Get Mystery Box with random crypto!

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

የቴሌግራም ቻናል አርማ terbinos — ❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️
የቴሌግራም ቻናል አርማ terbinos — ❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️
የሰርጥ አድራሻ: @terbinos
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.69K
የሰርጥ መግለጫ

« ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ ወይሰመይ ስሙ አማኑኤል ዘበ ትርጓሜሁ እግዚአብሔር ምስሌነ »
••••
« ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ሰሙንም አማኑኤል ትለዋለች ትርጉሙም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ
••••
ቻናላችንን ይቀላቀሉ ዘንድ ግብዣችን ነው‼️
-------------------------------------------

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-05 21:52:58 ቅዱስ ባለወልድ - እግዚአብሔር ወልድ ከክፉ ሁሉ ይጠብቃችሁ ይጠብቀን አሜን
••
ባለወልድ ፤ (በዓለ ወልድ) ትርጉም ጌታችን በድንግል ማርያም ማሕፀን ተፀንሶ መወለዱንና ሙቶ መነሣቱን የሚያሳስብ በዓል ሲሆን ወር በገባ በ፳፱ ቀን የሚከበር በዓል ነው።
••
ቅዱስ ባለወልድ አባቴ
••
የጠፋውን ልትፈልግ የመጣህ #ወልድ አቤቱ ጌታዬና አምላኬ የነፍስና የሥጋ ፈጣሪ እንደመሆንህ " በከንቱ የጠፋውን ልጄን #በደሜ ዋጅቼ አግኝቼዋለሁና እናንተ የመላእክት ነገዶች ሁሉ #ደስ_ይበላችሁ" በላቸው። እነርሱ ነገደ መላእክት በአንዱ በግ መገኘት ደስ ይሰኛሉ ብለህ በወንጌል ተናግረሃልና! የጠፋሁም እኔ ነበርኩኝ በመከራና በሕማም ፈለከኝ በሞትህም አገኘህኝ ወደ ቤቴም መለስከኝ።
••
አቤቱ ኃጢአትን ሁሉ ይቅር የምትል ይቅር ባይ ነህና በይቅርታህ መነሳነስ እርጨኝ ከበረዶም እነፃ ዘንድ ከኃጢአቴ #እጠበኝ። ኃጢአትን የሚያስተሠርይ በግዐ #መሥዋዕት አንተ ነህ። ስለ እኛ መከራን ለመቀበል በግፍ አደባባይ መታየት ፈቃድህ ሆነ። ይህ ሁሉ እንዲሆን አንተ አስቀድመህ ያዘጋጀኸው ነውና። የራቀውን የሚያቀርብበት የቀረበውን የሚያርቅበት #የአብ ቀኝ ክንዱ አንተ ነህና አቤቱ አምላኬ እግዚአብሔር #ወልድ ሆይ! ንብ የዱር አበቤችን ቀስሞ ማር እንደሚያዘጋጅ የጥበባት ሁሉ ፍሬ የሚሆን ፈራሂ መለኮትን በልቡና አሳድርብኝ። ከዓለም ላይ ጭለማን ያስወገድህ እውነተኛ ብርሃን አንተ ነህ። ከላይ በኪሩቤል ላይ ተቀምጠህ የውቅያኖስን ጥልቀነት ትመለከታለህ ስለዚህም ልዑልና የተመሰገነህ ነህ።
••
ከመስቀልህ ስር የሸለምከኝ #ውድ ስጦታህ እናትህ #ድንግል #ማርያም የኔ መሸሸግያ ፤ የኔ አምባ መጠግያ ፤ የኔ መማጸኛ ፤ ጌጤ ክብሬ ሞገሴ ያለችኝ ሀብቴ ገንዘቤ እርሱ ብቻ ናትና የመስቀልህን የአደራ #እናቴን ተደግፍያትና ተመርኩዣት ለዘለዓለም በእናትነት ፍቅሯ እንዳትለየኝ ምልጃዋን አምኜ እየተማጸንኳን እኖር ዘንድ ፍቀድልኝ። ምስጋና ሁሉ ውዳሴ ሁሉ አምልኮም ላንተ ይገባሃል ጌትነትና መንግሥትም ያንተ ናትና ለዘለዓለሙ አሜን።
•••
የዓለም ቤዛ የድንግል ማርያም ልጆች ቅዱስ ባለወልድ በያለንበት ይጠብቀን ፍቅር ሰላም አንድነትን ያድለን ምህረት ቸርነቱ አይለየን! አሜን
•••
https://www.facebook.com/terbinos
622 viewsየእኔ ሀብት, 18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 21:52:50
458 viewsየእኔ ሀብት, 18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 23:54:57 #አማኑኤል_ሆይ - ስለሚወጣው ስለሚገባውም ተመስገንልን
•••
ስምህን ሰምቶ ሞት ይደንግጥ ፤ ቀልያት ይሰንጠቁ ፤ ዲያቤሎስ ይረገጥ አንተ ሳትደክም ሁሉን ትሸከማለክ ፤ ዝም ሳትል ለሁሉ ታስባለክ ፤ ጠላት ግን አንተን መጥፎ አለክ
•••
" #የፍቅር ዓለት ፤ የሕይወት ራስ ፤ የጽድቅ መዝገብ ሆይ " አንተ በነፃ ሥጋህን ቆርሰህ ደምህን አፍሰክ የሁሉን #ኃጢአት ይቅር ትላለክ ፤ ጠላት ግን አንተን ኀጥአ አለክ " የድሆች አባት ፤ የፍትህ ቱንቢ ፤ የእውነት ማማ ሆይ " አንተ በዙፋንክ ለሁሉ በጽድቅ ትፈርዳለክ ፤
ጠላት ግን አንተን ግፈኞች ፍርድ አቆመክ
•••
6666 ግዜ በመንዶል አጥንትክ እስኪታይ እየተቀያየሩ ከበው ፤ #ግፍ_ግፍ_ገረፉክ ፤ ኀያላን ኩሪቤል ቀና ብለው እማያዩትን ውብ ፊትህን 120ግዜ በጭካኔ በድንጋይ #መቱክ ፤ #ተፋብክ #አፌዙብክ ፤ የተመሳቀለ እንጨት አሸከሙክመው 136ግዜ ገፍትረው ከመሬት ጣሉክ ፤ እየጎተቱ ወደ ጎለጎታ ወስደው ከነፍሰ ገዳዮች መሐል ሰቀሉክ #በመንግስተ_ሰማይ የተመላለሱ እግሮች መስቀል ቀኖ ተቸነከሩ ፤ " አዳምን የፈጠሩ ቸር እጆች በመስቀል ቀኖ ተቸነከሩ " " ለአዳም እፍ ብለው ሕይወት የሰጡ መለኮታዊ ከንፈሮች ፤ የዝሆን #ሐሞት ተጋቱ " ወደ
ውኆች መሠረት ሊወርድ ፤ ኀይለኛውን ሊያስር ፤ ምርኮን ከጥልቁ ሊበዘብዝ ፤ ቤተክርስትያኑን በደሙ ሊዋጅ ፤ መሠዊያውንም ሊሰራ ፤ እንደሚታረድ በግ በዝምታ #ጎኑን_በጦር ተወግቶ ሕይወቱን ሰጠ ••• ኦ ክርስቶስ
•••
#አማኑኤል_ሆይ ሙሽራክ ተዋህዶ ትገዛልሀለች ፤ ሕዝብህም ይሰግዱልኻል ፤ ሕይወትህን ቤዛ አርገህ ከሞት ዋጅተኻቸዋልና የአብ የወልድ እና የመንፈስ ቅዱስ ሥም ከፀሐይ መውጫ ፤ እስከ ፀሐይ መጥለቅያ ፤ ለዘላለም #የተመሰገነ ይሁን
•••
የማይለወጠው ቅዱስ አማኑኤልን ግን ትምህክት አድርገን በኦርቶዶክሳዊነት አምድ እንቆማለን ።
ቅዱስ አማኑኤል አባቴ ሆይ ተመስገንልኝ ••• አማኑኤል ፍቅር የመንፈስ ቅዱስ አንድነት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን
•••
https://www.facebook.com/terbinos
683 viewsየእኔ ሀብት, 20:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 23:54:44
459 viewsየእኔ ሀብት, 20:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 21:03:26
ለሁሉም ጊዜ አለው የንፁሃን አምላክ አለ እግዚአብሔር ይፈርዳል
•••
አቤቱ የንስሐ እንባ ስጠኝ ፤
አቤቱ የጴጥሮስን እንባ ስጠኝ ፤
አቤቱ የፊቴን ጥቁረት የሚያጥብልኝ እንባ ስጠኝ፤
•••
ዛሬ በቄለም ወለጋ ለምለም ቀበሌ በተፈፀመ ጥቃት በርካታ ሰዎች ተጨፍጭፈዋል።
•••
https://www.facebook.com/terbinos
517 viewsየእኔ ሀብት, 18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 21:46:32
#መድኃኒዓለም አባቴ
•••
መድኃኒዓለም ማለት የአለም ሁሉ መድሃኒት ማለት ነዉ። ስጋዉን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ለኛ ሲል ህይወቱን የሰጠ
አባታችን ነው
•••
➥አሮንና ልጆቹን ለክህነት የመረጠ
➥ ኤልያስን በአዉሎ ነፋስ የነጠቀ
➥ እዮብን በባእድ ሀገር ከፍ ከፍ ያደረገ
➥ ሎጥን ከእሳት ያወጣ
➥ ለሳምሶን ሀይልን የሰጠ
➥ አዛርያን አናንያን ሚሳኤልን ከእሳት የታደገ
➥ ጥበብና ማስተዋልን ለሰለሞን የሰጠ
➥ ያዕቆብን
በመንገዱ የጠበቀ እና የባረከ
➥ እስራኤልን ከግብፅ ባርነት ያወጣ
➥ ለሙሴ ጽላት የሰጠ
➥ ለኪሩቤል ላይ የተቀመጠ ክብሩንም የገለጠ ስጦታዉ የማያልቅበት
•••
#ቸሩ_መድሃኒአለም ይክበር
ይመስገን አሜን /፫/
•••
➠ #መድኃኒአለም የገዢዎች ሁሉ ገዢ
➠ #መድኃኒአለም የነገስታት ሁሉ ንጉስ
➠ #መድኃኒአለም የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ ነዉ
➠ #መድኃኒዓለም ኃይልና ጉልበትን ታድሳለህ ቀና ቀና እንድንል ታደርጋለህ
መድኃኒዓለም መድኃኒታችን
•••
#መ ➠ መሃሪ ይቅር ባይ አምላክ
#ድ ➠ ድካሜን ተመልከት ስለዉ ተበርክኬ
#ኃ ➠ ኃያላት የማይችሉህ የኃያላን ኃያል
#ነ ➠ ነፍሴ ትልኃለች ጌታዬ ይረዳኛል
#አ ➠ አለምን ለማዳን መስቀል ላይ የዋለ
#ለ ➠ ለዘላለም ፍቅር ነህ ሁሌ የማትቀየር
#ም ➠ ምህረትህ የበዛ
•••
ቸሩ መድኃኒአለም በያላቹሁበት ይጠብቃችሁ ወጥቶ ከመቅረት ከድንገተኛ አደጋ ይጠብቃችሁ አሜን/፫/
•••
https://www.facebook.com/terbinos
ለሌሎች ሼር በማድረግ ይተባበሩ
700 viewsየእኔ ሀብት, 18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 17:30:19
#መሬት_ደም_አለቀሰች
•••
ከሰሞኑ ቤተክርስቲያናችን አንድ ትልቅ የፀሎት አባት አጥታለች። እኒህ አባት የኔታ ነብዬልዑል በትሩ ይባላሉ።
•••
ነዋሪነታቸው በደቡብ ጎንደር ዞን ስማዳ ወረዳ ሰኔ ግባ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ሲሆን በዚህ ቤተክርስቲያን ለበርካታ አመታት እንዳገለገሉ ነው የተነገረው።
•••
የኔታ ነብዬልዑል በትሩ ሰኔ 24/10/2014 ከዚህ ዓለም ድካም በ90 ዓመታቸው አርፈዋል።
•••
አባታችን በፀሎታቸው ከፈጣሪያቸው ጋራ የሚነጋገሩ የቤተክርስቲያን ሊቅ ፣ በአካባቢው እንደ ዋርካ የሚፈሩና የሚከበሩ ፣ በፆምና በፀሎት የተጉ ፣ የተጣላ የሚያስታርቁ ፃድቅ የበረከት አባት ነበሩ። ታዲያ አባታችን በዚሁ በደብራቸው ሰኔ ግባ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በ25-10-2014 ስርዓተ ቀብራቸው ተከናውኖ ከተፈፀመ በሗላ እንግዳ ነገር ተከሰተ።
•••
በቀብራቸው ቀን በቤተ ክርስቲያኑ አካባቢው ያለው ውሃ ደም በማንባት ሀዘኑን ገልጿል። ውሃና ደም ተቀላቅሎ ታይቷል። የአካባቢውን ማህበረሰብም በምትመለከቱት መልኩ የውሃውን ደም መቀላቀል አይቶ ተደንቋል ፣ አልቅሷል ፣ አንብቷል። መሬት ደም አልቅሳ ሸኝታቸዋለች።
•••
አንዳንዴ ደጋግ አባቶች ሲያልፉ ፈጣሪ ምልክትን ይሰጣል

➠ ይሄ የፈጣሪ ቁጣ ይሆን
➠ ደሙስ በየቦታው የሚፈሰው የሰው ልጅ ደም ይሆን
•••
ብቻ ፈጣሪ በምህረት እጁ ይታረቀን እግዚአብሔር አምላክ የአባታችንን ነፍሳቸውን በአብርሃም በይስሐቅ በያዕቆብ አጠገብ ያሳልፍልን። የአባታችን በረከታቸው ይደርብን። በጋዜጠኛ ታርቆ ፈንታው ስንኝ ልቋጭ
•••
" ታቹን ከበጌምድር ፣ ደብሩ ጊዮርጊስ ፣ ቦታው ሰኔ ግባ ፤
በደጋጎች መሄድ ፣ እንኳን ሰው መሬቱ ፣ የደም እንባ አነባ ፤ "
•••
ሰናይ ሰንበት
•••
ለሌሎች ሼር በማድረግ ይተባበሩ
640 viewsየእኔ ሀብት, 14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ