

ነገሩን በይበልጥ አስገራሚ የሚያደርገው፥ እነኚህ ምሳሌዎች ያሉበት የሉቃስ ወንጌልና የሐዋርያት ስራ በአንድ ጸሐፊ መጻፋቸው ነው። እንደሚታወቀው፥ የሉቃስና የሐዋርያት ስራ ጸሐፊ ሐኪሙ ሉቃስ ነው (ሐዋ 1:1-2 ሉቃ 1:1-4) ይህ ጸሐፊው፥ መልአክ የሚለውን ቃል እንዴት ይጠቀመው እንደነበር ግልፅ ያደርጋል። ለሉቃስ "መልአክ" የሚለው ቃል አሰራርን እንጂ ባህርይን አያመለክትም። መለኮትም፥ ሰዎችም፥ ፍጡራን መናፍስትም የሚጠሩበት የአሰራር ስያሜ ነው።

ሉቃስ ለፍጡራን መናፍስትም እንዲሁ ቃሉን በብዛት ሲጠቀመው እንመለከታለን፦ (ሐዋ 7:52-53 ሐዋ 12:15 ሉቃ 2:15 ሉቃ 1:30)

ስለዚህ ሐዋ 7:30 ላይ መልአክ ብሎ ስለጠራው ብቻ ፍጡር ነው ማለት አይደለም። የመልአኩ/መልእክተኛው ባህርይ የሚታወቀው በአውዱ ነውና። አውዱ እንደ መለኮት ይገልጸዋል ወይ፥ የሚለውን ጥያቄ መመለስ ይኖርብናል

በቀጣዩ ክፍል እንዴት እስጢፋኖስ የእግዚአብሔርን መልአክ ክርስቶስ መሆኑን እንደገለጸ ከራሱ ከሐዋርያት ሥራ 7 እየጠቀስን ለመመልከት እንሞክራለን።

ይቀጥላል
377 viewsedited  16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-08 19:32:03 የሐዋርያት ሥራ እና የእግዚአብሔር መልአክ (ክፍል 1)

ከዚህ በፊት፥ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር መልአክ ተብሎ ይጠራ እንደነበር በተደጋጋሚ ለማየት ሞክረናል። መልአክ የሚለው ቃል መልእክተኛ ማለት ሲሆን አሰራርን እንጂ ባህርይን የሚያመለክት ቃል አይደለም። የተላከ ማንኛውም አካል መልአክ ተብሎ ይጠራል

ቃሉ ለመለኮት (ዘጽ 23:21 ዘፍ 31:10-13) ለሰዎች (ሚል 2:7 ሐጌ 1:13) እንዲሁም ለፍጡራን መናፍስት (ዘፍ 32:1 ዘፍ 28:12) ጥቅም ላይ ውሏል። መልአክ ተብሎ የተጠራው አካል፥ ምን አይነት ባህርይ እንዳለው የምናውቀው በዙሪያው ባለው አውድ ነው። እንጂ መልአክ ተብሎ ስለተጠራ ብቻ የሆነ ባህርይ አለው ማለት አይደለም

ይህ የእግዚአብሔር መልአክ ግን በባህርይው/ስሙ መለኮት ነው (ዘጽ 23:21) አምላክ ነው (ዘጽ 24:11) እግዚአብሔር ነው (ዘጽ 24:1 ዘካ 3:2) እግዚአብሔር ብቻ የሚያደርጋቸውን ነገሮች ያደርጋል (ዘካ 3:3-4 ዘፍ 16:10) ተመልኳል (ዘጽ 3:2-6 ኢያ 5:14-15 መሳ 6:21) እግዚአብሔርም አምላክ መሆኑን መስክሯል (ዘፍ 35:1)

ነገር ግን ብዙ ክርስቲያን ያልሆኑ ወገኖች ይህን አስተምህሮ ይቃወማሉ። ትምህርተ ሥላሴን ወይንም የክርስቶስን አምላክነት ለመቃወም ከሚጠቀሟቸው ስልቶች መካከል አንዱ፥ የተለያዩ ጥያቄዎችንና ተቃውሞዎችን በማንሳት ይህን ጥንታዊና መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ ለመቀልበስ መሞከር ነው።

ጌታ ቢፈቅድ፥ ዛሬ በዚህ ጉዳይ ላይ የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች ለመመለስ እንሞክራለን። በተጨማሪም፥ እንዴት ጌታ ኢየሱስ ያ መለኮታዊው የእግዚአብሔር መልአክ (The Divine Angel) እንደሆነ ለማየት እንሞክራለን

እነዚህ ወገኖች የመጀመሪያ ተቃውሟቸውን የሚያነሱት የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 7 ላይ ተመስርተው ነው፦

“ከአርባ ዓመት በኋላ፣ በሲና ተራራ አካባቢ ባለው ምድረ በዳ፣ በሚነድ ቍጥቋጦ ነበልባል ውስጥ #መልአክ ተገለጠለት።”
ሐዋርያት 7፥30 (አዲሱ መ.ት)

➣ የሐዋርያት ሥራ 7 የመጀመሪያው የቤተክርስቲያን ሰማዕት እስጢፋኖስ በአይሁድ ፊት ቀርቦ፥ ስለ ክርስቶስ መስክሮ በስተመጨረሻም ለጌታ ኢየሱስ ክብር ሕይወቱን የሰጠበት ታሪክ የተዘገበበት ክፍል ነው።

የሚናገርበትን ጥበብና መንፈስ መቋቋም ያልቻሉት አይሁድ፥ ኦሪትንና ሙሴን እግዚአብሔርንም ሲሳደብ ሰምተነዋል በማለት በሀሰት ከሰሱት (ሐዋ 6:10-15) ወደ ሸንጎ ከቀረበ በኋላ፥ እግዚአብሔር ለአባታቸው ለአብርሃም ካደረገው ነገር አንስቶ እስከ መሲሑ እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ መምጣት ድረስ ያለውን ወንጌል ሰበከላቸው። በስተመጨረሻም፥ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ፥ ጌታ ክርስቶስን በአባቱ ቀኝ እንዳየ ሲነግራቸው በድንጋይ ወግረው ገደሉት።

እነዚህ ወገኖች፥ የእስጢፋኖስ ስብከት፥ ክርስቶስ የእግዚአብሔር መልአክ አለመሆኑን ያሳያል ይላሉ።

ሀሳባቸው በአጭሩ ሲቀመጥ ይህን ይመስላል፦ "በዚህ ስፍራ እስጢፋኖስ በዘጽ 3 ላይ የሚገኘውን ታሪክ መልሶ ሲተርክ እንመለከታለን። ሙሴ እንዴት የእግዚአብሔርን መልአክ በበርሃ እንደተገናኘውና እንደተናገረው በፊቱ ለነበሩት አይሁድ ነግሯቸዋል

ነገር ግን መልአኩ ኢየሱስ ነው አላለም። እስጢፋኖስ በክርስቶስ የሚያምን ክርስቲያን ነበር። ነገር ግን በቁጥቋጦው ለሙሴ የተገለጠው መልአክ ክርስቶስ ነው አላለም። እንደውም ለያይቷቸዋል። ስለዚህ፥ ክርስቶስ ያ የእግዚአብሔር መልአክ አይደለም።"

ይህ አውዱን ያልጠበቀ መረዳት ከመሆኑም ባሻገር፥ መሠረታዊ የሆነ የመጽሐፍ ቅዱስ አፈታት እውቀት የጎደለው አረዳድ ነው።

በመጀመሪያ ደረጃ፥ የሐዋርያት ሥራ 7 አውድ ምንድነው የሚለውን ሀሳብ በአግባቡ መረዳት አለብን። ሐዋ 6:9 እንደሚናገረው፥ የነጻ ወጪዎች ሙክራብ ከተባለችው ሙክራብ የመጡ አይሁድ እስጢፋኖስን ይከራከሩት ነበር። ነገር ግን ይናገርበት የነበረውን ጥበብና መንፈስ መቋቋም ስላቃታቸው፥ በሀሰት ከሰሱት።

ወደ ሸንጎ ከቀረበ በኋላም፥ ሊቀካህናቱ ይህ ነገር እንዲህ ነውን? በማለት ይጠይቁታል (ሐዋ 7:1) ማለትም፥ እውንም የተከሰስክበትን ነገር ፈጽመሃል ወይ ነው። ስለዚህ እስጢፋኖስ ኦሪትን እየጠቀሰ ከአብርሃም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ መምጣት ድረስ እግዚአብሔር ለእስራኤል ያደረገውን ነገር በመተረክ፥ አይሁድ በሀሰት የከሰሱትን ክስ አለመፈጸሙን በተግባር አሳየ

አስተውሉ! አይሁድ፥ እስጢፋኖስ እግዚአብሔርን፥ ቅዱሱን ሕግ (ኦሪትን) እና ሙሴን ተሳድቧል በማለት ነበር የከሰሱት። ነገር ግን እስጢፋኖስ እግዚአብሔር እውነተኛው አምላክ መሆኑን፥ ኦሪትን እንደ ትክክለኛ የእግዚአብሔር ቃል በመጥቀስ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን፥ ሙሴም የእግዚአብሔር ሰው እንደነበር በመናገር ክሳቸውን በተግባር አስተባበለ

ለአብርሃም የተገለጠው እግዚአብሔር የክብር አምላክ መሆኑን (ሐዋ 7:2) ሙሴም እግዚአብሔር ያስነሳው ነቢይ መሆኑን (ሐዋ 7:37) እርሱም የተቀበለው ኦሪት የሕይወት ቃል መሆኑን (ሐዋ 7:38) ተናግሯል። ይህ እግዚአብሔርንና ሙሴን ኦሪትንም የሚሳደብ ሰው የሚሰጠው ምስክርነት አይደለም። ስለዚህ ክሳቸው ሀሰት መሆኑን በተግባር አሳየ

እነርሱ ያሉት እውነት ቢሆን ኖሮ፥ እግዚአብሔር እውነተኛ አምላክ መሆኑን፥ ኦሪትም የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን ሙሴም እግዚአብሔር የተገለጠለት የእግዚአብሔር ሰው መሆኑን ባልመሰከረ ነበር። ከአብርሃም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ ኢየሱስ መምጣት ድረስ ያለውን ታሪክ መተረኩ፥ አንዱ ምክንያት የነርሱ ክስ ሀሰት መሆኑን ለማሳየት ነው።

ሲቀጥል ደግሞ፥ እግዚአብሔር ለእስራኤል ሕዝብ ከአብርሃም ጀምሮ ያደረገውን ነገር በመናገር እንዴት የክርስቶስ ወንጌል ከዛን ጊዜ ጀምሮ እንደተተረከ ለማሳየት ነው። መጻሕፍት ሁሉ የሚናገሩት ስለ ጌታ ኢየሱስ ነውና (ሉቃ 24:54)

ስለዚህ የመላ ንግግሩ አላማ "የእግዚአብሔር መልአክ ማነው?" የሚል አልነበረም። የመልአኩን ማንነት ማሳወቅ ወይንም መግለጥ የንግግሩ አለማ አልነበረም።

ከአብርሃም ጀምሮ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያደረገለትን ነገር ለማሳየት ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን እየጠቀሰ ነበር። ድንገት በንግግሩ መሃል "ይህም መልአክ ኢየሱስ ነበር" ቢል ትርጉም ይሰጣል??? ፈጽሞ የማይመስል ነገር ይሆን ነበር። ሰሚዎቹ የነበሩት በክርስቶስ የማያምኑ አይሁድም "ከዘጽ 3:2 ኢየሱስ የሚል ቃል አሳየን" ማለታቸው አይቀርም ነበር። ምከንያቱም የንግግሩ አላማ ከአብርሃም ጀምሮ እግዚአብሔር ለሕዝበ እስራኤል ያደረገውን ነገር መናገር ነበርና። ስለዚህ ድንገት አቋርጦ "ያ መልአክ ኢየሱስ ነበር" ማለት ትርጉም አይሰጥም

እስጢፋኖስ በፊቱ ለነበሩት አይሁድ ሲያስረዳቸው ከመጽሐፍ ቅዱስ እየጠቀሰ ነበር። ጥቅስ ሲጠቀስ ደግሞ እንደተጻፈው ነው። ስለዚህ "የእግዚአብሔር መልአክ" በሚልበት ቦታ ላይ፥ የእግዚአብሔር መልአክ ብሎ ነው ሊያነበው የሚችለው። እንጂ ቃል በቃል ኢየሱስ የሚለው ስም ሳይጻፍ፥ ኢየሱስ ሊል አይችልም። ይህ በmisquatation ያስከስሰው ነበር። ልክ በዚህ ዘመን ያለን ክርስቲያኖች፥ ብሉይ ኪዳንን እንደተጻፈው እንደምንጠቅሰው ነው እስጢፋኖስም የጠቀሰው። እኛ "የእግዚአብሔር መልአክ" የሚልበትን ቦታ ስንጠቅስ፥ ኢየሱስ ብለን እንደማናነበው ሁሉ፥ እስጢፋኖስም እንደተጻፈው ያነበዋል እንጂ፥ ኢየሱስ የሚለው ቃል ሳይኖር ኢየሱስ ብሎ አያነበውም። በተለይ በክርስቶስ ላላመኑ አይሁድ ያልተጻፈውን ማንበብ ተገቢ አይሆንም ነበር
358 viewsedited  16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 00:07:56 <<አስተምህሮተ ስላሴ አሕዳዊ ወይስ መድብላዊ?>>

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
✟አሐዱ አምላክ✟

“እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር #አንድ_እግዚአብሔር ነው፤”
— ዘዳግም 6፥4
ሞኖቴይዝም(monotheism) የሚለው ግሪክ(ጽርዕ) ቃል ከሁለት ቃላት የተዋቀረ ሲሆን ሞኖስ(μόνος) ማለት አንድ ወይም ብቸኛ ማለት ሲሆን ቴዎስ(θεός) ማለት ደግሞ አምላክ ማለት ነው። በአጠቃላይ በስነመለኮት አንጻር አሐዳዊ አስተምህሮት የሚያንጸባርቅ አመለካከት (Ideology) ሞኖቴይዝም (monotheism) ይባላል። ከዚህ በተቃራኒው ደግሞ የመድብለ አማልክት አራማጆች ፖሊቴይዝም (Polytheism) ይባላሉ። ፖሉ(πολύ) ወይም ፖሊ ማለት ብዙ ማለት ነው። ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በፖሊቴይዝም (Polytheism) ረገድ የሚታወቁ አገራት መካከል ሮማውያንና ግሪካውያን ግምባር ቀደም ነበሩ። ግሪካውያን ለብዙ ነገር አምላክ አላቸው። ለፍቅር፣ ለሰላም፣ ለቀን፣ ለጦር፣ ለወቅቶች፣ ለእድል........ወዘተ ለእያንዳዱ ተግባር አማልክት ነበሯቸው። ከሁሉም በላይ ደግሞ በጣም የሚገርመው የሚያመልኩት ነገር ከመብዛቱ የተነሳ <<ለማይታወቅ አምላክ>> በግሪኩ <<አግኖስቶ ቴዎ(Ἀγνώστῳ θεῷ)>> ብለው መስዋዕትን ያቀርባሉ[ሐዋ 17:23]። በሐዋርያት ስራ ም.17 ቁ.16-34 ላይ ያለውን ክፍል ስንመለከት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የግሪክ መዲና በሆነችው በአቴና ሲዘዋወር ያገኘው ነገር ከተማውን የሞሉት የሚታወቁና የማይታወቁ የአማልክት መሰዊያዎችን ነበር። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በቁጥር 24 ላይ አንድ ወሳኝ ንግግርን በአርዮስፋጎስ አደባባይ ላይ ቆሞ ስለ ክርስትና አስተምህሮ ሰበከ።

“ዓለሙንና በእርሱ ያለውን ሁሉ የፈጠረ #አምላክ #እርሱ የሰማይና የምድር ጌታ ነውና እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም፤”
— ሐዋርያት 17፥24
"ὁ #θεὸς ὁ ποιήσας τὸν κόσμον καὶ πάντα τὰ ἐν αὐτῷ, #οὗτος οὐρανοῦ καὶ γῆς ὑπάρχων #κύριος οὐκ ἐν χειροποιήτοις ναοῖς κατοικεῖ." (Πραξεις Αποστολων 17:24)

በክፍሉ ላይ እርሱ ወይም ሆውቶስ/οὗτος የሚለው በባለቤትነት ሙያ(Nominative case) የመጣው ነጠላ መደብ ተውላጠ ስም እየገለጸ ያለው አምላክ(ቴዎስ/θεὸς) እና ጌታ(ኩርዮስ/κύριος) የሚለውን ስም ነው። ይሄ ደግሞ በክርስትና አስተምህሮት ውስጥ ነጠላ ምንነት ያለው አሐዳዊ አምላክ ወይም ጌታ እንዳለ ያሳያል። እግዚአብሔር አምላክ በምንነት ደረጃ(በስልጣን፣ አገዛዝ፣ በባህሪይ፣ በመፍጠር) አንድ ወይም ነጠላ አምላክ እንደሆነ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በአርዮስፋጎስ አደባባይ ለአቴና ሰዎች አጥብቆ ሲናገር እናስተውላለን። ይሄ ንግግር ደግሞ አስተምህሮተ ክርስትና(ስላሴያውያን) አሕዳዊ የመለኮት አስተምህሮ(Monotheism) እንዳላቸው የሚያረጋግጥ ነው። በሚገርም ሁኔታ ደግሞ በንጽጽር መልኩ የአቴና ሰዎች መድብላዊ አማልክት (Polytheism) አምላኪዎች እንደሆኑ በቁጥር 23 ላይ ገልጾልን እንመለከታለን፦

“ #የምታመልኩትን እየተመለከትሁ ሳልፍ፦ ለማይታወቅ አምላክ የሚል ጽሕፈት ያለበትን መሠዊያ ደግሞ አግኝቼአለሁና፦ እንግዲህ ይህን ሳታውቁ የምታመልኩትን እኔ እነግራችኋለሁ።”
— ሐዋርያት 17፥23
"διερχόμενος γὰρ καὶ ἀναθεωρῶν τὰ σεβάσματα ὑμῶν εὗρον καὶ βωμὸν ἐν ᾧ ἐπεγέγραπτο· Ἀγνώστῳ θεῷ. ὃ οὖν ἀγνοοῦντες εὐσεβεῖτε, τοῦτο ἐγὼ καταγγέλλω ὑμῖν."
(Πραξεις Αποστολων 17:23)

<< #የምታመልኩትን>> ከሚለው አማርኛ ይልቅ የበኩረ ቋንቋው(ግሪኩን) ይበልጡን መመልከቱ ጠቃሚ ነው። ምክንያቱም " #የምታመልኩትን" ብሎ የገባው << ታ ሴባስማታ ሁሞን(τὰ σεβάσματα ὑμῶν) >> የሚል የግሪኩ ሐረግ ነው። ሴባስማታ (σεβάσματα) የሚለውን የግሪክ ቃል ነጥለን ስንመለከተው የመጣው በቀጥተኛ ተሳቢ ሙያ(Accusative case) በብዙ ቁጥር አመልካች መደብ(plural form) በግዑዝ ጾታ(Neuter Gender) የገባ ሲሆን በቀጥታ ሲተረጎም << #የሚመለኩ ነገሮች>> የሚል ትርጓሜን ይሰጣል። ይህ ማለት ደግሞ ከላይ ለማየት እንደሞከርነው መድብለ አማልክት አምላኪዎች(Polytheists) እንደሚባሉ ተመልክተናል። ስለዚህ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በአቴና የሚገኙት ጣኦት አምላኪ ሰዎች መድብለ አማልክት አምላኪዎች (Polytheists) እንደሆነ እግረ መንገዱን ሲናገራቸው እንመለከታለን።

በመጨረሻም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በክርስትናና በግሪካውያን መካከል ያለውን የነገረ መለኮት ልዩነት በግልጽ ሁኔታ አሳይቷል። ደግሞ እኛ ክርስቲያኖች የክርስትናችን አስተምህሮ በስላሴ እምነተ አምድ ላይ የተመሰረተ ነው። በታሪክም ውስጥ ነብያት በብሉይ ሐዋርያት በአዲስ ኪዳን አስተምረው አልፈዋል። ቤተ ክርስቲያንም ይህን እውነት ተቀብላና አምና ስታስተምረውና ስትጠብቀው ቆይታለች። ስላሴ የሚለው ቃል በራሱ የእግዚአብሔር የመለኮታዊ መገለጫ ስያሜ ነው። ስላሴ የግእዝ ቃል ሲሆን *ሠለስት* ሶስት፤ *ሠለሰ* ሶስት ሆነ ማለት ሲሆን "ሥላሴ" ማለት ደግሞ *ሶስትነት በአንድነት* ማለት ነው።ይህም ማለት አንድ ሲሆን ሶስትነትም እንዳለው የሚያመለክት ነው። ይህም ደግሞ እግዚአብሔር በስም፣ በአካልና በግብር በሶስትነት የተገለጠ አምላክ ሲሆን በመለኮታዊ ስልጣን፣ በአገዛዝ፣ በባህሪ፣ በመፍጠርና በፍቃድ አንድ የሆነ አምላክ ነው። ስለዚህ አስተምህሮተ ስላሴ ፈጽሞ ስሉስ አማልክትን (Tritheism) የሚያሳይ አይደለም። በስሉስ አማልክት (Tritheism) የሚያምኑት ሞርሞኖች (የመጨረሻው ዘመን ቅዱሳን) የጆሴፍ ስሚዝ ተከታዮች እንጂ ስላሴያውያን አይደሉም። ስለ ሞርሞኖች በሰፊው በሌላ ጊዜ እንመለሳለን። ብዙ ለዘብተኛም ሆኑ አጥባቄያነ የነገረ መለኮት ሊቃውንት አስተምህሮተ ስላሴን የአሕዳዊ የመለኮት አስተምህሮ (Monotheism) እንደሆነ በጥናታቸው አረጋግጠውት እንመለከታለን።
(*William F. Albright, From the Stone Age to Christianity; H. Richard Niebuhr; *Monotheistic Religion resources; Kirsch, God Against the Gods; *Woodhead, An Introduction to Christianity; The Columbia Electronic *Encyclopedia Monotheism; *The New Dictionary of Cultural Literacy, monotheism)
እንዘ አሐዱ ሰለስቱ ወእንዘ ሰለስቱ አሐዱ

Jonathan(Yeshua Apologetics)
455 viewsedited  21:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 13:34:10 <<እውነታው ይህ ከሆነ [መንፈስ ቅዱስ አሁን እንደ ሆነው ሁሉ ዘላለማዊ ካልሆነ፣ በዘመናት ውስጥ ዕውቀትን ገብይቶ መንፈስ ቅዱስን መሆን ከቻለ] መንፈስ ቅዱስ ለዘላለም ዓለም መንፈስ ቅዱስ መሆን ካልቻለ፣ እንደማይለወጠው አብና እንደ ልጁ ሁሉ መንፈስ ቅዱስ የሥላሴ አንዱ አካል ነው ማለት አይቻልም>>(፯)

<<የመለኮት ምንጭ ብቻ ሁሉን ነገር በቃሉና በምክንዩው የሚይዝ ከሆነ፣ በሥላሴ አካላት ውስጥ መበላለጥ ወይም መተናነስ የለም>>(፰)

6)ሔሬኔዎስ(Irenaeus)፦ በ115 ዓ.ም ተወልዶ 190 ዓ.ም ሞተ፣ በልጅነቱ የሐዋርያው ዩሐንስ ደቀ መዝሙር ከነበረው ከጶሊቃርጶስ እግር ሥር የተማረ እንዲሁም የልዮን ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት የነበረ ሰው ነው፦

➞<<ቤተ ክርስቲያን በዓለም ሁሉ እንዲሁም እስከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ብትበተንም፣ ቤተ ክርስቲያን ከሐዋርያትና ከእነርሱ ደቀ መዛሙርት የተቀበለችውን የሚከተለውን መሠረተ እምነት ነው፦.....ሁሉን ቻይ የሆነ እና ሰማይንና ምድርን እንዲሁም ባሕርን በእነዚህም ውስጥ የሚኖሩትን ሁሉ የፈጠረ አንድ እግዚአብሔር፤ በእግዚአብሔር ልጅ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ፣ ለድነታችን ሲል ትስብእት የሆነ፣ በመንፈስ ቅዱስ፣ የእግዚአብሔርን ዘመን በነብያቱ ያበሠረ እንዲሁም የተወዳጁ ጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምጽአት፣ ከድንግል መወለድ፣ ሕማም፣ ከሙታን መነሣት፣ በአካለ ሥጋ ወደ ሰማይ ማረግ፣ "ሁሉን አንድ አድርጎ ለመሰብሰብ በአብ ክብር ከሰማይ መገለጥ፣ የሰው ልጆችን ሁሉ በአዲስ አካል ከሙታን ማስነሳት፣ ይኸውም ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታችንና አምላካችን እንዲሁም አዳኛችንና ንጉሣችን መሆኑን፣ በማይታየው አብ ፈቃድ "በሰማይና በምድር ከምድርም በታች" ያለ ጉልበት ሁሉ እንዲበረከክለት፣ ምላስም ሁሉ ኀጢአት ብሎ እንደ ተሰዋ እንዲመሰክርለት ነው....>>(፱)

ከጉባኤ ኒቂያ በፊት እንዲህ አይነት እምነት ያላቸው ከሆነ፣ የአስተምሮው ቀዳማይ አመንጪ ጉባኤ ኒቂያ ሳይሆን የሚባል ነገር የለም ግን ቢባል እንኳን ይህ አስተምህሮው ቃለ እግዚአብሔር ነው ማለት እንችላለን። ....ከኹሉ በፊት ግን በኒቂያ ነው የሥላሴ ትምህርት የጀመረው ቢባል እንኳን ክርስቲያኑ ማህበረሰብ ከቀድሞው አስተምሮው ጋር የማይጣጣም ነው በሚል ተቃውሞ ለምን አላቀረበም?...ኖሮስ ካለ ለምን በታሪክ ተዘግቦ አልተገኘም!?...

እነዚህን እና ተጨማሪ በክፍል ሁለት ይቀርባል

.....ይቀጥላል.....

ማጣቀሻዎች
፩ትምህርተ ሥላሴ መሠረታውያን በዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ
፪Martyrdom of Polycarp, 14. ANF, I:42.
፫Justin, First Apology, LXI. ANF, I:183.
፬Epistle to the Magnesians, Chapter 13
፭Tertullian, Against Praxeas, 2. PL 2.156–57.፣ በቅንፍ ያለውን አይጨምርም።
፮De Princ. 1.2.; PG 11.132).
፯Alexander Roberts and James Donaldson, eds., The Ante-Nicene Fathers, Grand Rapids: Eerdmans, 1975 rpt., Vol. 4, p. 253, de Principiis, 1.111.4)
፰Roberts and Donaldson, Ante-Nicene Fathers, Vol. 4, p. 255, de Principii., I. iii. 7
፱Irenaeus, Against Heresies X.1
ቸር ይግጠመን

.....ይቀጥላል.....

@CChristianApologetics
404 views10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 13:34:10 <<ትምህርተ ሥላሴ እና የቤተክርስቲያን ታሪክ>>
ክፍል አንድ(፩)

በመጀመሪያ ይህን ክፍል ለማጥናት ምሥጢረ ስላሴ ምን ማለት ነው!?

የትምህርተ ሥላሴ ቀዳማይ አመንጪ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። አንዳንድ ሥላሴን ስሩን ሳይዙት ዕውቀን ጨርሰናል በማለት ሲናገሩ አስተውያለሁ በዕውነቱ ያሳዝናል ለዚህም ነው በተለይ በአባቶች መምህራን የምሥጢረ ሥላሴ በስፋቱና በትልቅነቱ ሲነገርም እንዲህ ይባላል ፦

<<ምሥጢረ ሥላሴን ጠልቆ ለማወቅ መሞከር ባሕረ ውቅያኖስን በዕንቁላል እየቀዱ ለመጨረስ እየጨለፉም ለመጨለጥ እንደ ማሰብ ነው ይላሉ>>...እውነት ነው፤ ለሰው ከተሰጡ ስራዎች ምሥጥረ ሥላሴን ከመመርመር የሰፋና እና የከበደ የለም።

➝ ሆኖም ስለ ሥላሴ በትክክል ማሰብ ለክርስቲያናዊ ኑሮ ዋንኛ ነገር መሆኑን አንባቢ ልብ ይበል።...አይሁድ፣ ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች አንድን አምላክ ሲያመልኩ፥ የሥላሴን ትምህርት በአንድ አምላክ ከሚያምኑ ሌሎች ሁሉ ክርስቲያኖች ይለዩዋቸዋል።..ስለዚህ ክርስቲያን ለራሱ ብቻ ሳይሆን የራሱን እምነት ለሌሎች ለመግለጥም የሥላሴን ትምህርት ማወቅ ይገባዋል።..

➝ሥላሴ የሚለው ቃል በአዲስ ኪዳን
አይገኝም።...በግእዝ ቋንቋ ቃሉ <<ሦስትነት>> ማለት ነውና በትምህርተ መለኮት ጥቅም ላይ ሲውል..በአንዱ እግዚአብሔር ሦስት አካላት እንዳሉ ያሳስባል።

በ2ኛው መቶ ዓመት የአንጾኪያ ጳጳስ የነበረው ቴዎፍሎስ በግሪክ ቋንቋ <<ትሪአስ>> እና ጠርጡሊያን በላቲን ቋንቋ <<ትርንታስ>> በእንግሊዘኛው ደግሞ TRINITY የሚለው ሲሆን፣ ቃሉ "Tri" ወይም "ሦስት" እና "Unity" ወይም "ኅብረት/አንድነት" ከሚሉት ሁለት የላቲን ቃላቶች የመጣና አንድ ቃል ሆኖ በተገናኝ የሚነበብ ("tri" + "unity" ) ነው።(፩)

ሥላሴ የሚለው ቃልና ትምህርቱ <<እንደ መነጥር ሆነው በመፅሐፍ ቅዱስ ያለውን ትምህርት ጉልሕ ሆኖ እንዲታየን ያደርጋሉ እንጂ በእግዚአብሔር ቃል ላይ አዲስን ትምህርት አይጨምሩም።>>...ትምህርተ ሥላሴ ለክርስቲያን ረቂቅ ፍልስፍናም አይደለም። ወደፊት እግዚአብሔር ቢፈቅድ ሥላሴን በደንብ እንመረምራለን....ወደ ዋናው ርዕሴ ወደ ሚያንደረድር ሀሳብ ልመለስ....

ትምህርተ ሥላሴ እንደ አርዮስ ያሉ የመናፍቃን ጥቃት በቤተክርስቲያን ላይ ሲያደርሱ የመጠበቁ ሂደት ውስጥ ትልቅ ድርሻ ከነበራቸው አትናቴዎስ(Athanasius) አንዱ ቢሆንም ርእሰ ጉዳዩን በዳበረ መልኩ የተነተኑት ቀጰዶቃውያን አበው ናቸው።....በመጀመሪያ ከዛ በፊት <<ቀጰዶቃውያን>> አበው እነማን ናቸው የሚለውን በጥቂቱ እንመልከት...

ቀጰዶቃውያን አበው(Cappadocian Fathers) የሚባሉት ውስጥ፦
1, የቂሳርያው ትልቁ አባት ባልዮስ( Basil The Great)
2, ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ(Gregory of Nazianzus)
3,ጎርጎሪዮስ ዘኑሲስ (Gregory Nyssa) ናቸው።.ከላይ እንዳልኳቹህ እንደ እግረ መንገድ ዳሰሳ አደረግን እንጂ.ወደፊት በስፋት እንመለከተዋለን..

ትምህርተ ሥላሴ በቤተክርስቲያን ታሪክ ቅድመ ጉባኤ ኒቂያ አበው ግንዛቤአቸው ምን ነበር!?

ከላይ እነዳየነው ሥላሴ የሚለው ቃል በአዲስ ኪዳን ባይገኝም ትምህርተ ሥላሴ የነገረ መለኮት ዐብይ ርዕስ መሆኑን አይተናል።...የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች ምን ያህል ትምህርተ ሥላሴን እንደተረዱት ባናውቅም ግን፥ << እግዚአብሔር ሦስት አካላት እንዳሉ አምነው የመለኮትን አንድነትንና የአካል ሦስትነትን ለትምህርታቸው መሠረት አደረጓቸው>>.....

የትምሕርተ ሥላሴ ቀዳሚ አመንጪ መጽሐፍ ቅዱስ ቢሆንም፣ በሐዋሪያት እግር ስር የተማሩ ቀደምት የሆኑ የቤተክርስቲያን አበው ምን አሉ የሚለውን ጉዳይ መቃኘት፣ የተዛባ የታሪክ መረጃ ያላቸው ሰዎችን ለማቅናት ጠቃሚነት ስላለው ይህ ጽሑፍ ዳሰሳዊ ጥናት ስለሆነ የሁሉንም አበው እማኝነትና ትምህርት በክፍል አንድ በስፋት ማቅረብ ስለማይቻል በተወሰነው እንመለከታለን....

1) ጶሊቃርጶስ (Polycarp) :- በ70ዓ.ም ተወልዶ በ155 ዓ.ም ወይም በ160 ዓ.ም የሞተ፣ የሐዋሪያው ዮሐንስ ደቀ መዝሙር የነበረ እንዲሁም የሰምርኔስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት የነበረ ሰው ነው።..ይህ ሰው ትምህርተ ሥላሴን በተመለከተ እንዲህ ብሏል፦

<<ሁሉን ቻይ እግዚአብሔር ሆይ...ዘላለማዊና ሰማያዊ በሆነ ሊቀ ካህናት በምትወደውና ባከበርኸው ልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ለአንተና ለእርሱም እንዲሁም ለመንፈስ ቅዱስ አሁንም ሆነ ለዘላለም ክብር ይሁን>>(፪)

2) ዮስጦስ ሰማዕት (Justin Martyr) ፦ የቤተክርስቲያን አቃቤ እምነት የነበረና የሰማዕትነትን ክብር የተቀናጀው ይህ አባት አባት በ100 ዓ.ም ተወልዶ በ165 ዓ.ም እንደ ሞተ ይገመታል። ይህ አባት ትምህርተ ሥላሴን በተመለከተ እንዲህ ብሏል፦

<<የዓለማት ጌታ በሆነው በእግዚአብሔር በስመ አብ፣ በመድሐኒታችንም ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ በውሃ መታጠብን ያገኛሉ>>(፫)

3)አግናጢዮስ ዘአንጾኪያ (Ignatius of Antioch) ፦ የአንጾኪያ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት የነበረና በ98 ዓ.ም ወይም በ117 ዓ.ም እንደሞተ የሚገመት ክርስትናን ከመናፍቃን በመከላከሉ ዙሪያ ብዙ የጻፈ ዐቃቤ ክርስትና ነው። እንዲህም አለ፦

<<በእምነትና በፍቅር፤ በወልድ፣ በአብና በመንፈስ ቅዱስ፤ በመጀመሪያው እና በመጨረሻው፤ ከሚያስደንቅ ጳጳስችሁ ጋር እናም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ካሉ ዲያቆናት ጋር በሚገባ በጠበቀ መንፈሳዊ አክሊል የምታደርጉትን ሁሉ በስጋና በመንፈስ እንዲከናወን በጌታችንና በሐዋርያት ትምህረት እድትጸኑ አጥኑ። ክርስቶስ ኢየሱስ ለአብ በስጋው እንደተገዛለት እናም ሐዋርያት ለክርስቶስ፣ ለአብና ለመንፈስ ቅዱስ እደሚታዘዙ እናንተም ለጳጳሳችሁ እና እርስ በእርሳችሁ ተገዙ(ታዘዙ) በዚያን ጊዜ በስጋችሁም በመንፈሳችሁም አንድነት ይኖራችኋል።>>(፬)

4) ጠርጡሊያኖስ ወይም ተርቱሊያኖስ (Tertullian 160-215) ፦ አፍሪካዊ ዕቃቤ ክርስትና እንዲሁም የነገረ መለኮት ሊቅ ነው። ክርስትናን ከመናፍቃንና ከሌሎች ሐያስያን ለመከላከል ብዙ ጽፎአል፦

<<አብና ወልድ ሁለት ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ደግሞ ሦስት መሆናቸውን እንገልጻለን። የቁጥሩንም ቅድመ ተከተል ከድነት አንጻር ነው....ይህም አንድነትና ሦስትነትን መሠረት አድርጎ ሦስቱንም ማዕከል ያደረገ ነው፤ እነርሱም አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ። [አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ] ሦስት ናቸው....ነገር ግን በባሕርይ ሳይሆን በገጽ፣ በኀይል ሳይሆን ነገር ግን በዐይነት። በባሕርይና (Substance) በኀይል አንድ ናቸው፤ ምክንያቱም አንድ አምላክ ብቻ ስላለና ይህም ባሕርይ፣ ገጽና ዐይነት በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ዙሪያ ያለ በመሆኑ>>(፭)

5) አርጌንስ (Origen 185-254) ፦ የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን የነገረ መለኮት ምሁር ነው። አርጌንስ ክርስትናን በተመለከተ ብዙ የጻፈ ነው፦

<<የእግዚአብሔር ቃል ወይም የእግዚአብሔር ጥበብ ጅማሬ አለው የሚል ማንኛውም ሰው፣ ቢያንስ እግዚአብሔርን መናቁ እንደሆነ ልብ ሊለው ይገባል...ምክንያቱም እግዚአብሔር ባለፉት ዓመታት ሆነ ዘመናት ከዚህ ውጪ ሊገመት በሚችልበት ጊዜ ሁሉ፣ እግዚአብሔር የጥበብ ባለቤት ነውና ይህ እውነት ለእግዚአብሔር አብ እንደሆነው ሁሉ ለወልድም ነው>>(፮)
343 views10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 13:04:17
311 views10:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ