የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
1.70K
የሰርጥ መግለጫ
#ደብተራ |Network
✝ ስብከተ ወንጌል ትምህርቶች እና ዝማሬዎች የሚለቀቁበት
✝የብራና ላይ መዛግብት የሚዳሰሱበት
✝የጉባኤ፣ የመፅሐፍ እና የመንፈሳዊ ጉዞ ማስታወቂያ የሚለቀቅበት
✝ቤተ ክርስቲያንን በተመለከተ ወቅታዊ ዜና የሚዘገብበት የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/debteranetwork
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
0
3 stars
1
2 stars
1
1 stars
1
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች
2022-04-07 12:41:38
1.8K views09:41
2021-09-27 09:19:35
የልጆች ደመራ ዝግጅት በድምቀት ተካሔደ::/አዲስ አበባ : መስከረም 16 2014 ዓ.ም./
የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም መስከረም 16 2014 ዓ.ም. ያዘጋጀው ልዩ የልጆች ደመራ ትምህርታዊ ዝግጅት ከተጠበቀው ቁጥር እጅግ የሚበዙ ሕፃናት በታደሙበት ተካሔደ፡፡ በጸሎትና በትምህርተ ወንጌል በተጀመረው በዚህ ዝግጅት ላይ የኔታ ጥዑም በአካል ተገኝተው ጣፋጭ የመስቀሉን ታሪኮች ለልጆች ተርከዋል፡፡ የቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ፈለገ ዮርዳኖስ ሰንበት ትምህርት ቤት ሕፃናትም ለእንግዶቻቸው ልዩ ልዩ የመስቀል ዝማሬን አቅርበውላቸዋል፡፡
ከመክፈቻው ዝግጅት በኋላ ለሙሉ ቀን የቀጠለው ሕፃናቱ ከተመልካችነት ወደ ተሳታፊነት የሚለወጡበት አዝናኝና አስተማሪ የሆኑ ልዩ ልዩ ውድድሮችና ሙከራዎች ነበሩ፡፡ ሕፃናቱ በዚህ ትምህርታዊ ዝግጅት ላይ በየተራ የተሳተፉ ሲሆን የዜማ መሣሪያዎችን በመሞከር፣ ሥዕል በመሣል ፣ መስቀሉን ቆፍራ ላወጣችው ለንግሥት ዕሌኒ ደብዳቤ በመጻፍና የንግሥት ዕሌኒ ተምሳሌታዊ ፎቶ በመነሣት፣ ጥያቄ እየመለሱ ችቦ በመራመድ፣ ሥዕላትን በመገጣጠም፣ ቃለ መጠይቅ በማድረግ እና በመሳሰሉ አሳታፊ ዝግጅቶች የመስቀሉን ነገር ሲማሩ ውለዋል፡፡
ሕፃናቱ በዚህ ዝግጅት እጅግ ደስታቸውን ያሳዩ ሲሆን ወላጆችም ከዚህ በኋላ ተመሳሳይ ዝግጅት የሚኖርበትን ቀን በመጠየቅ ደስታቸውን ገልጸዋል፡፡ ይህንን መሰል የሕፃናትና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችን የሚያሳትፉ ዝግጅቶችን በማዘጋጀት ላይ የሚሠራው የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ የአግናጥዮስ ፕሮጀክት ሰብሳቢዋ ሀና አድማሱ ‘ይህ ዓይነቱን የሕፃናት ዝግጅት ቢያንስ በዓመት ሦስት ጊዜ ለማካሔድ ዕቅድ እንደተያዘና ከዚህ በተጨማሪ በዐሥራዎቹ ዕድሜ ላይ ላሉ ልጆችም የታሰቡ ልዩ ልዩ አሳታፊ ዝግጅቶችም በቅርቡ ይኖራሉ’ በማለት ምላሽ ሠጥታለች፡፡
በልጆች ደመራ መርሐ ግብር ላይ ለተፈናቀሉ ወገኖችም እርዳታ ለማሰባሰብ በተደረገው ጥሪ መሠረት በርካታ ወላጆች ከልጆቻቸው ጋር አልባሳትን የሕፃናት ንጽሕና መጠበቂያዎችንና ምግቦችን ይዘው በመምጣት ከተጠበቀው በላይ እርዳታ ያደረጉ ሲሆን የኢጃት ፕሮጀክት ቂርቆስ አባላትና የማኅበረ ጽዮን አገልጋዮች በጋራ ተረክበዋል፡፡
Via--ጃንደረባው Media JOIN US ╔═════════════╗
@debteranetwork
╚═════════════╝
3.7K views06:19
2021-09-27 09:19:25
2.9K views06:19
2021-09-27 09:19:20
2.5K views06:19
2021-09-27 09:19:17
2.2K views06:19