Get Mystery Box with random crypto!

አስ–ሱናህ

የቴሌግራም ቻናል አርማ tewihd — አስ–ሱናህ
የቴሌግራም ቻናል አርማ tewihd — አስ–ሱናህ
የሰርጥ አድራሻ: @tewihd
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.33K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው።
💎እዲሁም የኡለማዎች አጫጭር ፈትዋዎች ይለቀቁበታል إن شاء الله
ስተቴ በቁርአን በሀዲስ ላረመኝ الله ይዘንለት።

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 20:08:21 አንድ ቀን አንዲት አሮጊት ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ዘንድ መጣችና
ያረሱለላህ አላህ ጀነት ያስገባኝ ዘንድ ዱዓ አድርጉልኝ አለቻቸዉ
ረሱልም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የእገሌ እናት ሆይ....ጀነት ዉስጥ እኮ አሮጊቶች አይገቡም አሉዋት::
አሮጊትዋም የነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ንግግር ሀሳቡ ስላልገባት ማልቀስን ያዘች ነብዩ ግን እየቀለዱባት ነበር::
እዉነቴን ነዉ ጀነት ዉስጥ አሮጊቶች የሉም አሮጊት ሴት ጀነት
የምትገባዉ በአሮጊትነትዋ ሳይሆን ወጣትና ዉብ ሆና ነዉ በማለት ገለፁላት::
በማስከተለም ስለ ጀነት ሴቶች በቁርዓን የተጠቀሰዉን
አነበቡላት:-"( إنا أنشأناهن إنشاء فجعلناهن أبكارا عربا أترابا)"
"እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን ፈጠርናቸዉ ደናግሎችም አደረግናቸዉ" ::
(ኢማሙ ቲርሚዚ ዘግቧል ኢማሙል አልባኒ ሐሰን ብለውታል

https://telegram.me/tewihd
29 views17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 06:52:07 ‍ ይድረስ
ኢንተርኔት ለምትጠቀሙ እህቶች

በኢንተርኔት ከንቱ ምኞት ትዳርዋን የተበላሸባት፤ ህይወቷን የጨለመባት እንስት አስተማሪ ታሪክ…

ወጉ ወዲህ ነው
ሚስት አላህ ይጠብቀንና በኢንተርኔት ሱስ የተጠመደች ናት። ባለቤትዋ ከዚህ ተግባርዋ እንድትቆጠብ በተደጋጋሚ ቢመክራትም ልትቀበለው አልቻለችም። ብዙ ለመናት ብዙ አስመከራት "አሻፈረኝ" አለች። የምትጠቀምበትን ስልክ ሳይቀር ወስዶባታል። እሷም ሌላ ስልክ በመፈለግ ኢንተርኔት ላይ መዘውተሯን ቀጠለች።

በዚህ ጊዜ ባል አንድ ዘዴ ይዘይዳል
ወደ facebook በመግባት እንደ ሚባለው "fake acount" (የውሸት አድራሻ) በመክፈት ስሙን ይቀይርና ፕሮፋይሉ ላይ ሀብታምና ቆንጆ የሚመስል የወንድ ምስል ያስቀምጣል። ከዝያ በኋላ የሚስቱን የ facebook አድራሻ በመፈለግ ያናግራት ጀመረ።

ጨዋታው የተጀመረው እዚህ ቦታ ነበር
በሰላምታ የተጀመረው ንግግር ወደ ትውውቅ ይሸጋገርና ያለችበትን የኑሮ ሁኔታ ጨርሳ ትነግረዋለች። እሱ ግን እየዋሻት እሷን በምትፈልገው አይነት ራሱን እየገለፀ ያጫውታታል።
ባለ ትዳር እንደሆነችና ነገር ግን በትዳሯ ላይ ደስተኛ እንዳልሆነች ስትነግረው
"እንግዲያውስ ባልሽን ይፍታሽና ከእኔጋ እንደመር" ይላታል።
ባቀረበላት ሀሳብ ደስተኛ ሆና ከባልዋ ጋ በምን ዓይነት መልኩ መፋታት እንዳለባት መላ ይፈልጋሉ። እሱም "በቃ ሳትጎዳዱና ሳትጨቃጨቁ እንድትለያዩ ችግር በማይፈጥር መልኩ ባህሪሽን ቀይሪበት" ይላታል።

ባል ስራ ውሎ ማታ ሲገባ የሚስቱ ባህሪይ ከቀን ወደ ቀን እየተቀያየረ ይመጣል። ሚስት የማታውቀው ባል የፈጠረው ጨዋታ ነውና ቀን እያወራት ማታ ገብቶ ይታዘባታል። [አላህ ይጠብቀን]

ጨዋታው ሲጧጧፍ ባል ማታ ይገባና
"ሰሞኑ እያየሁብሽ ያለው ነገር እያስደሰተኝ አይደለም ምን ተፈጥሮ ነው?" ይላታል
"ምንም" ትለዋለች
"ንገሪኝ ችግርሽ ዝምታ መፍትሄ አይሆንም" ሲላት
"ምንም አልሆንኩም" ትለዋለች
"ሀሳብሽ በግልፅ ንገሪኝ ከእኔ መለየት ትፈልጊያለሽ ያልተመቸሽ ነገር አለ እንዴ?" ሲላት
"ቢሆን አይከፋኝም" ብላ ፍላጎትዋን ገለፀችለት።

ፍላጎቷን ግልፅ ካደረገች በኋላ ባልየው ቀጥታ ወደ ፈለገው ጨዋታ ይገባና ያናግራታል
"እንግዲህ መለያየታችን አይቀሬ ከሆነ አንቺም የሄድሽበት እንዲቀናሽ እኔም ቤቴና ንብረቴ ተበታትኖ ህይወቴ እንዳይበላሽ ከመሄድሽ በፊት ሁለተኛ ላግባና ልክ እንዳገባኋት ለእሷ አስረክበሽ ትሄጃለሽ" ይላታል።
ሚስትም ያሳሰባት ሁለተኛ ማግባቱ አለ ማግባቱ ሳይሆን የእሷ መፈታት ነበርና "ምንም ችግር የለውም" ብላ ትስማማለች።

ባልየው በማግስቱ ወደ ሚስቱ ቤተሰቦች በመሄድ የተነጋገሩበት ነገር ያጫውታቸውና ሁለተኛ ሊያገባ መሆኑ ይነግራቸዋል።
ሁለተኛ ሚስት ፍለጋ ተ ጀ መ ረ

ባል ሊያገባት ሚስት ደግሞ አስረክባት የምትወጣዋ ሁለተኛ ሚስት በሁለቱም ብርቱ ፍለጋ "ትሆናለች፣ ትመጥናለች" የተባለችዋን አፈላልገው አገኙ።
ያዝ እንግዲህ……

የሁለተኛዋ ሚስት የኒካህ ቀጠሮ ይያዛል። ልብ በሉ ሁለተኛዋ እንደ መጣች የመጀመሪያዋ ተሸኝታ ያ በኢንተርኔት መንፈስ ብቻ የምታውቀው ባልዋ ሊያገባት ነው።

የማይደርስ የለምና የኒካሁ ቀን ደረሰ። ባል ልክ የሁለተኛ ሚስቱ ኒካህ እንዳሰረ ያ ሚስቱን ሌላ ሰው መስሎ ያወራበት የነበረው የ facebook አድራሻ ዘግቶት ከኢንተርኔት መንደር ይወጣል።
لا إله إلا الله

የመጀመሪያዋ ሚስት ባልዋ ሌላ እንዳገባና ከባልዋ ተለያይታ አዲስ የተዋወቀችው ሰወዬ ልታገባው እንደሆነ ልታበስረው ስትገባ ያ በውሸት ሲያወራት የነበረው ባለ facebook አድራሻው ዘግቶ ከመንደሩ ጠፍቷል።

ዱንያ የት አትጥበባት?
"ምድር ዋጭኝ" ብትላት መች ልትውጣት? ህይወት ጨልሞባት፣ መኖር አስጠልቷት ራሷን እየረገመች አዝና ተክዛ ቁጭ ብላለች።

ባል አዲሷ ሙሽራው ጋ መቆየት ያለበትን ቆይቶ መጫወት ያለበትን ተጫውቶ ወደ ቀድሞ ሚስቱ ቤት ሲሄድ በሀዘን ተውጣ ተቀምጣለች።
"ምንድን ነው ሰላም አይደል እንዴ?" ሲላት
"ሰላም ነው" ትለዋለች
"ምን ሆንሽ?" "ምንም"
ትቷት ይሄዳል።

አሁንም ተመልሶ ሲመጣ ሰውነቷ ከሳስቶ ፊቷ ተሸብሽቦ ያገኛታል
"ምንድን ነው የሆንሽው?"
"ምንም አልሆንኩም"
"ያስቀየምኩሽ ነገር አለ"
"ኧረ የለም"
"ሀሳብ መቀየር አስበሽ ነው?"
ፀጥ ረጭ አለች።

የዛኔ ባል አጠገቧ ቁጭ ብሎ እያፅናናት
"ምን ላርግ ታድያ? ከአንቺ መኖር እየፈለግሁ፣ ሳልጠላሽ፣ ሳላስከፋሽ በራስሽ ፍላጎት ያመጣሽው ሀሳብ ነው። እኔ ግን አሁንም ቢሆን የማከብርሽ የምወድሽ ባለቤቴ ነሽ። አንቺም ከእኔ የመለየት ፍላጎት ከሌለሽ ያመጣኋትም ሙስሊም እህትሽ ናት አብራችሁ ትኖራላችሁ። እሷም በቤቷ አንቺም በቤትሽ አብረን እንኑር።" አላት

በዚህ ሰዓት ካላይዋ ላይ የተጫናት ተራራ የተነሳላት በሚመስል መልኩ በደስታ ፈንጥዛ ባልዋን እየሳመችና እያመሰገነች እያለቀሰች ደስተኝነቷን ገለፀችለት።

በመጨረሻም ባልየው ባለ ሁለት ሲም ሆኖ ከሁለቱም ሚስቶቹ ጋ አብረው መኖር ጀመሩ።


NB: ታሪኩ ላይ የተጠቀሱ በሸሪዓ ክልከላ ያለባቸው ነጥቦች አሉ [ፎቶ መጠቀምና ውሸትን] ይመስል
ዘንግተናቸው ሳይሆን ከታሪኩ ብዙ ሰው ሊማር ይችላል ብለን ስላሰብን ነው።
ማስተላለፍ የተፈለገውም ባሎች እንዲህ እንዲያደርጉ ሳይሆን ሴቶች ከምንም ነገር በፊት ክብራቸውን (ትዳራቸውን) ማክበርና መታዘዝ እንዳለባቸው ለማስገንዘብ ነው።


https://t.me/tewihd/
104 views03:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 06:46:07 _ሁለተኛ ሚስት ማግባት ያሰኘው ሰው ለሚስቱ ይቺን( የኢብኑ ባዝ) መልክት እንድታነብ ይስጣት ፡፡_
_
ሸይኽ ኢብኑ ባዝ (ረሂመሁላህ) ይሄን ጥያቄ ተጠየቁ ፡

ጥያቄ፡- ክቡር ሸኽ አንዲት ሚስት አለችኝ፡ ከእሷም ልጆች አሉኝ፡ ሁለተኛ ሚስት ለማግባት በጣም እፈልጋለው፡ ግን ስለዚህ ጉዳይና ማግባት እንደምፈልግ ሚስቴን በነገርኳት ቁጥር አይሆንም ትለኛለች ፡ ካገባህ ትቼህ እሄዳለው ልጆችህንም ጭምር እያለች ትዝትብኛለች፡ ሸይኽ እኔንም እሷንም ምን
ትመክሩናላችሁ


መልስ፡- አንቺ የአላህ ባሪያ ሆይ ! በዚህ ተግባርሽ አላህን ልትፈሪው ይገባል፡ ማግባት የባል መብት (ሃቅ) እንጂ የሚስት አይደለም ፡ ባል ሁለተኛም፣ ሶስተኛም፣ አራተኛም ማግባት ቢፈልግ ሚስት መከልከል አትችልም ፡፡ ይሄን የደነገገው ከሰባት ሰማያት በላይ ያለው (አላህ ሱብሃነሁ ወተኣላ) ነው፡፡ አላህ ለወንዶችም ሆነ ለሴቶች የሚበጀውን ያውቃል፡፡ ለዚህም ነው አላህ ይሄን የፈቀደው ለብዙ ጥቅሞች ሲል ነው፡ ከፊሎቹ ጥቅሞች ለራሷ ለሚስት ሲሆኑ ፡ ...... ከዚህ ሁሉ ዋናውና አሳሳቢው
ነገር ግን ባልሽ ሁለተኛ ማግባቱን መጥላትሽ ይህ በአንቺ ላይ በጣም ከባድ የሆነ አደጋ ነው ፡ አላህ በቁርአኑ ላይ ካወረደው ህግ ከፊሉን በመጥላትሽ መልካም ስራወችሽ እንዳይታበሱብሽ የሚያስፈራ ከባድ አደጋ ነው፡ ምክኒያቱም አላህ ግልፅ በሆነ የቁርአን አንቀፅ እስከ አራት ድረስ ሚስትን መደጋገም አዟል ፡፡
አላህ እንዲህ ይላል፡-
(وَإِنْ خِفْتُمْ أَلَّا تُقْسِطُوا فِي الْيَتَامَىٰ فَانْكِحُوا مَا طَابَ لَكُمْ مِنَ النِّسَاءِ مَثْنَىٰ وَثُلَاثَ وَرُبَاعَ ۖ فَإِنْ خِفْتُمْ أَلَّا تَعْدِلُوا فَوَاحِدَةً أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَانُكُمْ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَلَّا تَعُولُوا
" ከሴቶች ለእናንተ የተዋበላችሁን ሁለት ሁለት፣ ሶስት ሶስትም፣ አራት አራትም አግቡ ፡
[ ምዕራፍ፡ ኒሳዕ፣ አንቀፅ 3 ]
አላህ በቁርአን ላይ ያወረደውን ህግ መጥለት መልካም ስራወችን የግድ ያሳብሳል፡፡
አላህ እንዲህ ይላል፡-" ይህ እነርሱ አላህ ያወረደውን ስለጠሉ ነው ስለዚህ ስራወቻቸውን አበላሸባቸው "
[ምዕራፍ፡ ሙሃመድ፣ አንቀፅ 9]
መልካም ስራን ለማሳበስ የግድ ሁሉንም አላህ ያወረደውን ማስተባበል አይጠበቅብሽም፡ አንዲትም
ብትሆን በቂ ናት
፡፡


( _ፈትዋ ኑሩን አለ - ደርብ_)

https://t.me/tewihd/
91 viewsedited  03:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 13:28:14 ከወንጀል ሁሉ የከፋ ወንጀል.....
[ ከኢብኑል ቀይም ንግግር]

★<በወንጀል መደሰትህ ከአላህ ዘንድ ከወንጀሉ የባሰ አስከፊ ነው።ወንጀል እየሰራህ መሳቅህ ከአላህ ዘንድ ከወንጀሉ ይበልጥ ከባድ ጥፋት ነው። ምክንያቱም ለአላህ ይሉኝታ አጥተሃልና፤ እርሱን ማፈር ትተሃልና....

★አንድ ወንጀል ስላመለጠህ ማዘንህ ከአላህ ዘንድ ከወንጀሉ የከፋ ወንጀል ነው። ወንጀል እየሰራህ ወንጀሉን ለመደበቅ መሞከርህም ከአላህ ዘንድ ከወንጀሉ የባሰ ሐጢአት ነው።ምክንያቱም እርሱ እያየህ መሆኑን ታውቃለህና.... @tewihd
149 views10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 07:42:03 # "አላ ቢዚክሪላሂ ተጥመኢኑል ቁሉብ!!"


ወንድሞችና እህቶች ስራችን ብለን ቁጭ ብለን ዚክር ላለማረጋችን አዋጣም አላዋጣም ምክኒያት ይኖረን ይሆናል፡፡ አሰልቺ ረጃጂም ጉዞዎችን ስናደርግ አሁንም አሁንም ከማዛጋት፣ አስቀያሚ ማስታወቂዎች ላይ ከማፍጠጥ፣ ዚክር ብናረግ ምን ነበረበት? ሱብሃለህ!!! አንዴ ሱብሃለህ ሳንል ስንት መቶ ኪሎ ሜትሮችን አቋርጠናል?! ስንት ረጃጅም ሰአቶችን በከንቱ አሳልፈናል? አራት መቶ አምስት መቶ ኪሎ ሜትሩ ይቅር:: የአራትና አምስት ሰዐት መንገዱም ይቅር:: ኧረ ሌላው ቀርቶ የፒያሳ መገናኛ፣ የመርካቶ አየር ጤና መንገድም ይቅር እሩቅ ነው እንበል:: በአንዲት አጭር ፌርማታ ስንትና ስንት ዚክር ማረግ ስንት አጅር ማፈስ አይቻልም? እውነት በዚክሩ የሚገኘው አጅር በገንዘብ ቢቀየር እንዲህ እንዘናጋ ነበር? አቤት የኛ ነገር!!!
እስኪ አንድ ደቂቃ በማይፈጁ ዚክሮች የሚገኘውን አጅር ያስቡ
- “ሱብሐነላሂ ወቢሐምዲሂ ሱብሐነላሂል ዐዚም” በሐዲስ እንደተነገረው እነኚህ ለምላስ የሚቀሉ፣ ሚዛን ላይ የሚከብዱ፣ አረሕማን ዘንድ የተወደዱ ቃላት ናቸው፡፡ በደቂቃ ስንቴ ማለት ይቻላል?
- “ላሐውለ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላህ” ከጀነት ድልብ ሀብቶች ውስጥ አንዷ ነች፡፡ በደቂቃ ስንቴ ማለት ይቻላል?
- የነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ባለቤት ጁወይሪያ ከፈጅር ሶላት እስከ ረፋድ ዚክር ስታደርግ ቆይታ “እኔ ካንቺ በኋላ አራት ከሊማዎችን ሶስት ጊዜ ደጋግሜ ብያለሁ፡፡ ብትመዘን እስካሁን አንቺ ካልሺው ትበልጣለች አሏት፡፡(ሱብሐነላሂ ወቢሐምዲሂ ዐደደ ኸልቂሂ፣ ወሪዷ ነፍሲሂ፣ ወዚነተ ዐርሺሂ፣ ወሚዳደ ከሊማቲሂ)
- አንዴ በነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ላይ ሶላት ያወረደ አላህ በሱ ላይ 10 ሶለዋት ያወርድበታል፡፡ በደቂቃ ስንቴ ማድረግ ይቻላል? … እነኚህ ጥቂት ምሳሌዎች ናቸው፡፡
ውድ የኢስላም ወንድሞችና እህቶች ኢስላም እኮ ሂወት ነው፡፡ አይደል እንዴ? ጁሙዐ ወይም ረመዳን ብቻ ተጠብቆ ሽር ጉድ የሚባልበት ድግስ አይደለም፡፡ “የኢስላም ድንጋጌዎች በዙቡኝ” ያላቸውን ሰው “ምላስህ አላህን በማውሳት ከመርጠብ አይወገድ” ብለው አይደል ያመላከቱት ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም? ጌታችን እንዲህ ይላል፡ ((… እነዚያ ያመኑት ልቦቻቸውም አላህን በማስታወስ የሚረኩ ናቸው፡፡ አዋጅ! አላህን በማስታወስ (የአማኞች) ልቦች ይረካሉ)) (አረዕድ፡ 28) ነብያችን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ፡ ((ጌታውን የሚያስታውስና እና የማያስታውስ ምሳሌ የህያው እና የሙት ምሳሌ ነው)) ቡኻሪና ሙስሊም፡፡ አሁን እኛ ህያዋን ነን ወይስ የቁም ሙት?
የአላህ ሰዎች ሀይላቸውም፣ ምግባቸውም፣ እስትንፋሳቸውም፣… ዚክር ነው፡፡ በአንድ ወቅት ያነበብኩት የኢብኑል ቀይም ረሒመሁላህ ንግግር ትዝ አለኝ፡፡ ካየሁት ቆየሁና ምናልባት በትክክል ላላሰፍረው እችላለሁ፡፡ በግርድፉ ይሄን ይመስላል፡፡ “እንደ ኢብኑ ተይሚያ ዚክር የሚያበዛ አላየሁም፡፡ በአንድ ወቅት ፈጅር ከሰገደ ጀምሮ ዚክር ያረጋል፡፡ ባለበት ሁኔታ ላይ እያለ ሰዐቱ በጣም ሄደ፣ ረፈደ፡፡ በሁኔታው ተገርሜ እያየሁት ነው፡፡ እንደተገረምኩ ገብቶታል፡፡ ዘወር ብሎ እንዲህ አለኝ፡- “ይሄ ምግቤ ነው፡፡ እሱን ካላገኘሁ ብርታት አይኖረኝም”
“ጌታችን ሆይ! አንተን ለማስታወስ፣ አንተን ለማመስገን እንዲሁም አንተን ባማረ መልኩ ለመገዛት አግዘን፡፡”


➥ሼር
https://t.me/tewihd/
108 views04:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 22:07:13 #የላሟ እና የአላህን ፈሪው ልጅ ታሪክ
#የመጨረሻው ክፍል

ሙሳም አለሂ ሰላም ልጁን «ለምን አትሸጥላቸውም» ብለው ሲጠይቁት «መሸጥ ያለብኝ በዚህ ዋጋ ስለሆነ ነው»አላቸው ነብዩላህ ሙሳም «በዚህ ካልሆነ አልሸጥም ብሏል የሰውን ንብረት እኛ ካልሸጥክ ብለን ማስገደድ ስለማንችል በሚሸጥላችሁ ዋጋ መግዛት አለባችሁ» አሏቸው። ተንኮል አስበው የተወሰነ ቀብድ ሰጥተውት ሌላ ጊዜ እንሰጥሃለን ብለው በማታለል ጊደሯን ማረድ ፈለጉ። እንዲህም አሉት«የተወሰነ ገንዘብ እንስጥህና ግማሽ ከፍለን ግማሹን ሌላ ጊዜ እንሰጥሃለን አሁን ጊደሯን ሽጥልን የምትለውን ዋጋ በምትፈልገው ጊዜ ሞልተን እንከፍልሃለን እኛም ተቸግረን ነው ባለየን ሰው ገድላቹሃል ተብለን በወንጀል ተጠርጥረን ነፃነታችንን ማረጋገጥ ፈልገን ነውና ልትተባበረን ይገባል »አሉት።

ተንኮለኛ እና አታላይ ሰው ያለ ስለማይመስለው ያሉትን አምኖ ይሸጥላቸዋል። እናም ጊደሯን አርደው የሞተውን በድን ሲመቱት የተባለው በድን ሳይነሳ ሳይናገር ሲቀር ።ለነብዩላህ ሙሳ የሞተው ሰው ይነሳል ብለውን ነበር ያሉትን ብናደርግም ተነስቶ ሊናገር አልተቻለም ።አሏቸው
ነብዩላህ ሙሳ «ለመሆኑ የጊደሯን ዋጋ በሙሉ ከፍላቹሀልን» ዋጋውን ከፍላችሁ ካልጨረሳችሁ ሰውየው ተነስቶ አይናገርም ሲሏቸው በኒ እስራኤሎች ያለ የሌለ ሀብትና ንብረት እየሸጡና እለወጡ ወርቅ በመግዛት ቆዳውን እንሞላለን ብለው ቢጥሩም ሊሞላ አልቻለም ። ምክንያቱም እነሱ ወርቁን በጨመሩ ቁጥር ጅብሪል አለሂ ሰላም የጊደሯን ቆዳ እየተለጠጠ ይሰፋ ያደርገው ስለነበር። በኒ እስራኢሎች በዚህ ላይ እያሉ አንዲት ጧሪ ቀባሪ የሌላት በእድሜዋ የገፋች ሴት በአካባቢው ስለነበረች እሷ እንኳን ሳትቀር ለጊደሯ ዋጋ የሚከፈል ገንዘብ አምጪ ብለው ሲያስገድዷት ( ላኢላሀ ኢለላህ ሙሳ ረሱሉላህ) የሚል ፅሁፍ ያለበት የጣት ቀለበት በስተቀር ምንም ስላልነበራት የጣት ቀለበቷን ሰጠቻቸው ። በቀለበቱ ላይ የአላህ ስም ስለነበረበት ነበር የጊደሯ ቆዳ የሞላው።

እናም ዋጋውን በሙሉ ከከፈሉ ቡሀላ ነብዩላህ ሙሳ የተገደለውን በድን በከፊል ስጋዋ ሲመቱት ከሞት ተነስቶ «የገደለኝ የወንድሜ ልጅ ነው»ብሎ ሲያጋልጠው ። ተገድሎ ከስስታም አጎቱ ጋር ተቀበረ።
#በዋናነት የታሪኩ ሀሳብ በጥልቅ በቁርአን ውስጥ ሱረቱል በቀራ ላይ ከ67―73 ድረስ እንዲህ በማለት ገልፆታል
*
ﻗﺎﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺗﻌﺎﻟﻰ: } (ﻭَﺇِﺫْ ﻗَﺎﻝَ ﻣُﻮﺳَﻰ
ﻟِﻘَﻮْﻣِﻪِ ﺇِﻥَّ ﺍﻟﻠَّﻪَ ﻳَﺄْﻣُﺮُﻛُﻢْ ﺃَﻥْ ﺗَﺬْﺑَﺤُﻮﺍ
ﺑَﻘَﺮَﺓً ﻗَﺎﻟُﻮﺍ ﺃَﺗَﺘَّﺨِﺬُﻧَﺎ ﻫُﺰُﻭًﺍ ﻗَﺎﻝَ ﺃَﻋُﻮﺫُ
ﺑِﺎﻟﻠَّﻪِ ﺃَﻥْ ﺃَﻛُﻮﻥَ ﻣِﻦَ ﺍﻟْﺠَﺎﻫِﻠِﻴﻦَ * ﻗَﺎﻟُﻮﺍ
ﺍﺩْﻉُ ﻟَﻨَﺎ ﺭَﺑَّﻚَ ﻳُﺒَﻴِّﻦْ ﻟَﻨَﺎ ﻣَﺎ ﻫِﻲَ ﻗَﺎﻝَ
ﺇِﻧَّﻪُ ﻳَﻘُﻮﻝُ ﺇِﻧَّﻬَﺎ ﺑَﻘَﺮَﺓٌ ﻟَﺎ ﻓَﺎﺭِﺽٌ ﻭَﻟَﺎ
ﺑِﻜْﺮٌ ﻋَﻮَﺍﻥٌ ﺑَﻴْﻦَ ﺫَﻟِﻚَ ﻓَﺎﻓْﻌَﻠُﻮﺍ ﻣَﺎ
ﺗُﺆْﻣَﺮُﻭﻥَ * ﻗَﺎﻟُﻮﺍ ﺍﺩْﻉُ ﻟَﻨَﺎ ﺭَﺑَّﻚَ ﻳُﺒَﻴِّﻦْ
ﻟَﻨَﺎ ﻣَﺎ ﻟَﻮْﻧُﻬَﺎ ﻗَﺎﻝَ ﺇِﻧَّﻪُ ﻳَﻘُﻮﻝُ ﺇِﻧَّﻬَﺎ ﺑَﻘَﺮَﺓٌ
ﺻَﻔْﺮَﺍﺀُ ﻓَﺎﻗِﻊٌ ﻟَﻮْﻧُﻬَﺎ ﺗَﺴُﺮُّ
ﺍﻟﻨَّﺎﻇِﺮِﻳﻦَ * ﻗَﺎﻟُﻮﺍ ﺍﺩْﻉُ ﻟَﻨَﺎ ﺭَﺑَّﻚَ ﻳُﺒَﻴِّﻦْ
ﻟَﻨَﺎ ﻣَﺎ ﻫِﻲَ ﺇِﻥَّ ﺍﻟْﺒَﻘَﺮَ ﺗَﺸَﺎﺑَﻪَ ﻋَﻠَﻴْﻨَﺎ ﻭَﺇِﻧَّﺎ
ﺇِﻥْ ﺷَﺎﺀَ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻟَﻤُﻬْﺘَﺪُﻭﻥَ * ﻗَﺎﻝَ ﺇِﻧَّﻪُ
ﻳَﻘُﻮﻝُ ﺇِﻧَّﻬَﺎ ﺑَﻘَﺮَﺓٌ ﻟَﺎ ﺫَﻟُﻮﻝٌ ﺗُﺜِﻴﺮُ ﺍﻟْﺄَﺭْﺽَ
ﻭَﻟَﺎ ﺗَﺴْﻘِﻲ ﺍﻟْﺤَﺮْﺙَ ﻣُﺴَﻠَّﻤَﺔٌ ﻟَﺎ ﺷِﻴَﺔَ
ﻓِﻴﻬَﺎ ﻗَﺎﻟُﻮﺍ ﺍﻟْﺂﻥَ ﺟِﺌْﺖَ ﺑِﺎﻟْﺤَﻖِّ ﻓَﺬَﺑَﺤُﻮﻫَﺎ
ﻭَﻣَﺎ ﻛَﺎﺩُﻭﺍ ﻳَﻔْﻌَﻠُﻮﻥَ * ﻭَﺇِﺫْ ﻗَﺘَﻠْﺘُﻢْ ﻧَﻔْﺴًﺎ
ﻓَﺎﺩَّﺍﺭَﺃْﺗُﻢْ ﻓِﻴﻬَﺎ ﻭَﺍﻟﻠَّﻪُ ﻣُﺨْﺮِﺝٌ ﻣَﺎ ﻛُﻨْﺘُﻢْ
ﺗَﻜْﺘُﻤُﻮﻥَ * ﻓَﻘُﻠْﻨَﺎ ﺍﺿْﺮِﺑُﻮﻩُ ﺑِﺒَﻌْﻀِﻬَﺎ
ﻛَﺬَﻟِﻚَ ﻳُﺤْﻲِ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﺍﻟْﻤَﻮْﺗَﻰ ﻭَﻳُﺮِﻳﻜُﻢْ ﺁﻳَﺎﺗِﻪِ
ﻟَﻌَﻠَّﻜُﻢْ ﺗَﻌْﻘِﻠُﻮﻥ)
«ሙሳም ለሕዝቦቹ«አላህ ላምን እንድታርዱ ያዛችኋል»ባለ ጊዜ የሆነውን አስታውሱ «መሳለቂያ አድርገህ ትይዘናለህ?»አሉት «ከተሳላቂዎች ከመሆን በአላህ እጠበቃለው» አላቸው። «ለኛም ጌታህን ጠይቅልን እርሷ ምን እንደሆነች እድሜዋን ያብራራልን አሉ።ጊደር ናት ይላችኋል ፤ የታዘዛችሁትንም ስሩ» አላቸው። «ለኛ ጌታህን ጠይቅልን ፣እርሷ ምን እንደሆነች ይግለፅልን ከብቶች በኛ ላይ ተመሳሰሉብን።እኛም አላህ የሻ እንደሆነ በእርግጥ ተመሪዎች ነን»አሉ። እርሱ እርሷ ያልተገራች ምድርን «በማረስ»የማታስነሳ እርሻንም የማታጠጣ «ከነውር» የተጠበቀች ልዩ ምልክት የሌለባት ናት ይላችኋል»«አሁን በትክክል መጣህ»አሉ ሊሰሩ ያልተቃረቡ ሲሆኑ አረዷት።

ነፍስንም በገደላችሁና በርሷም «ገዳይ»በተከራከራችሁ ጊዜ «አስታወስ። አላህም ትደብቁት የነበራችሁትን ሁሉ ገላጭ ነው። «በድኑን በከፊሏም ምቱት»አልን እንደዚሁ አላህ ሙታንን ያስነሳል፤ታውቁም ዘንድ ታምራቶችን ያሳያችኋል» ሲል ሚስጥሩን በቁርአን ውስጥ በነዚህ አንቀፆች ገልፆታል ።


ታሪኩ አስተማሪ ነው ተጠቀሙበት

https://t.me/tewihd/
139 views19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 08:21:13 #የላሟ እና የአላህን ፈሪው ልጅ ታሪክ
ክፍል#2

ልጁም እናቱ እንደነገረችው ወደ ተባለው ተራራ ሄዶ ልክ አላህን በሚጠይቅ ጊዜ ጥጃዋን እንዳየች ላም ከጫካ ውስጥ ወጥታ እየጮኸች በመምጣት ወደሱ ቀረበች ። በሚያስገርም መልኩ ያያት ሁሉ በመልኳ እንደሚደነቅና እንደ ሚፈዝ በቁርአን ውስጥ /በምዕራፍ ሁለት አንቀፅ 69 / ላይ «ለሚያያት ሁሉ የምታስደስት ናት» በሚል ተገልጻለች ።ከዚያም በሰውኛ ቋንቋ «አባትህ ለአላህ አደራ ሰጥቶኝ የሄደው እኔን ነው በጀርባዬ ወጥተ እንደ ፈረስ ጋልበኝ» ስትለው «እኔ እናቴ አላዘዘችኝም ቀንዷን በገመድ አስረ አምጣ ነው ያለችኝ» ሲላት «የእናትህን ትእዛዝ ባታከብር ኖሮ እኔም ለፈተና እንጂ ለመጋለብ አልተፈጠርኩም የትም በረሃ ለበረሃ ይዤክ እሄድ ነበር»አለችው።

ጊደሯን እየጎተተ ወደ እናቱ ጋ ይሄዳል። እንደማንኛውም ሰው ጊደሯን ጠዋት ወጥት ማታ ስትገባ የጎረቤት ሰዎች «ጊደሯ ስትወጣ እና ስትገባ አንዳንድ ጥፋት አደረሰችብን» እያሉ ሲያሰሙ እናት አላህን ፈሪ ስለነበረች ይህች ጊደር ከጎረቤት ሰው ጋር ከምታቀያይመን በእሷ የመጣ ጥቅም ይቅርብን ገበያ ወስደህ ሽጣት ስትለው። እሱም በስንት መሸጥ እንዳለበት እናቱን ሲያማክር «ላሟን ብዙ ስላልደከምንባት በአላህ ጥበቃ ስር ስለኖረች ትርፉ ይቅርብን የተገዛችበት 3 ዲናር ስለሆነ በሶስት ዲናር ሽጣት» አለችው።

ገበያ እንደወሰዳት አንድ የከብት ነጋዴ የመሰለ ሰው የጊደሯ ዋጋ ስንት ነው ብሎ ሲጠይቀው «ሶስት ዲናር »ሲል« ሞኝ ነህ እንዴ እንዴት ሶስት ዲናር ትላለህ አንተ እንደምትለው በሶስት ዲናር ብገዛት ሰው አያምነኝም ያታለልኩህ ስለሚመስላቸው በስድስት ዲናር ነው የምገዛህ» ሲለው «እኔ ሞኝ አይደለሁም እናቴ ያዘዘችኝ በ3 ዲናር እንድሸጣት ነው ከፈለክ ግዛት» ሲለው «እናትህ ሽጥ ካለችህ በላይ አተረፍክ እንጂ አልከሰርክም» ሲለው «ምን ይታወቃል ለምን ባልኩህ ዋጋ አልሸጥክም ብላ ብትቆጣኝስ» ሲል ቤቱ በአቅራቢያ ስለነበር «ሂድና እናትህን በስድስት ዲናር ልሽጣት ወይ ብለህ ጠይቃት» አለው።

እቤት ደርሶ ለእናቱን «ልሽጣት ወይ» ብሎ ሲጠይቃት ሽጣት ብላ ፈቀደችለት ። እናም ወደ ሰውዬው ተመልሶ «እናቴ ሽጣት ብላኛለች እና በስድስት ዲናር ግዛት» ሲለው። ከብት ነጋዴውም «አይ አልገዛም አስራሁለት ዲናር ነው የምገዛህ» ሲል። ነጋዴው እስኪተዋት ጣልቃ ላለመግባት የሚጠብቁ ሌሎች ሰዎች ስለነበር። ልጁ በንዴት «ለምንድን ነው ለሌላ ሰው እንዳልሸጥ የጊደሯን ዋጋ የምትዘጋብኝ ካገኘው ለሌላ እሸጣታለው» ሲለው
«አሁንም ሂድና እናትህን በ12 ዲናር ልሽጣት ወይ ብለህ አማክራት እኔ ነኝ የምገዛት እንጂ ሌላ ሰው እንዲወስዳት አልፈልግም።» አለው።

ልጅ ለሁለተኛ ጊዜ ሄዶ ለእናቱ ሲያማክራት «ምንአልባት መላኢካ እንጂ ሰው እንደዚህ አይልም እናም ተመለስና ጊደሯን መሸጤ ነው ወይስ አለመሸጤ የሚያዋጣኝ ምን የምትመክረኝ ነገር አለ ብለህ » ጠይቀው አለቸው።
እናትየው ያው እንደገመተችው ሌላ ሰው እንዳይገዛ ሊመልስ የመጣ መላኢካ ነበር።ልጅ እናቱ ያለቸውን ሲነግረው «እንግዲያውስ የምመክርህ ጊደሯን መሸጥ ያለብህ ገዢው ቤትህ ድረስ ሲመጣ ነው ።ዋጋዋም ጊደሯ ታርዳ በቆዳዋ ሙሉ ወርቅ ተሰፍሮ ነው የምትሸጠው ከዚህ በላይ እንዳትሸጥ ።በቅርብ ጊዜ መጥተው ይጠይቁሀል እና ያኔ ነው የምትሸጣት ።» ምክሩን በመቀበል ጊደሯን ይዞ ወደ ቤቱ እንደተመለሰ።

በዚያው ሰሞን በአካባቢው አንድ ክስተት ተፈጠረ ።እሱም
በአካባቢው የሚኖር ባለፀጋ ሰው ነበር ።ከአንዲት ልጅ በስተቀር ሌላ ቤተሰብ አልነበረውም ።
አንድ ምንም ዱኒያ የሌለው የወንድሙ ልጅ ነበርና አጎቱ የሚቋቋምበት ገንዘብ እንዲረዳው ፈልጎ እንዲህ ሲል ጠየቀው« አጎቴ ሆይ አንተ የተረፈክ ሀብታም ነህ ።አንተ እያለህልኝ ለምንድን ነው የምቸገረው? አንተ እያለህ ማንን ነው ምጠይቀው? የተወሰነ ገምዘብ ስጠኝና እንደሰው እራሴን ችዬ እንድኖር ልታደርገኝ ይገባል። »አጎት በጣም ስስታም ስለነበር ልጁን ሊረዳው ፍቃደኛ አልሆነም።

በዚህም ተናዶ እያለ ሰዎች እንዲ ብለው መከሩት«ልጁን በሚስትነት እንዲሰጥህ ጠይቅ ምናልባት ለልጁ ሲል ሀብትና ንብረቱን ሰጥቶ ያቋቁምህ ይሆናል» ሲሉት

አጎቴ ሴት ልጁን በሚስትነት ይስጠኝ በማለት የላካቸው ሽማግሌዎች አጎቱን ሲጠይቁለት አጎት እንዴት ደፈረኝ በማለት የላካቸውን ሽማግሌዎች ገልምጦና ሰድቦ ሲመልስበት ። ልጁ በአጎቱ ንቀት በመበሳጨት «እንዴት ገንዘብ ባይኖረኝ በስድብ ያዋርደኛል ለምን ይሄን ሰው ገድዬ ልጁቷን አላገባትም ሀብቱንም እወርሳለው በማለት ከሰይጣኑ ጋር ተማክሮ አጎቱን ለመግደል ይወስናል ።

ከዛም ወደ አጎቱ ይሄድና «ያለ አቅሜ ነው ልጅቷን የጠየቅኩህ ሰዎች ሽማግሌ ላክ ብለዉኝ ነው ይቅርታ አድርግልኝ»በማለት ይጠይቀዋል። አስከትሎም«አጎቴ እባክህ አንድ ነገር ላማክርህ እፈልጋለው አንተ ባትረዳኝ እንኳን ቢያንስ ዋስ ከሆንከኝ እንዳቋቋምከኝ ነው። አንዳንድ ሀብታሞች ከሩቅ ሀገር ሸቀጥ እያመጡ በአካባቢው ላሉ አነስተኛ ነጋዴዎች በዱቤ የሚሰጡ ስላሉ ከነሱ ጋር የዱቤ እቃ ወስጄ ልሰራ አስቢያለው እና እባክህ ተባበረኝ ። አንተ እያለህ ማንስ ዋስ ይሆነኛል» ሲለው አጎቱ እሺታውን ገለፀ።

በዚህ ሰአት ነጋዴዎችን አብረው ሄደው ለማነጋገር በምሽት ወደ ነገዴዎች መንደር እየሄዱ እያሉ ሰው በማይደርስበት ሰዋራ ስፍራ ሲደርሱ አጎቱን በስለት በመውጋት ገድሎ አስክሬኑን ጥሎ ወደ ቤቱ ይመለሳል ።የሰራውን ሰርቶ ካበቃ ቡሀላ «አጎቴ በምሽት ወጥቶ ቀረ ምን አጋጠመው ይሆን»በማለት ያስወራል በማግስቱ «ኡኡ ያገር ያለህ አጎቴ ጠፋብኝ አፋልጉኝ» ሲል ኡኡታውን የሰማው ሁሉ ሲያፈላልጉ በሰዋራ ስፍራ ተገድሎ ያገኙታል።

ገዳይ አቧራ ላይ እየተንከባለለ አጎቴን አጣሁኝ እያለ ሲያለቅስ የአካባቢው ሰዎች ባላዩት በሰፈራቸው ነው ሞቶ የተገኘው ወንጀለኛውን አምጡ ተብለው ይያዛሉ ።
«እኛ አላየንም» ቢሉም የሚሰማቸው ያጣሉ። «ከሆነም ካሳ እንክፈል እንጂ ገዳዩን ማግኘት አልቻልንም» ሲሉ ልጁ አልፈልግም የአጎቴን ገዳይ ነው የምፈልገው ካሳ አልቀበልም በማለት አስቸገረ።

በኑ እስራኤሎች ግራ ሲገባቸው ወደ ነብዩላህ ሙሳ አለሂ ሰላም ዘንድ በመሄድ«በማናቀው ነገር ተቸግረናልና መፍትሄውን ከአላህ ዘንድ ይጠይቁልን»አሏቸው።ነብዩላህ ሙሳ መልስ ያገኙላቸው ምላሽ በቁርአን ውስጥ በምዕራፍ 2 አንቀፅ 67 እስከ 73 ድረስ በቁርአን ላይ ተጠቅሶ እናገኘዋለን ። እሱም አንዲት ላም ገዝታችሁ ጊደሯን አርዳችሁ በከፊል ስጋዋ የተገደለውን ሰው በድን ምቱት ከሞተበት ተነስቶ ማን እንደገደለው ይናገራል የሚል ነበር።

የተባለችዋን ጊደር ፈልገው እና አፈላልገው አገኟት ።ጊደሯ ከላይ የተጠቀሰው ልጅ ጊደር ነበረች።እናም በኒ እስራኤሎች እንግዛህ ብለው ሲጠይቁት አውቆ አልሸጥም ይላቸዋል። ለምን መግዛት ያለብን ያንተን ጊደር ስለሆነ ነው? ሲሉ ዋጋዋን የምትችሉት አይመስለኝም አላቸው። ስንት ነው የምትሸጣት አሉ«ዋጋዋ ጊደሯ ታርዳ ቆዳዋ እንደ ማዳበሪያ ተሰፍቶ በሙሉ ወርቅ ተሰፍሮ ነው»አላቸው «ሞኝ ነህ እንዴ በዚህ ዋጋ ማን ነው የሚገዛህ?ማንስ ሲሸጥ አይተሀል»ቢሉት «እኔ መች ግዙኝ ብዬ ለመንኳቹ ከፈለጋቹ ግዙኝ ካልፈለጋቹ ተውት »ብሎ ኮራባቸው ። እንዳይተዋትም ተቸገሩ እንዳይገዙትም ዋጋዋ ከበዳቸው ሁኔታውን ለነብዩላህ ሙሳ አለሂ ሰላም ነገሯቸው ....

ይቀጥላል....

https://t.me/tewihd/
165 viewsedited  05:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 09:09:12 #የላሟ እና የአላህ ፈሪው ልጅ ታሪክ

ነብዩላህ ሙሳ አለሂ ሰላም ለበኒ እስራኤል ተልከው ኦሪትን ከመቀበላቸው በፊት አንድ አላህን የሚፈራ እና እናቱን የሚካድም ልጅ ነበር ።የሚተዳደርበት ሀብትና ንብረት ስላልነበረው በየቀኑ ሶስት ዲናር እንጨት እየሸጠ ነበር እናቱን የሚካድመው። ከሚያገኛት ሶስት ዲናር 1/3 ኛውን ለአቅመ ደካማ ምንም መስራት ለማይችሉ በቀን አንድ አንድ ዲናር፣ በወር 30 ዲናር ሰደቃ ይሰጥ ነበር።

እዚህ ጋር አንድ ነገር እንይ ይህ ወጣት ከሚያገኛት አነስተኛ ገቢ 1/3 ኛውን ሰደቃ መስጠት መቻሉን ስናይ እኛስ በቀን አንድ ብር ቀርቶ በወር ፣በሳምንት እንኳን ለእናቴ ለአባቴ ሶደቃ ብለን የማንሰጥ እንዲሁም የቤተሰብ ችግረኛን እንኳን ዙረን የማናይ ሆነን በአጠቃላይ ለዱንያ ፍቅር ምን ያህል ቦታ የሰጠን መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል ። እዚህ ጋር ሀቂቃ ቆም ብለን እራሳችንን እንፈትሽ ። ወደ ነበርንበት ታሪክ ስንመለስ

ወጣቱ ለሊቱን ቢሆን እንደ ቀን ውሎውን ለ3 በመክፈል 1/3 ኛው አላህን የሚገዛበት ሲሆን ቀሪው እናቱን የሚካድምበትና የሚያርፍበት ሰአት ነበር። በዚህ ላይ ሳለ የሚሸጠው እንጨት ተወዶ ሶስት ዲናር ይሸጥ የነበረውን ስድስት ዲናር ሽጦ ወደ እናቱ ሲመጣ ሁሉን ነገር ለእናቱ ያማክር ስለነበር እስከዛሬ ሶስት ዲናር እሸጠው የነበረውን እንጨት የሚገዙኝ ሰዎች እጥፍ አድርገው በስድስት ዲናር ስለገዙኝ ሶስቱን ዲናር ምን ላድርገው ብሎ እናቱን ያማክራታል ።

እናቱ አላህን የምትፈራ ብልህና አዋቂ ስለነበረች "እንደዚህ ከሆነ ያንተ ስራ ከእጅ ወደ አፍ ነው ታመህ እንኳን ብትተኛ ምንም የምንሸጠው የምንለውጠው ነገር የለም ። ጊደር ግዛበት ምን አልባት አላህ ካለ ጊደሯ ብትወልድልን ወተት እና ቂቤ ልናገኝ እንችላለን ።ከቸገረንም እንሸጣታለን» ብለው እናት ልጃቸውን ይመክራሉ ።ልጅም የእናቱን ምክር በመቀበል በሶስት ዲናር አንዲት ጊደር ገዝቶ ይመጣል።

ከዛም ጊደሯን ሲጠብቅ ከዋለ ለእናቱም ሆነ ለራሱ ለሚስኪንም የሚሰጠው ሰደቃ እንደሚቋረጥ በተረዳ ጊዜ ይሄኔ ጊደሯን ሰው ወደሌለበት ጫካ ወስዶ ድምፁን ከፍ አድርጎ «ያአላህ» እያለ ለሶስት ጊዜ ተጣራ ከዚያም «ይህቺን ጊደር የሚጠብቅልኝ አጣው ለሰው ብሰጣት እንዳንተ የማምነው የለም ይህቺን ጊደር ጠብቅልኝ በፈለኩ ጊዜ ትሰጠኛለህ ጉዳት እንዳይደርስባት እንደ ምትጠብቅልኝ አልጠራጠርም» ካለ ቡሃላ «ሰማኸኝ»? «አዎ ሰምቼሀለው» በማለት ለራሱ ለጥሪው ምላሽ ከሰጠ ቡሃላ ጊደሯን ጫካ ወስጥ ትቶ እንጨቱን ተሸክሞ ወደ ቋሚ ስራው ይመለሳል

ከጥቂት ዘመን ቡሃላ እናቱ በሞት ሲለዩት ሚስት አግብቶ በትዳር እየኖረም ቢሆን በዛው እንጨት በመሸጥ ነበር የሚተዳደረው በዚህ ላይ እያለ እንደሚሞትና ወደ አኼራ እንደሚሄድ ህልም አይቶ ስለነበር ልጅ ልትወልድለት ፅንስ ለፀነሰቸው ባለቤቱ እንዲህ በማለት ኑዛዜ ይነግራታል ።

« እኔ የተረገዘውን ልጄን ለማየት አልታደልኩም እና ልጁ ከተወለደና ካደገ አባቴ ምን የተወልኝ ነገር አለ ካለ በእንደዚህ ጫካ ውስጥ ሄዶ ረከአተይን ለአላህ ሰግዶ ይጣራ አላህን ከተጣራ ቡሃላ « አባቴ የሰጠህን አደራ ስጠኝ ፥ ይበለው። በአደራ መልክ ለአላህ የሰጠሁለት ጊደር አለች እና አላህ ይሰጠዋል ይላታል።

ሚስቱም ብትሆን እንደ ባለቤቷ በአላህ ላይ ጠንካራ ተወኩል ስለነበራት በሰማቸው ነገር ሳትጠራጠር እሺ በማለት ትቆያለች። ልጅም ቢሆን ተወልዶ የአባቱን ስራ በመቀጠል እንጨት እየሸጠ እናቱን በመካደም ላይ ሳለ አንድ ቀን ለእናቱ «አባቴን በህይወት ባላገኘውም ለማስታወሻ የሚሆን ምንም ጥሎልኝ የሄደው የለም?» ብሎ ይጠይቃታል። እስከዚህ ሰአት ደረስ ረስታው ስለነበር አባቱ የነገራት ኑዛዜ ትዝ አላት እና «የልጄ ማስታወሻ ይሆናል ብሎ አባትህ ተናዞ ነው የሞተው ሁለት ረከአ ሰላት ለአላህ ሰግደህ ስትጨርስ ያአለህ ብለህ 3 ጊዜ ከተጣራህ ቡሃላ አባቴ የሰጠህን አደራ ብለህ ጠይቀው» አለችው

ልጁም እናቱ እንደነገረችው ወደ ተባለው ተራራ ሄዶ ........

........ ይቀጥላል

https://t.me/tewihd/
192 views06:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 13:40:05 የቂያማ ቀን ቋሚ የችሎት ስርዓት

ለቂያማ ቀን በሚዘጋጀው የፍርድ አደባባይ ላይ ከመቆማችን በፊት ቦታው የሚኖረውን ድባብ በጥቂቱ ...

ያኔ ፋይሎች ሁሉ ሚስጢራዊ አይደሉም

ﻭﻧُﺨﺮِﺝُ ﻟَﻪُ ﻳَﻮْﻡَ ﺍﻟﻘِﻴﺎﻣَﺔِ ﻛِﺘﺎﺑﺎ ﻳَﻠﻘﺎﻩُ ﻣَﻨْﺸُﻮﺭًﺍ

"በዕለተ ትንሳኤ ተዘርግቶ የሚያገኘውን መዝገብ እናቀርብለታለን"

ወደ ችሎቱ ቦታ ለመታደም የሚጓዙ ፍጡራን ጥብቅ ቁጥጥር
ይደረግባቸዋል

ﻭَﺟَﺎﺀﺕْ ﻛُﻞُّ ﻧَﻔْﺲٍ ﻣَّﻌَﻬَﺎ ﺳَﺎﺋِﻖٌ ﻭَﺷَﻬِﻴﺪٌ

"እያንዳንዷ ነፍስ ፣ አንደኛዋ ነጂና ሌላኛዋ መስካሪ በሆኑ ሁለት መልአክት ታጅባ ትመጣለች"

አድሎ የማይታሰብ ነው

"ﻭَﻣَﺎ ﺃَﻧَﺎ ﺑِﻈَﻠَّﺎﻡٍ ﻟِّﻠْﻌَﺒِﻴﺪِ "

" እኔም ለባሮቼ ፈፅሞ በዳይ አይደለሁም "

ተከላካይ ጠበቃ የለህም

ﺍﻗْﺮَﺃْ ﻛِﺘَﺎﺑَﻚَ ﻛَﻔَﻰٰ ﺑِﻨَﻔْﺴِﻚَ ﺍﻟْﻴَﻮْﻡَ ﻋَﻠَﻴْﻚَ ﺣَﺴِﻴﺒًﺎ

"የስራ መዝገብህን አንብብ። ዛሬ ራስህን ለመመርመር አንተው
በቂ ነህ።" (ይባላልም)።

ጉቦ ፣ አስታራቂ ዘመድ እና ባለስልጣን ከቦታው ዘር ይላሉ ማለት ፈፅሞ አይታሰብም።

ﻳَﻮْﻡَ ﻻ ﻳَﻨﻔَﻊُ ﻣَﺎﻝٌ ﻭَﻻ ﺑَﻨُﻮﻥَ

" ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን"

የስሞች መመሳሰል አይከሰትም

ﻭَﻣَﺎ ﻛَﺎﻥَ ﺭَﺑُّﻚَ ﻧَﺴِﻴًّﺎ

"ጌታህ የሚረሳም አይደደለም።"

ፍርድን በእጅ መቀበል

ﻓَﺄَﻣَّﺎ ﻣَﻦْ ﺃُﻭﺗِﻲَ ﻛِﺘَﺎﺑَﻪُ ﺑِﻴَﻤِﻴﻨِﻪِ ﻓَﻴَﻘُﻮﻝُ ﻫَﺎﺅُﻡُ ﺍﻗْﺮَﺅُﻭﺍ ﻛِﺘَﺎﺑِﻴﻪ
ْ
" የስራ መዝገቡን በቀኝ እጁ የተቀበለ ሰው እንዲህ ይላል ያዙ፣ የስራ መዝገቤን አንብቡልኝ "

በአካል በሌሉበት ፍርድ የለም። ከችሎቱ አደባባይ
የሚያመልጥም ሆነ የሚቀር የለም።

ﻭَﺇِﻥْ ﻛُﻞٌّ ﻟَﻤَّﺎ ﺟَﻤِﻴﻊٌ ﻟَﺪَﻳْﻨَﺎ ﻣُﺤْﻀَﺮُﻭﻥَ "

" ሁሉም ከእኛ ዘንድ ለፍርድ ይሰበባሉ"

ፍርዱ አይሻርም፤ይግባይኝም የለው

ﻣَﺎ ﻳُﺒَﺪَّﻝُ ﺍﻟْﻘَﻮْﻝُ ﻟَﺪَﻱَّ

" ከኔ ዘንድ ቃሉ (የተላለፈው ፍርድ) አይለወጥም።"

ፍፁም የሆነ ፍትህ ሰፍኗል። የእዝነትና የምህረት ወቅት
አክትሟል። ብይኑ ተላልፏል። ከእንግዲህ የሚለወጥ ነገር የለም ነው መልዕክቱ።

በሀሰት የሚመሰክሩ ህሊና ቢስ ሰዎች በጭራሽ የሉም

ﻳَﻮْﻡَ ﺗَﺸْﻬَﺪُ ﻋَﻠَﻴْﻬِﻢْ ﺃَﻟْﺴِﻨَﺘُﻬُﻢْ ﻭَﺃَﻳْﺪِﻳﻬِﻢْ ﻭَﺃَﺭْﺟُﻠُﻬُﻢ ﺑِﻤَﺎ ﻛَﺎﻧُﻮﺍ ﻳَﻌْﻤَﻠُﻮﻥَ

" ምላሶቻቸው፣ እጆቻቸውና እግሮቻቸው ይሠሩት በነበረው ሥራ ( እኩይ) በሚመሰክሩባቸው ቀን ( ከባድ ቅጣት አላቸው) "

የተረሱ ፋይሎች ፈፅሞ አይኖሩም

" ﻳَﻮْﻡَ ﻳَﺒْﻌَﺜُﻬُﻢُ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﺟَﻤِﻴﻌًﺎ ﻓَﻴُﻨَﺒِّﺌُﻬُﻢْ ﺑِﻤَﺎ ﻋَﻤِﻠُﻮﺍ ۚ ﺃَﺣْﺼَﺎﻩُ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻭَﻧَﺴُﻮﻩُ ۚ ﻭَﺍﻟﻠَّﻪُ ﻋَﻠَﻰٰ ﻛُﻞِّ ﺷَﻲْﺀٍ ﺷﻬﻴﺪ "

" አላህ ሁሉንም ዳግም በሚቀሰቅሳቸውና እርሱ መዝገብ ውስጥ ያሰፈረውን እነርሱ ግን የዘነጉትን ተግባራቸውን
በሚነግራቸው ቀን። አላህ ሁሉንም ነገር አዋቂ ነው።"

ፍፁም ትክክል የሆነ የስራ ሚዛን ይቀርባል

ﻭَﻧَﻀَﻊُ ﺍﻟْﻤَﻮَﺍﺯِﻳﻦَ ﺍﻟْﻘِﺴْﻂَ ﻟِﻴَﻮْﻡِ ﺍﻟْﻘِﻴَﺎﻣَﺔِ ﻓَﻠَﺎ ﺗُﻈْﻠَﻢُ ﻧَﻔْﺲٌ ﺷَﻴْﺌًﺎ ﻭَﺇِﻥ ﻛَﺎﻥَ ﻣِﺜْﻘَﺎﻝَ ﺣَﺒَّﺔٍ ﻣِّﻦْ ﺧَﺮْﺩَﻝٍ ﺃَﺗَﻴْﻨَﺎ ﺑِﻬَﺎ ﻭَﻛَﻔَﻰٰ ﺑِﻨَﺎ ﺣَﺎﺳﺒﻴﻦ

" በትንሳኤ ቀን ፍትሃዊ ሚዛናችንን እናቆማለን። በመሆኑም ነፍስ ሁሉ ቅንጣት በደል አይደርስባትም። የሰነፋጭ ቅንጣት የምታክል ሥራ እንኳ ሳትቀር ለሚዛን እናቀርባታለን። ተቆጣጣሪነት በኛ በቃ "

መቆም ከማይቀርልን የችሎት አደባባይ ላይ ከመቆማችን በፊት
የስራ መዝገባችንን ለማሳመር እንትጋ። ጌታየ እዝነትህን እንሻለን ። የተኮረጀ ከከፊል Edition ጋ

@Tewihd
222 views10:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 12:58:26 ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች ከዛሬ ጀምሮ ከነብዩላህ ኢብራሂም ቤተሰብ ጀምሮ የነበሩ ድንቅ የአላህ ባሮችን ማንነትና ተአምር የሚያሳይ ተከታታይ የሆነ ታሪክ በቻናላችን ይዘንላቹ እንቀርባለን !!!! ኢንሻ አላህ በተቻለን አቅም በቀን ሁለቴ ጥዋትና ማታ የምንለቅ ይሆናል ሀቂቃ ታሪኩ በጣም አስተማሪና ወደ ህይወታችን አምጥተን ልንሰራበት የሚገባ ነው እንዲሁም በማንበብ ብዙ የማናቃቸውን ነገሮች እናውቃለን…
200 viewsedited  09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ