2022-07-07 21:49:41
ፅናት
ክፍል
"""""
""""""
፨ፅናትም "አዎ ሙታን ሙታን ነው ያሉት ልክ ነሽ በፀሎቴ ልቤ
ሊፈነዳ ነው ምን ይሻላን ኧረ ወይኔ" አለች። በድንገት 1 ከ
እንቅልፍ የነቃ ድምፅ "ምንድነው?" አለ።ፅናት በድንጋጤ ዘላ
በፀሎት አልጋ ላይ ወጣች። ፅናት ተኝታበት ከነበረበት አልጋ
እግርጌ ሊባኖስ ቀና አለች። ፅናት ደነገጠች "እንዴ ሊቦ አንቺ
አንቺ አንቺ ቆይ የት ነበርሽ? "አለቻት። በፀሎትም ግራ ተጋብታ
"እንዴ ቆይ ምን እየተፈጠረ ነው?" አለች። ሊባኖስ በፅናት ሁኒታ
ግራ ተጋብታ "ሚጢጢዋ ምንድነው የሆንሽው? እየተንቀጠቀጥሽ
እና በፍረሀት አይን እያየሽኝ ያለሽው ቆይ ለምድነው?" አለቻት።
፨በፀሎት የፅናትን እጅ ጥብቅ አድርጋ ይዛዋለች። ሊባኖስ አሁን
ይበልጥ ግራ በተጋባ አስተያየት እያየቻት "በፀሎት አንቺስ
ለምንድነው ቆይ የፅናትን እጅ እንዲ አጥብቀሽ የያሽው?" አለቻት
። በፀሎትም ምንም ሳትል በቶሎ የፅናትን እጅ ለቀቀችው።
ሊባኖስ አሁን ደሞ ወደ ፅናት እያፈጠጠች "ሚጢጢዋ ቆይ ምን
ተፈጥሮ ነው?አለቻት ቀዝቀዝ ለማለት እየሞከረች። ፅናት
በሚንቀጠቀጥ ድምፅ " አይ ከእንቅልፌ ስነሳ አንቺ አጠገቤ
አልነበርሽም ከዛ ከዛ..." እያለች የተሰማትን ስሜት ከፈጠረባት
ጭንቀት ጋር ደምራ ነገርቻት ፅናት ንግግሯን ያቆመችው ሊባኖስን
ሙታን ማን እንደሆኑ በመጠየቅ ነው። ሊባኖስ ግን "አይ አይ
ጆሮዋቹ ነው" በሉ አሁን ተኑ እኔም ልተኛ ብላ ወደ ፅናት እግርጌ
ሄዳ ተኛች።
፨ ፅናትም ረዥም ደቂቆች በፀሎትን አቅፋ ከቆየች በኋላ
ከበፀሎት አልጋ ተነስታ "ሊቦ ትራስ አለሽ?" ብላ ስትሄድ ሊባኖስ
የለችም። ፅናት እየተዝለፈለፈች ወደ በፀሎት አልጋ ሂደች።
በፀሎት ፈዛለች ተቃቅፈው ለሊቱን እንቅልፍ በአይናቸው ሳይከትም
አሳለፉ እና ሊነጋጋ ሲል ሁለቱም እልም ያለ እንቅልፍ እንደተቃቀፉ
ወሰዳቸው።
፨ጠዋት ቀድማ የተነሳችው በፀሎት ነበረች።የቀሰቀሳት
በመስኮቱ በኩል የሚገባው ሀያል የፀሀይ ጨረር ነበር። በፀሎት
ፅናትን "ፅናቴ እህቴ የኔ ንቂ ንቂ ነግቷል" አለቻት። ፅናት አይኗን
እያሻሸች ስትነሳ የተኑበት ክፍል በር በረገግ( ከፈት) ብሏል። ግን
ተነስታ መሬቱን መረገጥም ፈራች። አልጋው ላይ እንዳለች አይኗን
ወደ ጣሪያው እጇቿን ወደ አፎቿ አድርጋ መፀለይ ጀመረች። ፅናት
ስትፀልይ በትንሹም ቢሆን ድምፅ ስለምታወጣ በፀሎት ፅናት
ፀሎት ላይ እንዳለች ተረዳች። በፀሎትም መፀለይ ጀመረች።
ሁለቱም ፀልየው ጨርሰው በዝምታ ቆዩ።
፨ በድንገት በሩ ቧ ብሎ ተከፈተ በፀሎትን ያዳንዋት ስውዬ አባ
በሬሳ ነበሩ። ፅናት ከአልጋው ላይ ተነሳች። በፀሎት ግራ ገብቷት
"ፅናቴ ማነው" አለች። ፅናትም ሀኪምሽ ናቸው አለቻት።" ደና
አደራቹ ፍጥረታት?"አሉ። ማንም መልስ አልስጣቸውም። ይህንን
ያስተዋሉት አባ በሬሳም "ምነው ልሳናቹ ጠፋ ልክ እንደ ሙታን?"
አሉና በፀሎትን ከጭንቅላቷ ብድግ አድርገው ከኪሳቸው የሚቀባ
ነበር አውጥተው ቀብተዋት ወጡ። ፅናትና ትግስት በድንጋጤ
ፈዘዋል።
፨ የአቶ በሬሳ እግር ከክፍሉ እንደወጣ ሊባኖስ መጣች። ደና
አደራቹ አለች ለእሷም መልስ የሰጣት የለም።ፅናት ቅድም
ከቆመችበት አልተነቃነቀችም በፀሎትም አልጋዋ ላይ ፈዛ እና
ደንዝዛ ነው ያለችው። ሊባኖስ " እናተ ልጆች" ስትል ሁለቱም
ደንግጠው ከፍዘታቸው ነቁ። "ሚጢጢዋ በሉ ቶሎ በሉ ወደ ቤታቹ
የመሄጃ ስአት ደረሷል ቁርስ ቤታቹ ትበላላቹ" ብላ ወጣች። ቆየት
ብላ ከአንድ ፈረጣማ ወጣት ጋር የበፀሎትን ዊልቸር ይዘው
መጡና በፀሎት ዊልቸሯ ላይ እንድትሆን እረድተዋት
አስቀመጡዋት። ከዛ ሊባኖስ የበፀሎትን ዊልቸር እየገፋች ከክፍሉ
ወጣችና "ሚጢጢዋ በይ ነይ" አለችና ወደ ፈረጣማው ሰውዬ
ዞራ "ጎረምሳው በል ቶሎ መኪናውን አዘጋጅ" አለችው። እሱም
እሺታውን ገልፆላት ወጣ።
፨ ልጁ እንደወጣ እነሱም ተከተሉት ፅናት ጊቢውን ቃኘችው
አስፈሪ ደባብ አለው። ብዙ ዛፎች መሬት ላይ ደሞ በየመጠኑ ኤሊ
እና ግዙፍ የፎቅ ቤት አለ። ከዛ ጊቢ ሲወጡ ፅናት እና በፀሎት
እፎይይይይይ እስይይይይይ ተመስገን አሉ።
፨ ከዛማ ፅናት እና በፀሎት ወደ ቤታቸው ከሊባኖስ እና ከሹፌሩ
ጋር ሄዱ። ቤታቸው ሲደርሱ ነፃነት ተሰማቸው። ሊባኖስ ነበረች
በፀሎትን እየገፋች ያስገባቻት።ቤት ከገቡ በኋላ ሊባኖስ ሹፌሩን
"ማርቆስ በል ቅድም መኪና ውስጥ ያስቀመጥኩትን አምጣው"
አለችው። ሹፌሩም ምንም መልስ ሳይሰጣት ወጣ። ወዲያው
በፌስታል ያለ ነገር ይዞ መጣ። ሊባኖስ ቁጭ በል ማርቆስ
አለችው። እሱ አሁንም መልስ ሳይሰጣት ቁጭ አለ። የሹፌሩ
ማረቆስ አለመናገር በፀሎት እና ፅናትን ግራ አጋብቷቸዋል።
፨በእዛች ቤት ውስጥ ሊባኖስ ፣ ፅናት እና በፀሎት ሆነው በሳቅ
እና በወሬ ድምቅ አረጉት። ማርቆስም አለ ግን ይስቃል እንጂ
አያወራም ፅናት ማርቆስን ሳታቋርጥ እያየችው ነው። አንዴም
እንኳን ሊያወራ አልቻለም። ፅናት ግራ ተጋብታ ወደ ሊባኖስ ጠጋ
ብላ "ሊቦ ቆይ ሹፌሩ ለምንድነው ምንም ሳያወራ የሚስቀው?"
አለች። ሊባኖስም " ዝም በይ አንቺ ልጅ በኋላ እነግረሻለው
አለቻት። "እሺ ሊቦ አትናደጂ ይቅርታ" አለች ፅናት ፈገግ ብላ
ሊባኖስም "ምንም አደል በቃ እኔ አሁን ልሂድ ማርቆስ በል ተነስ
እንሂድ ፅናቴ ያን ቆጠሮ ያመጣውት ለእናንተ ነው ሙዝ ብርቱካን
እና ብዙ ፍራፍሬ" አለው። ስትላት ፅናት "ውይ ሊቦ ብትነግሬኝ
ጥሩ ነበር እኮ ቀምሳቹ ትሄዱ ነበር" ስትል በፀሎትም "አዎ በቃ
ፅናቴ ቢያስ የሆነ እየሄዱ እሚበሉትን ነገር ስጫቸው" ስትል
ሊባኖስ "አይ አይሆንም በሉ በሉ ደና ዋሉ" ብላ ከማርቆስ ጋር
ሄዱ።
፨ ፅናት ማርቆስን እና ሊባኖስን እስከበር በእግሯ መኪና ውስጥ
ከገቡ በኋላ ደሞ በአይኗ ሸኝታቸው ወደ ደሳሳ ጎጆቸው
ተመለሰች።ቤት ከገባች በኋላ ፅናት ወደ በፀሎት ሄዳ "የእኔ ውድ
እህት እየውልሽ አሁን ሁለታችንም እንቅልፍ ያስፈልገናል በቃ
እንተኛ ለሊቱን ሙሉ ያሳለፍነው በቃ ቆይ ፍራሹ ላይ እንደትሆኒ
ላግዝሽና ፍራሹ ላይ ሁኔ ከዛ እቅፍቅፍ ብለን እንተኛለን" አለች
ፅናት። በፀሎትም "እሺ የእኔ ልዩ ልክ ነሽ በሩን ዝጊውና በቃ
እረፍት እናግ" አለች።ፅናት "እሺ" አለችና በፀሎትን ወደ ፍራሽዋ
እንድትወጣ ከረዳቻት በኋላ አደላድላ አስተኛቻት ከዛም በሩን
ዘግታ መጣችና።
፨ፅናት ፍራሹ ዳር ላይ ቁጭ ብላ "እህቴ በቃ አሁን ሁሉንም
እንረሳውና ጥሩ እንቅልፍ እንተኛ ከባድ ጊዜ ነበር ያሰለፍነው"
አለቻት።በፀሎትም "ልክ ነሽ እህቴ በጣም አስቀያሚ እና አስፈሪ
ነበር በቃ እንተኛ ነይ" አለችና ክንዷን ዘረጋችላት።ፅናት ፈጠን ብላ
የበፀሎትን ክንድ ተንተረሳ ፊቷን ወደ በፀሎት አዙራ ተኛች።
ብድግ ብላ በድጋሜ በፀሎትን አንገቷን ሳመቻት። በፀሎት ፈገግ
ብላ የፅናትን ጭንቅላት ሳመችው ከዛም ፀጉሯን እያሻሸች ቆየች
ከደቂቃዎች በኋላ እልም ያለ እንቅልፍ ወሰዳቸው።
ይቀጥላል
----------------------------------------------
@Sura16722
♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ
----------------------------------------
93 views18:49