2023-02-04 16:52:48
አደራ!
ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ በሁሉም ዘርፎች ላይ ያሏትን ልዩነቶች አስማምታ ዘመንን የተሻገረች ኃያል ሀገር ነች። በዘመኖቿ የሚፈጠሩ ችግሮችንም በጥበብ እየፈታች ከእኛ ደርሳለች።
እኛ በቆምንበት ጀንበር እየተፈጠሩ ያሉ ጥፋቶች በታሪክ ተወቃሽ ከመሆን የማያድኑን ናቸው። በኃይማኖታችን ተዋደንና ተከባብረን የኖርንባቸው የልጅነት ዘመኖች በጣም ሩቅ እስኪመስሉን ድረስ አስፈሪ ወቅት ላይ ደርሰናል።
መንግስት በምን ዐይነት መልኩ የኃይማኖት አባቶችን መንካትም መግፋትም የለበትም ይህ ትልቅ ጥፋት ነው። እስካሁንም የተፈጸመው ከበቂ በላይ የሆነ ጥፋት በይቅርታ ታልፎ እንጂ የማያስቆጣው አካል ሳይኖር ቀርቶ አይደለም። የኃይማኖት አባቶች ምክራቸውም ጸሎታቸውም የታፈረና ትልቅ ነው።
ትልቅን ማክበርም ሆነ ለትልልቆች መታዘዝ ከሀይማኖታዊ አውድ ውጪ እንኳ ብናየው አንዱ የኢትዮጵያዊነት መገለጫ ነው።
መንግስት ሁሉንም ኃይማኖቶች በአንድ ዐይን የማየት ግዴታ አለበት። ህጋዊ የሆኑ ተቋሞችንም ህገመንግስታዊ ከለላ የመስጠት ስራ ከመንግስት ተግባሮች አንዱ ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እና ተከታዮቿ ላይ የተጋረጠውን ስጋት በማጥራት ወደ ቀድሞ ሰላሟ መመለስ ሀገርን በቀደመ ሰላሙ እንደ ማጽናት ነው። በኃይል እና በጫና የሚፈጠሩ የለውጥ ውጤቶች ማመን በተለይ በዚህ ዘመን በፍጹም ተቀባይነት የሌላቸው ናቸው። ይህ ሁከት እና አስጨናቂ ወቅት በሌሎች ኃይማኖቶችም ላይ እንዳይደገም መንግስት ኃላፊነቱን በጥንቃቄ መወጣት አለበት።
ኃይማኖታዊ ጉዳዮች በቀላል መታየት የሌለባቸው፥ ትልቅ ትኩረትን እና ጥበባዊ ተግባርን የሚፈልጉ በመሆናቸው ውሳኔዎች ሁሉ እግዚአብሔርን በመፍራትና በጨዋ ደንብ መሆን አለበት። ለመንግስትም ከአደራ ጋ የማቀርበው ጥያቅ ይህ ነው።
ያሬድ ነጉ
202 viewsedited 13:52