Get Mystery Box with random crypto!

ሶስት አርሶ አደሮች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን የቡርጂ ልዩ ወረዳ ገለፀ። የቡርጂ ልዩ ወረዳ በ | TALIA MEDIA

ሶስት አርሶ አደሮች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን የቡርጂ ልዩ ወረዳ ገለፀ።

የቡርጂ ልዩ ወረዳ በተለያዩ ጊዜያት በገላና ሸጥ እና ከምዕራብ ጉጂ ጋር በሚያዋስኑን አከባቢዎች የአከባቢውን ሠላም የማይፈልጉ ሀይሎች የንፁሐንን ሕይወት እየቀጠፉ ይገኛሉ ብሏል።

" ምንም እንኳን የፀጥታ ሥጋት ብኖርም መተዳደሪያቸው የሆነውን የእርሻ ሥራ በማካሄድና ጤፍ በማጨድ ላይ የነበሩ ንፁሐን አርሶ አደሮች በገዛ መሬታቸው እና አከባቢያቸው ሲገደሉ ቁጥራቸው በርከት እያለ ያለ ነው " ብሏል።

ትላንትና በተመሳሳይ መልኩ #በዋሌያ ቀበሌ የዕለት ተግባራቸውን ለመከወን የወጡ ሶስት አርሶ አደረሮች ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ ተቀጥፏል ሲል አሳውቋል።

ልዩ ወረዳው የቡርጂ ማሕበረሰብ እና የሟች ቤተሰብና ዘመድ አዝማድ ሀዘኑን ገልጾ የተፈጸመው ድርጊት እጅግ አንዳሳዘነውና ቁጭት እንደፈጠረበት ገልጿል።

" ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እነዚህ ፀረ ሰላም ኃይሎች የእጃቸውን እንዲያገኙ በጥብቅ እየሠራን ነው " ያለው የቡርጂ ልዩ ወረዳ " " የክልል መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገልን እንዳለ ለማረጋገጥ እንወዳለን " ሲል አሳውቋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@taliamedia