Get Mystery Box with random crypto!

✝✝የመጽሀፍ ቅዱስ ጥቅሶች✝✝

የቴሌግራም ቻናል አርማ tekese48 — ✝✝የመጽሀፍ ቅዱስ ጥቅሶች✝✝
የቴሌግራም ቻናል አርማ tekese48 — ✝✝የመጽሀፍ ቅዱስ ጥቅሶች✝✝
የሰርጥ አድራሻ: @tekese48
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 967
የሰርጥ መግለጫ

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን ፣ የቤተ ክርስቲያን መረጃዎች ፣ ትምህርቶችን እና መረጃዎች ለማግኘት ይቀላቀሉ ለወዳጅ እና ዘመድም share ያድርጉ ቤተሰብ ይሁኑ።

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-01-19 12:30:10 ሌሊቱን በውዳሴ በማኅሌት ካሳለፉ በኋላ ውኃው በፓትርያኩ፣ በሊቀ ጳጳሳት እና በካህናት ከመባረኩ በፊት ማለዳ ቅዳሴ ይጀምራል፤ ምእመናንም የቅዳሴ አካል ለመሆን ቀደም ብለው ይገኛሉ፡፡ ሃይማኖት አባቶችም ውኃውን በአብ፣ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ከባረኩት በኋላ ወደ ተሰበሰቡት ክርስቲያኖች በብዛት ውኃውን ለመርጨት ዝግጅት ያደርጋሉ፡፡
በዚያን ጊዜ ክርስቲያኖች በሺዎች ከሚቆጠሩ ዓመታት በፊት በዓይነ ኅሊናቸው ወደኋላ በመመለስ የጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት በማሰብ ከተረጩ በኋላ በደስታ ታቦታቱን በኅብረት ወደየቤተ ክርስቲያን በማጀብ ይጓዛሉ፤ ካህናቱም የያሬድን ዝመሬ በመዘመር በዓሉን ያከብራሉ፡፡
ሕፃናት፣ ወጣቶች እንዲሁም አረጋዊያን በሙሉ በዝማሬው ይሳተፋሉ። የቅዱሱ ታቦትም በደኅና ወደ መንበሩ ሲመለስ ሕዝቡ በመንፈሳዊ ደስታ ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡ ኢትዮጵያውያን በዚህ አስደናቂ እና መንፈሳዊ ክርስቲያናዊ ምግባር አማካኝነት የእግዚአብሔርን ልጅ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወደሱን የቀጠልን ሲሆን ለመጪው ትውልድም ይህንኑ እንድናስተላልፍ በእምነት እና ሃይማኖት ልንጸና ይገባል፡፡
እግዚአብሔር አምላክ በጥምቀቱ ፈውሰ ሥጋንና ፈውሰ ነፍስን ያድለን ዘንድ ፍቃዱ ይሁንልን፤ አሜን!

Join us @Tekese48
1.8K viewsSuNo , 09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-19 12:30:10 ጥምቀት


በዘመነ ሥጋዌ በናዝሬት ከተማ፤ ዮርዳኖስ ወንዝ የእስራኤል ሕዝብ በመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ተራ ይዘው በሚጠብቁበት ጊዜ እርሱ እንዲህ እያለ ይሰብክ ነበር፤ ‹‹እናንተ የእፉኝት ልጆች፥ ከሚመጣው መቅሠፍት ታመልጡ ዘንድ ማን ነገራችሁ? እንግዲህ ለንስሓ የሚያበቃችሁን ሥራ ሥሩ፤ አብርሃም አባታችን አለን በማለት የምታመልጡ አይምሰላችሁ፤ እግዚአብሔር ከእነዚህ ድንጋዮች የአብርሃም ልጆችን ማንሣት እንደሚችል እነግራችኋለሁ፡፡ እነሆ፥ ምሳር በዛፎች ላይ ተቃጥቶአል፤ መልካም ፍሬ የማያፈራውን ዛፍ ሁሉ ይቈርጡታል፤ ወደ እሳትም ይጥሉታል፡፡›› (ሉቃ.፫፥፯-፱)
ሕዝቡም ምን ቢያደርጉ እንደሚሻል በተራ በተራ ይጠይቁት ጀመር፤ እርሱም ለእያንዳንዱ ሲመልስ፤ ሁለት ልብስ ያለው አንዱን ለሌለው እንዲሰጥ፣ ለተራበ እንዲያበላ፣ ቀራጮችን ደግሞ ከታዘዙት አትርፈው አንዳይውስዱ እንዲሁም ጭፍሮችን በማንም ላይ ግፍ እንዳይፈጽሙ እየመከረ አጠመቃቸው፡፡ እነርሱም በልባቸው እጅግ እያደነቁ ከጌታችን ኢየሱስ ጋር መሰሉት፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ግን እንዲህ አላቸው ‹‹እኔ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ግን የሚበልጠኝ የጫማውን ማሰሪያ እንኳን ልፈታለት የማይገባኝ ይመጣል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ፣ በእሳትም ያጠምቃችኋል፡፡›› (ሉቃ.፫፥፲፮-፲፯)
ሕዝቡ ሁሉም ከተጠመቁ በኋላ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ውስጥ ገብቶ ሊጠመቅ ወደ እርሱ ሲጠጋ ቅዱስ ዮሐንስ ግን ‹‹እኔ በአንተ ልጠመቅ እሻለሁ፤ አንተ ወደ እኔ ትመጣለህን?›› በማለት ከለከለው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ አሁንስ ተው፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ ልንፈጽም ይገባናልና›› አለው፡፡ እርሱም ተወው፤ ጌታችን ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያውኑ ከውኃ ወጣ፤ በዚይች ቅጽበትም ሰማይም ተከፈተ፤ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ ሲቀመጥ አየ፡፡ እነሆም በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወድደው ልጄ ይህ ነው የሚል ድምጽ ከሰማይ መጣ፡፡›› (ማቴ.፫፥፲፫-፲፯)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ ልጁ መሆኑን እግዚአብሔር አብ ልጄ ብሎ መሰከረ፤ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወረደ፤ ወልደ እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ተጠምቆ በፅንፈ ዮርዳኖስ ታየ፡፡
እግዚአብሔር አምላክም ለአዳም የገባለነትን ቃል ለመፈጸም አንድ ልጁን ልኮ ከኃጢአት ባርነት አወጣው፡፡ ስለዚህም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣው አዳምን እና ሔዋንን ከባርነት ነፃ ለማውጣትና ድኅነት ሊሆናቸው ነውና በጥምቀቱ ጊዜ በዮርዳኖስ ወንዝ በሰይጣን ተቀብሮ የነበረውን የዕዳ ደብዳቤያቸውን ቀደደላቸው። ይህንንም ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ በማለት ተናግሮታል። ‹‹እናንተም በበደላችሁና ሥጋችሁን ባለመገረዝ ሙታን በሆናችሁ ጊዜ፥ ከእርሱ ጋር ሕይወትን ሰጣችሁ። በደላችሁን ሁሉ ይቅር አላችሁ። በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰ፤…።›› (ቆላ.፪፥፲፫-፲፬)
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለነፍሳችን ድኅነት ይሆነን ዘንድ ተጠምቆ አርአያ ሆኖናል፡፡ በጥምቀቱም ጥምቀትን ባርኮልናል፤ በኦሪት ጥምቀት ሥጋን እንጂ ነፍስን አይፈውስምና እርሱ በተጠመቀው ጥምቀታችን ተባረከልን፡፡
እኛም ስንጠመቅ በአዳም በደል ተወስዳ የነበረች ልጅነታችን ተመልሶ፣ የዕዳ ደብዳቤያችንም እንዲደመሰስልን አስረዳን፡፡ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም ቀደማዊና ደኃራዊ እንደሌለው እንደተመሰከረ እኛም ስንጠመቅ ከሥላሴ መወለዳችን ይረጋገጥልና፡፡ (ዮሐ. ፫፥፭፣ የሐዋ. ፪፥፴፰፣ ቆላ. ፪፥፲፩-፲፬)
ጥምቀት ለክርስቲያኖች ሁለተኛ ልደታቸው ነው፡፡ ከሥጋ የተወለደ ሁሉ ወደ ፈቃደ ሥጋው ስለሚያደላ መንፈሳዊ ልደት ያስፈልገዋል፡፡ ‹‹ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር ወደ የእግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፡፡›› (ዮሐ. ፫፥፫-፭)
በዘመነ ብሉይ ይፈጸም የነበረው ጥምቀት የንስሓ ጥምቀት ነበር፡፡ በሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹ንስሓ ግቡ ኃጢአታችሁ ይሠረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ›› ብሏቸው እንደተናገረው ጥምቀት ኃጢአትን ያስተርይልናል፡፡ (ሐዋ. ፪፥፴፯-፴፰)
በሐዲስ ኪዳን የሚፈጸመው ግን የልጅነት ጥምቀት ነው፤ ይህን ተከትሎ ወንድ ልጅ በዐርባ ሴት ልጅ በሰማንያ ቀን ይጠመቃሉ፡፡ የዚህም ምክንያት አዳም በተፈጠረ በ፵ ቀኑ፣ ሔዋንም በተፈጠረች በ፹ ቀኗ ወደ ርስታቸው ገነት እንደገቡ ሕፃናትም በ፵ እና በ፹ ቀናቸው ተጠምቀው የሰማያዊት ኢየሩሳሌም አምሳል ወደሆነችው ወደ ቤተ ክርስቲያን ይገባሉ፡፡
በተጨማሪም ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እኛ ሁላችን በሞቱ እንደተጠመቅን ሁላችሁ ይህን ዕወቁ፤ እኛ ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደ ተጠመቅን አታውቁምን? እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደተነሣ እንዲሁ እኛ በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን›› በማለት በጥምቀት ክርስቶስን እንደምንመስለው ተናግሯል፡፡ ‹‹ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን›› የሚለውን በገቢር ለመግለጽ እንዲሁም ‹‹በጥምቀት ደግሞ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር ሥራ በማመናችሁ ከእርሱ ጋር ተነሳችሁ›› ያለውን እንዲሁ በድርጊት ለማሳየት ነው፡፡ (ሮሜ ፮፥፫-፬፣ቆላ. ፪፥፲፪)
‹‹ያመነ የተጠመቀ ይድናል፤ ያላመነ ያልተጠመቀ ይፈረድበታል›› እንደተባለው ከገሃነመ እሳት ፍርድ እንድናለን። ሰው ክርስቲያን ይባል ዘንድ ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ማግኘት አለበት፡፡ ይህም በልጅነት የሚያገኘው በረከት በተቀደሰ ውኃ በመጠመቁ ነው፡፡ ካልሆነ ግን የእርኩስ መፈንስ ማደሪያ ወይንም መናፈቅ ይሆናል ማለት ነው፡፡ (ማር. ፲፮ ፥ ፲፮)
በእምነት ለተጠመቀ ሰው ግን ጥምቀት ፈውሰ ሥጋን እንዲሁም ፈውሰ ነፍስን ይሰጣል፤ ምክንያቱም እምነት ኃይልን ታደርጋለችና ጥምቀት ድኅነት መሆኑን አምነን ከተጠመቅን ኃጢአታችን ይሠረይልናል፤ ይህም ጌታችን ጥምቀትን ባርኮ ስለሰጠን በምሥጢረ ጥምቀት የምንረዳው ነው፡፡
ጌታችን ኢየሱስ የጥምቀትን ሥርዓት ከመሰረተልን በኋላ ደቀ መዛሙርቱን በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም የሰውን ዘር እንዲያጠምቁ አዟቸዋል፡፡ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ተከታዮች በሙሉም በምሥጢረ ጥምቀት እንደምንረዳው ሥርዓቱን ጠብቀን እንጠመቃለን፤ ይህም ሥርዓት ከዋዜማው ከተራ ጀምሮ የሚፈጸም ነው፡፡ (ማቴ. ፳፰፥፲፱-፳)
የጥምቀት በዓል በእነዚህ ሁለት ቀናት ውስጥ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ጥምቀት እና ተግባር የሚያመለክቱ ብዙ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓቶች ይከናወናሉ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጠፋውን ፍጥረቱን ፍለጋ ወደ ዓለም እንዴት እንደወረደ የሚገልጹ ያሬዳዊ ዝማሬዎች እና መዝሙሮች በከተራ ይዘመራሉ፡፡

ሁሉም የቃል ኪዳኖች (ታቦቶች) በእያንዳንዱ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ በአቅራቢያው ውኃ ወዳለበት ወደ ጅረት ገንዳ ይሄዳሉ፡፡ የዚህም ምሥጢር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከኢየሩሳሌም ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ እንዴት እንደሄደ የሚያሳይ ነው፤ አንድ ሌሊት ማሳለፉ ጌታችን በትህትና የእርሱን ተራ መጠበቁን የሚያሳይ ነው፡፡ በቅዱስ ዮሐንስ እጅ ከተጠመቁት ሕዝቦች መካከል ተጠምቋልና፡፡ ይልቁንም ተራውን በመጠበቅ የትህትናን ተግባር አሳይቶናል፡፡ ታቦታቱም ከሕፃናት፣ ከወላጆች፣ ከወጣቶች፣ ከአረጋዊያን፣ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች፣ ከቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት እና ከሌሎችም ምእመናን ጋር በሁሉም ክርስቲያኖች ይታጀባሉ፡፡
1.6K viewsSuNo , 09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-19 12:30:10
1.3K viewsSuNo , 09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 08:14:06 የተደረገልንን አስበን የጌታችንን ልደት እንደ ዮሴፍና ሰሎሜ በአንክሮ፣ እንደ ጥበብ ሰዎች በአምሐ፣ እንደ ቤተልሔም እረኞች አገልግሎታችንን በትጋት በመፈጸም፣ እንደ ቅዱሳን መላእክት በሰማያዊ ምስጋና እንድናከብር የቅዱሳን አምላክ፣ የአብ የባህርይ ልጅ፣ የድንግል ማርያም ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነቱ ይጎብኘን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይሄን እና ሎሌዎች የቤተ-ክርስትያን መረጃዎች እና የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ለማግኘት በ Telegram Channel ላይ >> @Tekese48
1.5K viewsSuNo , 05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 08:14:06 የእግዚአብሔር መልአክ የሩቅ ነገስታትን ጌታ ወደተወለደበት ቦታ ወደ ቤተልሔም በብርሀን መራቸው፡፡ ነገስታቱ በምስራቅ ያዩት ኮከብ ሕጻኑ ባለበት ቦታ መጥቶ እስኪቆም ድረስ በሰው ቁመት ልክ ዝቅ ብሎ ይመራቸው ነበር፡፡ ይህ ኮከብ የእግዚአብሔር መልአክ ነበር፡፡ እስራኤልን በብርሃን ፋና የመራ ጥበበኞችን በኮከብ አምሳያ መርቶአቸዋል፡፡በቀን የሚያበራ፤ ወደ ምስራቅ የሚሄድ፤ ቆሞ በሰው ቁመት ወደታች የሚጠቁም መልአክ እንጂ ኮከብ አይደለም፡፡
3 እረኞች
እረኞች የመወለዱን ብስራት ከመልአኩ ሰምተው ከመላእክት ጋር አመሰገኑ (ዘመሩ)፡፡  መልካም እረኛ እርሱ ነውና ልደቱም ቀድሞ ለእረኞች ደረሰ፡፡ ዮሐ 10፡11 እረኞቹ አመስግነውም አልቀሩም፡-‹‹እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ ተባባሉ። ፈጥነውም መጡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ። አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ። የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሩአቸው ነገር አደነቁ፡፡›› ሉቃ 2፡15-18 እረኞች ልደቱን ሰሙ፤ አመሰገኑ፤ ፈጥነው ሄዱ (በሌሊት መንጋቸውን ትተው)፤ አዩ፤ ያዩትንም ለሌሎች ገለጡ፡፡ እረኞችም እንደ ተባለላቸው ስለ ሰሙትና ስላዩት ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እያከበሩ ተመለሱ። የእውነተኛው እረኛ ልደት ለትጉሀን እረኞች ተበሰረ፡፡ በግርግም ተኝቶ ከካህናቱ ከጸሀፍቱ ሳይሆን ከእረኞች ምስጋናን ተቀበለ፡፡ የበጎች እረኞች የበጉን ልደት ከሊቃውንት ከመምህራን ከነገስታቱም ቀድመው ሰምተው አመሰገኑት፡፡
4 የጥበብ ሰዎች
የሩቅ (የምስራቅ) ነገስታት – የጥበብ ሰዎች – ሊሰግዱለት ስጦታንም ሊያበረክቱለት መጡ፡፡ በቅርቡ የነበሩት ነገስታት በመጣው ሠራዊት ብዛትና ‹‹የተወለደው ንጉስ›› በመባሉ ደነገጡ፡፡የጥበብ ሰዎች በኮከብ (በመልአክ) ተመርተው፤ ሁለት ዓመት ተጉዘው መጥተው፤ ሰግደውለት (የነገስታት ንጉስ ነውና)፤ ወርቅን ለመንግስቱ፣ እጣንን ለክህነቱ፣ ከርቤንም ለሞቱ ገበሩለት፡፡ በነቢይ ‹‹የተርሴስና የደሴቶች ነገሥታት ስጦታን ያመጣሉ፤ የዓረብ ነገሥታት እጅ መንሻን ያመጣሉ” መዝ 71፡10። እንደተባለ የልደት (የገና) በዓል የስጦታ ቀን የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡ የጥበብ ሰዎች ‹‹የተወለደው የአይሁድ ንጉስ ወዴት ነው?›› አሉ፡፡ ንጉስ ሆኖ የተወለደ እርሱ ብቻ ነው፡፡ ሌሎች ተወልደው ይነግሳሉ እንጂ ንጉስ ሆነው ሊወለዱ አይቻላቸውም፡፡ የጥብበ ሰዎች መወለዱንም አውቀው ስለነበር ‹‹የሚወለደው›› ሳይሆን ‹‹የተወለደው›› አሉ፡፡
5 ሄሮድስና ኢየሩሳሌም
የሩቅ ሀገር ነገስታት በልደቱ ተደስተው አምሐ ሲያቀርቡ የቅርብ ነገስታትና ኢየሩሳሌም ግን ደነገጡ (ተረበሹ)፤ የቅርቡ ንጉስ ሄሮድስ ግን ‹‹የአይሁድ ንጉስ ተወለደ›› ሲባል ደነገጠ፡፡‹‹ የካህናት አለቆችንና የሕዝቡን ጻፎች ሁሉ ሰብስቦ “ክርስቶስ በየት ይወለዳል?” ብሎ ጠየቃቸው። እንዲህም አሉት “በይሁዳ ክፍል ቤተ ልሔም ነው፤ በነቢይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና…›› አሉት ። ከዚህምበኋላ ሄሮድስ ሰብአ ሰገልን በስውር ጠራቸው፤ ኮከቡ የታየበትንም ዘመን ከእነርሱ ተረዳ፡፡ “ሂዳችሁ የዚያን ሕፃን ነገር ርግጡን መርምሩ፤ ያገኛችሁትም እንደ ሆነ እኔም መጥቼ እሰግድለት ዘንድ በእኔ በኩል ተመልሳችሁ ንገሩኝ” ብሎ ወደ ቤተ ልሔምም ሰደዳቸው። › ማቴ 2፡4-9 ሄሮድስ ይህን ያለው እንደ ቃሉ ሊሰግድለት ሳይሆን ሊገድለው አስቦ ነበር፡፡ የጌታን ልደት የቅርቡ ንጉስ ሄሮድስ ሳይሆን የሩቆቹ ነገስታት ሰብአ ሰገል ሰሙ፤ እርሱ ሲሰማ ተረበሸ፤ እነርሱ ግን ሲያገኙት ተደሰቱ፡፡
ይህንን የጌታን ልደት እኛስ እንዴት እንቀበለዋለን? እንደ ቤተልሔም ሰዎች ወይስ እንደ እረኞቹ? እንደ ጥበብ ሰዎች ወይስ እንደ ሄሮድስ? የቤተልሔም ሰዎች በምድራዊ ተግባር ተጠምደው ሌሎች እንግዶችን በማስተናገድ ሲባክኑ ጌታቸው ሲወለድ ማደሪያ መስጠት አልቻሉም፡፡ ትጉሃን እረኞች ግን ከብቶቻቸውን በትጋት ሲጠብቁ የራሳቸውን ጠባቂ አገኙት፡፡ እኛም በተግባረ ሥጋ ብቻ ተጠምደን ቤተመቅደስ የተባለ ሰውነታችንን ለጌታችን ማደሪያ ከመሆን ከልክለን እንግዳ የተባለ ኃጢአት፣ እንግዳ የተባለ የዲያብሎስ ፍሬ እንዲሰለጥንብን መፍቀድ የለብንም፡፡ የጥበብ ሰዎች አባቶቻቸው የነገሯቸውን ተስፋ አስበው፣ ሩቅ መንገድ ተጉዘው፣ አምሐ ይዘው በመምጣታቸው ከመጡበት ያለማመን መንገድ ይልቅ በሌላ የእምነት መንገድ (የክርስቶስን ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆንን አምነው) ተመለሱ፡፡ (ማቴ. 2፡12)
በኢየሩሳሌም የነገሰ ሄሮድስና እረኝነታቸውን ረስተው፣ በምድራዊ ተንኮል ተጠምደው ሰማያዊ ተግባራቸውን የረሱት የአይሁድ አለቆች ግን በተስፋይቱ ምድር ተቀምጠው የጌታቸውን መወለድ ለመስማት አልታደሉም፡፡ ሲሰሙም ለክፋት እንጅ ለድኅነት አልተጠቀሙበትም፡፡ እኛም እንደ ጥበብ ሰዎች አባቶቻችን ያስተማሩንን የክርስቶስን ከሁለት አካል አንድ አካል፣ ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ሆኖ በሥጋ ማርያም የመገለጥ ፍቅር እያሰብን እንደ ጥበብ ሰዎች አምሐ ልናቀርብለት ይገባል፡፡ ለእግዚአብሔር የምናቀርበው አምሐም ቅዱስ ጳውሎስ እንዳስተማረን ቤተመቅደስ የተባለ ሰውነታችንን እንዲሁም በዕውቀትና በእምነት የታነጸ አገልግሎታችንን ነው፡፡ (ሮሜ. 12፡1)
እንደ ሄሮድስና የአይሁድ አለቆች በተስፋይቱ ምድር በቅድስት ቤተክርስቲያን ተቀምጠን ከእግዚአብሔር ጸጋ ተለይተን እንዳንጣል ልንተጋ ያስፈልጋል፡፡ ለዚህም አብነታችን የጌታችን፣ የመድኃኒታችን እናት፣ የቅዱሳን ነቢያት ተስፋ ፍፃሜ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ናት፡፡ እርሷ የተደረገውን ሁሉ በልብዋ እያሰበች በአንክሮ ትጠብቀው ነበርና፡፡ (ሉቃ 2፡9)፡፡ የዓለም መድኃኒት መወለዱን፣ የነቢያት ትንቢት መፈፀሙን፣ የመላእክትን ምስጋና፣ የእረኞችን ምስጋና፣ የጥበብ ሰዎችን ምስጋና፣ ስግደትና ስጦታ በልብዋ አኖረችው፡፡ የምስጢር መዝገብ ናትና፡፡ እርስዋ በልብዋ ያኖረችው ነው ለእኛም የደረሰን፡፡
በዚህ ሁሉ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር እንረዳለን፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና። 1ኛ ዮሐ 4፡9 እንዳለ፡፡ ይህን የእግዚአብሔርን ፍቅር መርምረን መፈጸም አንችልምና በአንክሮ እናደንቃለን፡፡
ይህን አስመልክቶ የደገኛው የባስልዮስ ወንድም፣ የኑሲስ ኤጲስ ቆጶስ ቅዱስ ጎርጎርዮስ እንዲህ አለ፡- “ለእኛም በሥጋ መገለጡን እንደሚገባው መርምረን ልናውቀው አይቻለንም፤ ጸጋን ለመስጠት ያደረገውን ተዋሕዶ የሚያምኑት ሰዎች ከእነርሱ ትምህርትን ይቀበሉ ዘንድ ይገባል ብሎ ቃል ስለእነርሱ ከተናገረላቸው ከመምህራን እንማር ዘንድ ያሻናል፡፡” ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ጎርጎርዮስ 35፡10፡፡ ስለዚህ ሁላችንም የተደረገልንን ድንቅ ተዓምር፣ የተሰጠንን ድንቅ ስጦታ እያሰብን ከቅዱስ ኤፍሬም ጋር እናመስግን፡- “በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሆኗልና፣ ኑ ይህን ድንቅ እዩ፣ ስለተገለጠልን ምስጢር ምስጋና አቅርቡ፣ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና፣ ቃል ተዋህዷልና፣ ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት፣ የማይታወቅ ተገለጠ፣ የማይታይ ታየ፣ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥ ሰው ሆነ” የረቡዕ ውዳሴ ማርያም፡፡
1.5K viewsSuNo , 05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 08:14:06 መድኅን ተወልዶላችኋል!

“እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋል፤ ይኽውም ቡሩክ ጌታ ክርስቶስ ነው፡፡” ሉቃ 2፡11
አዳም ከተሳሳተ ከገነትም ከወጣ በኋላ 5,500 ዘመን ሲፈፀም፣ ሕገ ኦሪት ከተሰጠች 1,800 ዘመን በኋላ፣ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ከተሠራ 1,000 ዓመት በኋላ፤ በልደተ ሥጋዌ (ማቴዎስ) ተቆጥሮ ከአብርሃም 42 ትውልድ በኋላ፣ በልደተ ሕጋዊ (ሉቃስ) ተቆጥሮ ከአዳም 77 ትውልድ በኋላ፣  ከዛሬ 2011 ዓመት በፊት በዓለማችን ላይ አንድ ታላቅ ተአምር ተከናወነ፡፡
አውግስጦስ ቄሳር የሮም ገዥ፣ ሄሮድስ የይሁዳ ንጉስ፣ እንዲሁም ቄሬኔዎስ የሶርያ ገዥ በነበሩበት ወቅት የሰውን ልጅ ሕይወት ወደ ታላቁ የድኅነት ምዕራፍ ያሸጋገረ ታላቅ ክስተት በማዕከለ ምድር፣ በሀገረ እስራኤል ተከሰተ፡፡ ይህም የጌታችን የአምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ነው (ማቴ 1፡17)፡፡ የእርሱ ልደት ከሌሎች ልደታት ሁሉ ልዩ ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በነቢያት ትንቢት ተነግሮለት፣ በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤልም ብስራት ተነግሮለት በህቱም ድንግልና ስለተወለደ የእርሱ ልደት እጅግ ልዩ ነው፡፡
በዚያ ወራት  ለግብር አሰባሰብ እንዲያመች በማሰብ ሰው ሁሉ እንዲቆጠር (እንዲፃፍ) ከአውግስጦስ ቄሳር ትዕዛዝ ወጣች፡፡ የእመቤታችን ጠባቂ የነበረው ዘመዷ አረጋዊው ዮሴፍም ከዳዊት ወገን ነበርና ፀነሳ ከነበረችው ከድንግል ማርያም ጋር ሊቆጠር ከገሊላ ናዝሬት ከተማ ተነስቶ ቤተልሔም ወደምትባል ከተማ ወደ ይሁዳ ሄደ፡፡ሁሉም በየወገኑ ይቆጠር ስለነበር ዮሴፍም ከዳዊት ወገን ስለነበር ወደቤተልሔም ሄዱ፡፡ ጌታም ከአሕዛብ ጋር (እነርሱን ሊያድን መጥቷልና) አብሮ ይቆጠር ዘንድ ወደዚያው አመሩ፡፡
በዚያም (በቤተልሔም) እያሉ የድንግል ማርያም የመውለጃዋ ወራት (9 ወር ከ 5ቀን) ደረሰ፡፡ የበኩር ልጅዋንም ወለደችው፡፡ ‹‹እኔም ደግሞ በኩሬ አደርገዋለሁ፤ ከምድር ነገስታትም ከፍ ይላል (መዝ 88፡27) ፡፡›› እንደተባለ የበኩር ልጅዋን ወለደችው፡፡ አውራ ነህ ስትል እንዲሁም እንደዚህ በዮሴፍና በኒቆዲሞስ ትገነዛለህ ስትልአውራ ጣቱን አሠረችው፡፡  በድርብ በፍታ ትገነዛለህ ስትል፤ ካህናት ሥጋህን ይጠቀልሉታል ስትል በጨርቅም ጠቀለለችው፡፡ በግርግምም አስተኛችው፤ በእንግዶች ማረፊያ ቦታ ስላልነበራቸው ህፃኑ በግርግም ተኛ፡፡
በዚህች ዕለት የመወለዱ ትንቢት ተፈፀመ፡፡ የመወለዱ ብስራትም ተፈፀመ፡፡ በነቢይ ‹‹ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች›› የተባለው (ኢሳ 7፡14) ተፈፀመ፡፡ ‹‹በጨለማ የሄደ ሕዝብ ታላቅ ብርሃን አየ በሞት ጥላና በጨለማ ሀገርም ለነበሩ ብርሃን ወጣላቸው (ኢሳ 9፡2)››እንደተባለም ያ ብርሀን ወጣ፡፡ እንዲሁም ‹‹ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኀያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።›› ኢሳ 9፡6 ተብሎ እንተተነበየም ሕፃን ተወለደ፡፡ ‹‹ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች ›› (ኢሳ 7፡15) እንደተባለም ስሙን አማኑኤል አለችው፡፡ አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡ ‹‹ ከጽዮን ታዳጊ ይመጣል፤ ከያዕቆብም ኃጢአትን ያርቃል፡፡››(ኢሳ 59፡20)ተብሎ እንደተፃፈ መድኃኒት ክርስቶስ፣ አዳኝ ክርስቶስ፣ ወገኖቹን እስራኤል ዘነፍስን የሚታደግ (የታደገ) ክርስቶስ ከአማናዊት ጽዮን ከድንግል ማርያም ወጣ፣ ተወለደ፡፡ ለድንግል ማርያም ‹‹ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ›› እንዲሁም ለዮሴፍ ‹‹ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ” (ሉቃ 1፡31 ማቴ 1፡21) ተብሎ በመልአኩ እንደተነገረም ስሙን ኢየሱስ አሉት፡፡
አስቀድሞ በነቢያት ስለመወለዱ ብቻ ሳይሆን ስለሚወለድበትም ቦታም፡-‹‹አንቺም የኤፍራታ ምድር ቤተልሔም ሆይ! አንቺ በይሁዳ አእላፋት መካከል ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፤ ነገር ግን አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘለዓለም የሆነ፥ በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ከአንቺ ይወጣልኛል።››(ሚክ 5፡2) እንደተባለ ታላቁ የሰማይና የምድር ንጉስ በቤተልሔም ተወለደ፡፡ ‹‹ እነሆ በኤፍራታ ሰማነው፤ ዛፍ በበዛበትም ቦታ አገኘነው፡፡››(መዝ 131፡6)ተብሎ እንደተፃፈም የሕይወት እንጀራ የሆነው መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእንጀራ ቤት  በተባለችው በቤተልሔም ተወለደ፡፡
የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት የተለያዩ አካላት በተለያየ መልክ ተቀበለውታል፡፡
1 እንስሳት
እንስሳት ትንፋሻቸውን ገበሩለት፤ በዚያ የነበሩ እንግዶች ግን ሥፍራ አልሰጡትም፡፡ ‹‹በሬ ገዢውን አህያም የጌታውን ጋጥ አወቀ፤ እስራኤል ግን አላወቁኝም፥ ሕዝቤም አላስተዋሉኝም።››(ኢሳ 1፡3) እንደተባለ እንስሳት (አድግና ላህም) አወቁት፤ ሰዎች ግን አራቁት፡፡ በእንስሳት በግርግም መተኛቱ የትህትናው ጥግ ነው፡፡ ‹‹ወራሹ ሕፃን ሳለ ለሁሉ ጌታ ሲሆን ከአገልጋይ የሚለይ አይደለም ››(ገላ 4፡1) እንደተባለ ንጹሐ ባህርይ የእግዚአብሔር በግ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎች በሚያድሩበት በበረት ተኛ፡፡በቀዝቃዛ (ተስፋ በቆረጠ ልብ)፤ በጨለማ (ብርሀን በሌለው ኃጢአተኛ ልብ)፤ ንፁህ ባልሆነ (ኃጢአት ባጎሰቆለው ልብ) ቦታ ተወለደ (አደረ)፡፡
2 መላእክት
የሰማይ መላእክት ልደቱን ለእረኞች አበሰሩ፤ ነገስታትን (ጥበበኞችን) ወደ ቤተልሔም መሩ፡፡ በጌታ ልደት መላእክት ከሰው ልጅ ጋር አብረው ዘመሩ፡፡ ‹‹በዚያ ሀገር እረኞች ነበሩ፤ ሌሊቱንም ተግተው መንጋቸውን ይጠብቁ ነበር፡፡ እነሆም፥ የእግዚአብሔር መልአክ በአጠገባቸው ቆመ፤ የእግዚአብሔርም ብርሃን በዙሪያቸው አበራ፤ ታላቅ ፍርሃትንም ፈሩ፡፡ መልአኩም እንዲህ አላቸው፣ “እነሆ፣ ለእናንተና ለሕዝቡ ሁሉ ደስታ የሚሆን  ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፡፡ እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋል፤ ይኽውም ቡሩክ ጌታ ክርስቶስ ነው፡፡ ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ።›› ሉቃ 2፡8-13 ይህ ለእረኞቹ የተነገረው የልደቱ ብስራት ነው፡፡የተወለደው ለመላእክት ሳይሆን ለሰው ልጆች ነውና መላእክት ተወልዶልናል ሳይሆን ተወልዶላችኋል አሉ፡፡
ይህ ታላቅ የምሥራች የእምነታችን መሠረት ነው፡፡ እምነታችን ከእግዚአብሔር ስለመሆኑ መገለጫው ይህ ነው፡፡‹‹ ወንድሞቻችን ሆይ፥ መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር ሆነው እንደ ሆነ መርምሩ፤ ብዙዎች ሐሰተኞች ነቢያት ወደ ዓለም መጥተዋልና። የእግዚአብሔርን መንፈስና የሐሰትን መንፈስ በዚህ ታውቃላችሁ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የሚያምን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስም በሥጋ እንደ መጣ የማያምን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ ይህም እንደሚመጣ የሰማችሁት ሐሳዊ መሲህ ነው፤ አሁንም እንኳ በዓለም ውስጥ አለ።›› እንደተባለው የጌታችን ልደት የተዋህዶ መሠረቷ ነው፡፡ 1ኛ ዮሐ 4፡1-3
መልአኩ አስቀድሞ ለተናቁት ለእረኞች ልደቱን አበሰረ፡፡ ‹‹ድንገትም ከዚያ መልአክ ጋር ብዙ የሰማይ ሠራዊት  እግዚአብሔርን እያመሰገኑ መጡ። “ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ ” ይሉ ነበር።›› ሉቃ 2፡14 አምላክ ሰው ሆነ፤ ሰውም አምላክ ሆነ፡፡ በመላእክት ዘንድ ምስጋና ተደረገ፤ በደቂቀ አዳምም ዘንድ አንድነት ሆነ፡፡ የሰው ፍቅር አገብሮት አምላክ ሰው ሆነ፡፡
1.2K viewsSuNo , 05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 08:14:06
1.0K viewsSuNo , 05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 08:00:44
#ተወልደና_ሆ_እም_ድንግል /2/
ሲነገር ነበረ በነብያት አፍ
...ተወልደና ሆ እም ድንግል /2/
በአንዱ በእግዚአብሔር በአንዱ በመንፈስ
...ተወልደና ሆ እም ድንግል /2/
አንድ ቀን እንዲሆን ፀሐይ እንዲወጣ
...ተወልደና ሆ እም ድንግል /2......
እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም
አደራሳችሁ።
መልካም በዓል ይሁንልን አሜን!!!
Join us @Tekese48
1.1K viewsSuNo , 05:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-28 07:22:10 በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል በዓል በሰላም አደረሳችሁ

ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ በተረዳኢነቱና በአማላጅነቱ በክርስቲያኖች ዘንድ ይወደዳል፡፡ ምክንያቱም ያዘኑትን ለማጽናናት የምሥራች ለመንገር ከእግዚአብሔር ወደ ምእመናን ይላካልና፡፡
ገብርኤል ማለት የእግዚአብሔርን ልጅ የሚመስል ጌታና አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱሳን ሰማእታት ገድላቸውን እንዲፈጽሙ እሳቱንና ስለቱን ተሳቀው ወደ ኋላ እንዳይመለሱ ይረዳቸዋል፡፡
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን የቅዱሳን መላእክትን ወርኃዊና ዓመታዊ በዓላቸውን በፀሎትና በምሥጋና ታከበራለች፤ በተለይ ታህሣሥ 19 ቀን የሚከበርበት ምክንያት ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሠለሥቱ ደቁቅን ከዕቶነ እሳት ( ከነደደ እሳት ) ያዳነበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡

በጣዖት ፍቅር እጅግ ከመጠን በላይ ልቡ ተቃጥሎ የነበረው የባቢሎን መሪ ናቡከደነጾር ቁመቱ ስድሳ ወርዱ ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቅ ምስል አሰርቶ መኳንንቱን ሰብስቦ ሕዝቡ በሙሉ ለጣኦት እንዲሰግድ አዋጅ አወጀ፡፡ ያ ዘመን ለእግዚአብሔር ወዳጆች የፈተና ዘመን ነበር፡፡ አስመሳዮች ለጣኦት ሰገዱ ተረበረቡ፡፡ እውነተኛው አማኞች ግን በእግዚአብሔር ላይ ያላቸው እምነት ንጉሥ የወደደው ጊዜ የወለደው በሚል አስተሳሰብ አይለወጥም፡፡

በዚያ ፈታኝ ዘመን ነበር ሶስት ታማኝ የእግዚአብሔር ባለሟሎች የተገኙት፡፡ ንጉሡ ላቆመው ጣኦት ያልሰገደ ወደ እቶን እሳት ተጥሎ እንደሚሞት ቁርጥ ውሣኔው መሆኑን ወጣቶቹ በሚገባ ያውቁታል ግን ይህንን አልፈሩም፡፡ ንጉሥ ሆይ አምላካችንን በመካድ አንተ ላቆምከው ጣኦት አንሰግድም አሉት፡፡ ሶስቱ ወጣቶች የወሰዱት ይህ አቋም ለንጉሡ ታላቅ ራስ ምታትን ፈጠረ፤ ንጉሡም አገልጋዮቹን ጠርቶ እሳቱ ሰባት እጥፍ እንዲነድ ትዕዛዝ ሰጠ እሳቱም ሰባት እጥፍ ነደደ፡፡
ወዲያውኑ የንጉሡ አገልጋዮች አናንያን፣ አዛርያ፣ ሚሳኤልን እያንከበከቡ ወደ እቶን እሳት ወረወሯቸው ፡፡ ሠለስቱ ደቂቅ ከየት እንደመጣ ከማይታወቅ እንግዳ ጋር በመሆን በዕቶን እሳት ውስጥ ይንሸራሸሩ ጀመር፡፡ ይህ ተዓምራት ንጉሡንና መኳንንቱን አስገረመ ንጉሡም በዚህ ወቅት እነሆ እኔ በእሳቱ መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ እሳቱ ምንም አላቆሰላቸውም አራተኛውም የአማልክትን ልጅ ይመስላል አለ፡፡

የነደደ እሳት ውስጥ ገብቶ ከመውጣት ባልተናነሰ መከራ ውስጥ ገብተው በቅዱስ ገብርኤል አማላጅነት ከሞተ ሥጋ ነፍስ ድነው እውነተኛ ምሥክርነታቸውን የሚሰጡ ብዙዎች ናቸው፡፡ በመልአኩ ሥም በፈለቀው ጠበል ተጠምቀው ደዌ የራቀላቸው እጅግ በርካታ ናቸው፡፡ በየዓመቱ በቁልቢና በቅዱስ ገብርኤል ስም በታነጹ አብያተ ክርስቲያናት የሚሰበሰበው ምዕመናን ሥዕለቱ የሰመረለት ልመናው የተሰማለት እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ስለዚህ ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ገብርኤል የተሰጠውን ጸጋ ተረድተን የመልአኩን አማላጅነት በመጠቀም ልናከብረው  ይገባል፡

ይሄን እና ሎሌዎች የቤተ-ክርስትያን መረጃዎች እና የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ለማግኘት በ Telegram Channel ላይ >> @Tekese48
1.3K viewsSuNo , 04:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-28 07:22:04
1.1K viewsSuNo , 04:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ