2022-07-22 12:39:07
ክህደት በምክኒያት አይጠገንም! መንግስት ውሀብያን ለማንገስ የሄደበትን ርቅት እንጅ ፍትሀዊነቱን ፈጽሞ አያሳይም
.*****.
ከሰነበተ እና ሊያስገኝ ይችል የነበረውን ጥቅም ካጣ በኋላ ቢሆንም ዐቢይ አህመድ ከሱፊ እና ከመሀብያ ተወካዮች ጋር ያደረጉት የድርድር የሚያሳየው ተንቀሳቃሽ ምስል ምሽቱን በመንግስት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ለእይታ በቅቷል።
ተቆራርጦ የቀረበ... ከማለት ይልቅ የዋናው ቀረፃ ላይ ጥቂት ቁራጭ ብቻ የቀረበ ለማለት የሚያስደፍር ከመሆኑም በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለወሀብያው ቡድን አድልዎ ያላደረጉ መሆኑን እንደሚያሳዩ የታመነባቸውን ምስሎች ብቻ ተቆራርጠው መቅረባቸው ደግሞ መንግስት ወሀብያን ለማንገስ የሄደበትር ርቀት የሚያሳብቅ ነው!
በፕሮግራሙ አቅራቢዎች ትኩረት የተሰጠው እና በአድማጮች ዘንድ የጠቅላ ሚኒስትሩን ሚዛናዊ አቋምን ያሳያሉ የሚል ግምትን እንደሚያሳድሩ ንግግሮች በቀናት ውስጥ መጅሊሱን መቶ በመቶ ለወሀብያ የማስረከብ ተግባር ከፖሊሲ ስህተት በባሰ በነባሩ እስልምና ላይ የተፈፀመውን ክህደት የሚያጋልጥ ነው!
ከቅርብ አመታት ወዲህ ከወሀብያ ጋር በተያያዙ ጉዳዩች ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ነገረ ስራ የሚያስተውሉ የእስልምና ሀይማኖት ተከታይ ያልሆኑ ቀለም ቀመስ ኢትዮጵያዊያን ዘንድ ይህንን በሀይማኖቶችን የውስጥ ጉዳይ ካልቃ ከመግባት አልፎ በባለቤትነት እስከ መያዝ የደረሰን መንግስታዊ ንዝህላልነት የበዛ ትዝብት ላይ እንደሚጥል መረዳት የሚችል መንግስታዊ አካል መታጣቱም እንዲሁ ለመፍታት የዳገተ እንቆቅልሽ ሆኗል!
ወሀብያ ከኢትዮጵያ ሙስሊም የህዝብ ብዛት አኳያ አስር በመቶ አካባቢ እንደሚሆን በተጨባጭ እየታወቀ "ኑ በአንድ ላይ ላሰግዳችሁ" በሚል አባታዊ በሚመስል ጥሪ ወደ ሱፊ/ወሀቢ የሀይማኖት ንትርኮች ተቻኩለው የገቡት ዐቢይ አሕመድ በሦስ አመታት ውስጥ የነባሩን ሙስሊሞች መጅሊስ "ሀምሳ በመቶ አካፍሉ" ከሚል ቀጭን ትእዛዝ አንስቶ የመጅሊሱን ህጋዊ መስራቾች እና ባለቤቶች ሙሉ በሙሉ እስከ ማስወጣት የደረሰውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዞ የአሳፋሪ ታሪካችን አንድ አካል ሆኗል!
ዐቢይ አሕመድ ይህንን ታሪካዊ ስህተት እንዴት አድርገው ሊያርሙት እንደሚችሉ ግልፅ ባይሆንም ሀቅ ማሸነፉ፣ ቅጥፈት መንኮታኮቱ ተፈጥሯዊ ህግ ነው!
ድል ለተበደሉት መዘንበሏም እንዲሁ!!
#ኤልያስ እሸቱ
SHARE SHARE SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/stop_wahababizm
#እኔ_ኡለሞቸን_ተቋሜን_መስጅዴን_የምጠብቀው_ጀግናው_የሙፍቲ_ትውልድ_ነኝ
280 views09:39