Get Mystery Box with random crypto!

ዕለተ ዓርብ፣ ዕለተ ስቅለት፣ መልካሙ ዓርብ በዚህች ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ | Teddy Afro

ዕለተ ዓርብ፣ ዕለተ ስቅለት፣ መልካሙ ዓርብ

በዚህች ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕፀ መስቀል የተሰቀለባት ዕለት ናትና “ዕለተ ስቅለት”የእግዚአብሔር መልካምነት ለሰው ልጅ ድኅነት በፍቃዱ ራሱን አሳልፎ ለሞት በመስጠቱ የተገለጠባት ናትና “መልካሙ ዓርብ” ይባላል።

ዓርብ ነግህ (ሲነጋ)

በዚህች ዕለት በነጋ ጊዜ የአይሁድ ሊቃነ ካህናት ኢየሱስን ወደ ፍርድ አደባባይ ሊያወጡት፣ ለጲላጦስ አሳልፈው ይሰጡት ዘንድ እንዲሁም በፍርድ አደባባይ ይሰቅሉት ዘንድ የተማከሩበት ዕለት ነው።

“ሲነጋም ጊዜ የካህናት አለቆችና የሕዝቡ ሽማግሎች ሁሉ ጌታችን ኢየሱስን ሊገድሉት ተማከሩ፤ አስረውም ወሰዱት፥ ለገዢው ለጰንጤናዊው ጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት” እንዲል። (ማቴ.፳፯፥፩-፪)

መልካሙ ዐርብ