2022-08-28 12:42:27
" ፈጣሪ ልብ ይሰጣቸው ፣ ኢሳያስ ቂመኛ አይደለም "
የኢትዮጵያን እግር ኳስ ፌዴሬሽንን ለቀጣዩ አራት ዓመታት ለመምራት የተመረጡት አቶ ኢሳያስ ጅሩ ከተመረጡ በኋላ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል ።
" እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል " ያሉት ፕሬዝዳንቱ በቀጣይ ተቋም ግንባታ ፣ እንደ ግል ልጄ አየዋለሁ ያሉት የፓይለት ፕሮጀክት ላይ ጠንካራ ስራዎችን እንደሚሰሩ ገልፀዋል ።
" ለቀጣዮቹ አራት አመታት እንድንመራ ትልቅ የቤት ስራ ነው የተሰጠን ፣ ለሀገር የሚጠቅሙንን ሀሳቦች ለመቀበል ሁሌም ክፍት ነን ወደኋላ አንልም ።
ለመመረጥ ብዬ መራጩን ማታለል አልፈልግም ከመንግስት ጋር በመቀራረብ በተለይም የባህርዳር ስታዲየም በቶሎ የሚጠናቀቅበትን መንገድ እንፈልጋለን።
ውጪ የሚጫወተው ብሔራዊ ቡድናችን በሀገር ውስጥ ሲጫወት መመልከት እንደ ሁላችሁም እኔም ናፍቆኛል ፣ እሱ ላይ ትኩረት አድርገን እንሰራለን ነገር ግን የሁሉም አካላት ርብርብ ያስፈልጋል።
ውሸት አልወድም ዋሽቼ ትዝብት ላይ መውደቅ አልፈልግም ፣ ትላንት በከተማው የተደረጉ ነገሮች ተገቢ ያልነበሩ እና ወደፊት ሊቀሩ የሚገባቸው ተግባራት ናቸው።
በጎንዮሽ ድምፅ ለማግኘት የሚደረጉ ነገሮች መልካም አይደለም ፈጣሪ ልብ ይሰጣቸው ፣
ደጋፊዎቼ እንኳን ደስ አላችሁ ኢሳያስ ቂመኛ አይደለም " ሲሉ ንግግራቸውን ቋጭተዋል ።
@tengertsport
@kidusyoftahe
@ቤቢ የአማኑኤል ልጅ
425 viewsedited 09:42