Get Mystery Box with random crypto!

ተረት ተረት

የቴሌግራም ቻናል አርማ teretteretgroup — ተረት ተረት
የቴሌግራም ቻናል አርማ teretteretgroup — ተረት ተረት
የሰርጥ አድራሻ: @teretteretgroup
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.04K
የሰርጥ መግለጫ

ጣፋጭ ተረት ተረቶችን ለልጆች እንዲሁም ለወላጆች አስተማሪ ልጆችን በተመለከተ ስለ ጤና እና አስተዳደግ ጠቃሚ ፅሁፎችን እናቀርባለን ።
ለሃሳብ አስተያየቶች በ @TeretTeret_Admin አድርሱን

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 07:15:13
ሰላም ፍቅር ለሀገራችን
175 views04:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 07:24:36
441 views04:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 07:21:01ክብር ዶክተር አርቲስት ለማ ጉያ የስዕል ስራዎች በጥቂቱ
440 views04:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 07:14:09 ሰላም ልጆች
ክብር ዶክተር አርቲስት ለማ ጉያ የተባሉትን ሰው ታውቃላችሁ?

እስኪ ለማታውቁ ላስተዋውቃችሁ።

ከአዲስ አበባ 45 ኪሎ ሜትር ርቃ ከምትገኘው ደብረ ዘይት(ቢሾፍቱ) ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ፣ ዶሎ በምትባል ቀበሌ በ1921 ዓም ተወለዱ።

ሠዓሊና ቀራፂው ለማ ጉያ የሸክላ ጥበብ ባለሞያ የነበሩትን እናታቸውን ወሮ ማሬ ጎበናን በማየት የቅርፃ ቅርፅ እና የሥዕል ዝንባሌ ይዘው በእረኝነት አደጉ።

በ15ዓመታቸው ደብረ ዘይት ላይ በተከፈተው የአፄ ልብነ ድንግል ት/ቤት ገብተው መማር ጀመሩ።

እስከ ሰባተኛ ክፍል ከተማሩ በኋላ በተሳቡበት ሥነ ጥበቡ ለመሠማራት ወደ ወላጆቻቸው ተመለሱ። ብዙም ሳይቆዩ በመምህርነት ለመሠልጠን ኮተቤ ማሠልጠኛ ቢገቡም፣ ከልባቸው ጋር አልገጠመምና ወዲያውኑ አቆሙት። ወደ ቀዬአቸው ተመልሰው፣ የሥነጥበቡንና የቅርፃ ቅርፅ ሥራቸውን አጠበቁ።

በደብረ ዘይትና አካባቢው በሠዓሊነታቸውና በቀራፂነታቸው ታውቀው ሣቆዩ፣ ንጉሠ ነገሥት አፄ ኃይለሥላሴ በከተማቸው የሚገኙበትን አጋጣሚ ጠብቀው የሥዕል ትዕይንት አዘጋጅተው እንዲመለከቱላቸው ጋበዟቸው።

ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ለስዕል ሥራዎች ልዩ ፍላጎት የነበራቸው በመኾኑ፣ የሥዕል ትዕይንታቸውን በሚገባ ተመልክተው በማድነቅ፣ ምን እንዲያደርጉለት እንደሚፈልጉ ወጣቱን ለማ ጉያን ጠየቋቸው።

ለማ፣ “የአየር ኃይሉ ሠራዊት አባል በመኾን፣ አየር ማብረርን ፣” እንደሚፈልጉ ነገሯቸው።
ወድያውኑ በደብረ ዘይቱ የአየርኃይል መኰንኖች ማሠልጠኛ እንዲማሩ አዘዙላቸው። በዚህም አጋጣሚ የአየርኃይል ወታደር ኾኑ።

በአየር ኃይሉ ግቢም የሥነ ጥበብ ሥራዎቻቸውን መሥራት ቀጥለው ነበርና አሥመራ ላይ በነበረው የጣሊያኖች የሥዕል ት/ቤት ገብተው የመማር ዕድል አግኝተው ለአጭር ጊዜ ሠለጠኑ።

በውትድርናው የሻምበልነት ማዕረግ ይዘው፣ እስከ ሠላሳ ሦስት ዓመታቸው፣ ለአስርት ዓመታት ሲያገለግሉ ቆይተው፣ አኹንም በጥበቡ ሥራ ብቻ ለመኖር በመፈለግ ከአየር ኃይል ተሰናብተው ወጡ።

ከዚያን ጊዜ ጀምረው በቀረው ዘመናቸው ኹሉ ሥነ ጥበቡን ሕይወታቸው አድርገው ኖረዋል።

ለማ ጉያ የአፍሪካ መሪዎችን ምሥል በመሥራት ለየ ራሳቸው በማበርከት ሥራዎቻቸውን በመላው የአፍሪካ አብያተ መንግሥታት አኑረዋል።
በቢሾፍቱ መኖርያቸው በስማቸው የተጠራ የግል ቤተ ሥዕል ከፍተዋል። ለብዙ ልጆች የእጅ መፍቻና መሠረታዊ የንድፍ ጥበብ መማርያ የኾነ
ያለ አስተማሪ የሥዕል መማርያ መጽሐፍ” አሳትመዋል።

ሠዓሊና ቀራፂ ሻምበል ለማ ጉያ የሦስት ሴቶችና የኹለት ወንዶች ልጆች አባት ነበሩ።
አርቲስት ለማ ጉያ ባጋጠማቸው ሕመም ምክንያት በአገር ውስጥ እና በውጪ በህክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ በ92 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
@TeretTeretChannel
433 views04:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 07:13:52
412 views04:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 23:00:03 ውቢት

በአንድ ትንሽ ከተማ ውስጥ የምትኖር ውቢት የተባለች ልጅ ነበረች ።
ውቢት በከተማው  በውበቷ እንደሷ ያለ ባለመኖሩ  የማያውቃትና የማያደንቃት ሰው አልነበረም ።

የከተማው ሰው ሁሉ ውበት ከውቢት ውጪ የትም የለም እስከማለት ደረሰ።

ታዲያ ውቢት ምን ውጫዊ መልኳ ያማረ ቢሆንም ፀባይዋ አስቸጋሪ እና የማይጨበጥ ነበር።

ከሷ ወዲያ ውብ እንደሌለ በማመን በሰዎች ላይ ትኮራ እና ሰዎችን በመናቅ ታመናጭቅ ነበር ።

ምንም አይነት ጓደኛም አልነበራትም ምክንያቱም ጓደኞቿን የምትንቅና ከሷ የበታች ሆነው ትዕዛዟን እንዲፈፅሙ ስለምትፈልግ የቀረቧት ሁሉ ራቋት።

በዚህም የተነሳ ብቸኝነት እየተሰማትና ደስታን እያጣች ሄደች።

የውቢት አባት ከሀገር ሀገር የሚዞር ነጋዴ ነበር ። የውቢት ፀባይ እንዲህ መሆንም በጣም ያሳስበው ነበር።

እሱ በሚሄድባቸው ሀገራት ከውቢት የሚበልጡ ቆንጆዎችን አይቷል።
በአጋጣሚም በስራ ምክንያት ያነጋገራቸውም ነበሩ ግን ፍፁም ትሁቶች ነበሩ።

እሱ እንደገመተው እነውቢት የሚኖሩበት ከተማ ትንሽ በመሆኗ ውቢትን ብቸኛዋ ቆንጆ እንድትሆን አስተዋፅኦ አድርጓል።
የከተማው ሰው ሁሉ ከውቢት ውጭ ቆንጆ ውብ የለም በማለቱ ልጁ እንድትኩራራና ሌሎችን በመናቅ የማይሆን ፀባይ እንዲኖራት ምክንያት ሆኗል።

በዚህ የተነሳ አባቷ አስቦ አስቦ አንድ ውሳኔ ላይ ደረሰ።
ይኽውም ውቢትን ለንግድ በሚሄድባቸው ሀገራት ይዟት በመዞር ያልተረዳችውን እንድታይ ወሰነ ።

ውቢት አባቷ ለሽርሽር ወደሌላ ቦታ እንደሚወስዳት በነገራት ጊዜ በደስታ ተፍነከነከች።
እንደተለመደው በሌሎች ከተሞች ውበቷ ሊወደስ መሆኑን በማሰብ ደስስስ ተሰኘች።
ለነገ ጉዟቸውም አሉኝ ያለቻቸውን ቆንጆ ቆንጆ ልብሶች በሻንጣዋ ያዘች።

በቀጣዩም ቀን ለጉዞ ተነሱ።

ጉዟቸው አስደሳች የነበረ ቢሆንም ለውቢት ግን ግራ የሚያጋባ ነበር ። እንደሚኖሩበት ከተማ ሰዎች ውበቷን ያደነቀ አላጋጠማትም በተዘዋወሩባቸው ቦታዎች ብዙ ቆንጆ ሰዎችን ለማየት ቻለች።
እነሱ ግን ከሰዎች ጋር ተግባቢና ሳቂታዎች ደስተኞችም ጭምር መሆናቸውን ተመለከተች።
በዚህ ጊዜ አንድ ያልገባት ነገር እንዳለ ጠረጠረች።

በቀጣይ ቀናትም አባቷ የሚያውቃቸው ደንበኞቹ ጋር ይዘት ሄደ ከሁለቱ ጋርም አስተዋወቃት ሴቶቹ እጅግ ውብና ዘመናዊ ነበሩ።  በዛውም ልክ ከማንኛውም ሰው ጋር የሚግባቡና በመከባበር የሚያወሩ ደስተኞችም ጭምር ሆነው አገኘቻቸው።

በዚህ ጊዜ ምን መልክ ቢያምር የውስጥ ውበት ከሌለ ሁሉም ነገር ከንቱ እንደሆነ ተረዳች።
ጎደኞቿ ላይ ታሳይ የነበረው ነገርን ባሰበች ጊዜ ሀፍረት ተሰማት።
የዚህ ጊዜ አባቷ አብዝቶ የሚለው ጥቅስ ትዝ አላት
"መፅሐፍን በሽፍኑ አታድንቀው"

'ለካንስ ውበት ውስጥ ነው ያለው እውቀት ፣ደግነት ፣ ትህትና፣ ፍቅር እነዚህ ናቸው ውበት ' ብላ በማሰብ ከአንባቷ ጋር በነበራት ጉዞ የህይወቷን ትልቅ ስህተት ለማረም ቻለች።

በሂደትም ያጣቻቸውን ጓደኞቿን በጥሩ ባህሪዋ ለመመለስ ቻለች።
ተረቴን መልሱ አፌን በዳቦ አብሱ
@TeretTeretChannel
1.0K views20:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 22:59:30
805 views19:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 23:38:11 ሰላም ልጆች እነሆ ዛሬ
ደብረ ታቦር ወይንም የቡሄ!  ትርጉምን በጥቂቱ
ቡሄ በመላው ሀገራችን በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን የሚከበር በዓል ነው ።

፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከምታከብራቸው ዓቢይ (ዋና) በዓላት አንዱ ይህ 'ደብረ ታቦር' የምትለው የቡሄ በዓል ነው።

ደብረ ታቦር በግዕዝ የታቦር ተራራ ማለት ነው፡፡

የታቦር ተራራ የሚገኘው አሁን ፍልስጥኤም ተብሎ በሚጠራው ሀገር ነው፡፡

ደብረ ታቦር ወይንም የታቦር ተራራ ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስት ደቀመዛሙርቱን ይዞ ወደ ተራራው የወጣበትና ፊቱ እንደ ፀሐይ የበራበት ልብሱም እንደብርሃን ነጭ የሆነበት ቦታ ነው፡፡ ይህ ቦታ ጌታ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ተራራ ነው።

በመፅሐፍ ቅዱስ የማቴዎስ ወንገል ምዕራፍ ፲፯፦ ቁጥር ፩ እስከ ፭ " እንደሚለው
" ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው።
በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።
ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ።
እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው።

"በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።"

ደብረ ታቦር በጥቂቱ ይህ ሲሆን በአገራችን የክረምቱ አፈና ተወግዶ የብርሃን ወገግታ የሚታየውም በዚህ በዓል አካባቢ ስለሆነ ይቺ ዕለት 'ቡሄ' የሚለውን ስያሜ አገኘች።
ቡሄ ማለት ገላጣ፣ የተገለጠ ማለት ነው፡፡
በገጠርም ሆነ በየከተማው ልጆች ጅራፋቸውን ገምደው ሲያጮሁ ይሰነብታሉ።
እናቶችም ለበዓሉ ዝግጅት ስንዴ ሲለቅሙ፣ ሲፈትጉ፣ ሲፈጩ ይሰነብታሉ።

ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን በገለጠበት ዕለት ጊዜው ምሽት ነበር፡፡
እረኞችም ከብርሃኑ የተነሣ እየተገረሙና እየተደነቁ ወደ ቤት አልተመለሱም ነበር፡፡ የልጆቹን መዘግየት ያዩ ወላጆች ችቦ አብርተውና ዳቦ ይዘው ፍለጋ ወጡ፡፡
ታዲያ ያንን ማስታወሻ «ቡሄ» ለሚሉ ልጆች ሙልሙል ዳቦ የሚሰጠውና ችቦ በማብራት በዓሉን የምናከብረው ከዚህ በመነሣት ነው፡፡

መልካም በዓል
1.3K views20:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 23:37:50
969 views20:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ