Get Mystery Box with random crypto!

የቴዲ አፍሮ ሽማግሌ ሚያዝያ 10/1965 ዓ.ም (የዛሬ 50 አመት) ሺ አለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ | Teddy Afro

የቴዲ አፍሮ ሽማግሌ

ሚያዝያ 10/1965 ዓ.ም (የዛሬ 50 አመት) ሺ አለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ የተወለደባት ዕለት ነች። ሀይሌ ገብረሥላሴ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ በዓለም ላይ ከፍ አድርጎ ያውለበለበ ታላቅ አትሌት ነው። ሩጫን ከጀመረባት ዘመን እስከ አሁኗ ቅጽበት ድረስ ኃይሌ ገብረሥላሴ በዓለም ላይ ያለው ክብር ወደር የማይገኝለት ሲሆን ኢትዮጵያን በዘመኑ በትልቅ ክብር ለዓለም ህዝብ አስተዋውቋል።

የዓለማችን ትልቁ የመገናኛ ብዙሃን ጣቢያ /DSTV/ ስለ ሺ አለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ ጀብድ በተደጋጋሚ ይዘግባል። ትልልቅ የዓለም መጽሔቶችም ኃይሌን አወድሰውታል። በተጨማሪም ኃይሌ ገብረሥላሴ ሽማግሌ ሆኖ ከዳራቸው ጥንዶች ውስጥ ቴዲ አፍሮ እና አምለሰት ሙጬ ተጠቃሽ ናቸው።

ሺ አለቃ አትሌት ኃይለ ገብረሥላሴ (የሀገር ሽማግሌ) አገርህን ያስከበርክ ሰንደቋንም ከፍ አድርገኽ ያውለበለብክ ታላቅ ሰው ነህና እንወድሃለን። በታላቅ ክብርም እናከብርሃለን።

ጥቁሩ የዓለማችን አንበሳ ሆይ እንኳን በምትወዳት ሀገርህ ላይ ተወለድክልን። መልካም ልደት።

"እዩት ንጉሡ ግርማ ሞገሱ
ዘውዱን ሸለመው ሰጠው ለአዲሱ"

@tataafro_official (ነፃ ብዕር)