2022-12-21 19:08:54
ወጣቶችን በቴክኖሎጂ መስክ ማሰልጠን እና ማብቃት ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገት ትልቅ ሚና አለው፦ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ
************************
ወጣቶችን በቴክኖሎጂ መስክ ማሰልጠን እና ማብቃት ለሀገራችን ሁለንተናዊ ዕድገት ትልቅ ሚና አለው ሲሉ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ገለጹ።
ፕሬዚዳንቷ ከአይኮግ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቤተልሄም ደሴ ጋር ተወያይተዋል።
ውይይታቸው ያተኮረው ድርጅቱ በታዳጊ ልጆች በተለይም ሴት ልጆች ላይ የሚያተኩሩ የቴክኖሎጂ ትምህርት ሥራዎች እንዲሁም በቅርቡ ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር እና ሁዋዌ ቴክኖሎጂስ ጋር ስላስመረቁት ዲጂትራክ ኢትዮጵያ የተሰኘ ፕሮጀክት ዙርያ መሆኑ ተገልጿል።
በዚሁ ወቅት ፕሬዚዳንቷ አብዛኛው የኅብረተሰብ ክፍል ወጣት በሆነበት ሀገር የቴክኖሎጂ ዘርፎችን ተግባራዊ ማድረግ ወሳኝ በመሆኑ ዓለም ውስጥ ይህንን ትውልድ በቴክኖሎጂው መስክ ማሰልጠን እና ማብቃት ለሀገራችን ኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገት ትልቅ ሚና አለው ብለዋል።
የአይኮግ ፕሮጀክት የሆነው ዲጂትራክ ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚገኙ ታዳጊ ወጣቶች እኩል የሆነ ዕድል ተሰጥቷቸው የኮዲንግ፣ የሮቦቲክስ እና ሌሎች አዳዲስ የዲጂታል ክህሎት ሥልጠና እንዲያገኙ ማስቻል እና በታለሙ አካባቢዎች ለሚገኙ ታዳጊ ወጣቶች የማገናዘብ፣ የችግር ፈችነት እና የፈጠራ ክህሎት የማዳበር ትምህርት ያለውን ጠቀሜታ ግንዛቤ ማስጨበጥ መሆኑን ከፕሬዚዳንት ጽ/ቤት የያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
አይኮግ ኢትዮጵያ በኮምፒውተር ኮዲንግ ላይ አተኩሮ የሚሰራ ሲሆን በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እና ሮቦቲክ የምርምር ማዕከል በማቋቋም እየሠራ እንደሚገኝ ኢቢሲ ዘግቧል።
491 views16:08