Get Mystery Box with random crypto!

(✍ ስለ ህይወት✍)

የቴሌግራም ቻናል አርማ sle_hiwot — (✍ ስለ ህይወት✍)
የቴሌግራም ቻናል አርማ sle_hiwot — (✍ ስለ ህይወት✍)
የሰርጥ አድራሻ: @sle_hiwot
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 794
የሰርጥ መግለጫ

👉 የህይወታችን ትርጉም የሚወሰነው በኛ መኖር ውስጥ በምናኖረው አካል ነው።
ማኖር ያለብን በእኛም ሊኖር የተገባው ኢየሱስ እሱ የህይወታችን ትርጉም ነው ህይወት ኢየሱስ ነው ስለ ኢየሱስ እናወራለን ተባረኩልኝ❤🙏
ለማንኛውም አስተያየትና ሀሳብ👉 @Elsinaaaa
@sle_hiwot
@sle_hiwot

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-08 07:14:35 ኢየሱስነን ብቻ መፈለግ ...

በኢየሱስ እንደመያዝ በርሱ እንደመታቀፍ ምን ደስ የሚል ነገር አለ?
በኢየሱስ እንደመመራት ምን ደስታ አለ?
በቤቱ ውሎ ከማደር የላቀ ደስታ ምን አለ ?
የኢየሱስ ልጅ እንደመሆን ምን የሚያኮራ ነገር አለ?
እሱን እንደመፈለግ ያለ እረፍትስ የታለ?
በእውነት ደስታ ከኢየሱስ ውጪ ፍፁም አይደለም። ኢየሱስ ኢየሱስ ያለ ከመልካም ነገር አይጎድልም።

1ኛ ቆሮንቶስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ እንደዚህ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን መገለጥ ስትጠባበቁ አንድ የጸጋ ስጦታ እንኳ አይጎድልባችሁም፤
⁸ እርሱም ደግሞ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ያለ ነቀፋ እንድትሆኑ እስከ ፍጻሜ ድረስ ያጸናችኋል።
⁹ ወደ ልጁ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር የታመነ ነው።

አባ ብለን የምንጠራው የወደደን የሰበሰበን፣ ከአለም ምናምንቴ ከክፉ ምኞቷ የገላገለን ፣ በርሱ ያለንን የዘላለም ፍስሀ እንድናውቅ ያደረገን መንፈስ ቅዱስ ይክበር

"አላውቅም ሌላ ደስታ ከዚህ ውጭ
ለኔ በቃኝ አልፈልግም ሌላ አማራጭ"

https://t.me/sle_hiwot
394 viewsedited  04:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-03 22:49:55 ያለፍቅር መልካም ነገር ሊሆን አይችልም...

የትኛውም መገፋት፣ የትኛውም ችግር ሊሆን ይችላል፣ አለመግባባት ወይም ግጭት፣ ግራ መጋባት...ታክሞ ፍፁም ሊፈወስ የሚችለው በፍቅር ነው!

አጋጠመን ያልነው ያ ችግር የተባለው የቱም ነገር የቱንም ያህል ቢገዝፍ ፍቅርን ገፍተን ሌላ መድሀኒት ልናገኝለት አንችልም! በፍቅር ግን ሁሉ ይዋባል!

በኑሮ ሂደታችን ውስጥ ለሚያጋጥመን አንዳንድ ወጀብ ግራና ቀኝ መቀላወጥ ሳይጠበቅብን በፍቅር ብቻ ችግሩን እንደምንፈታው ማሰብ አለብን!

ሁሉን በፍቅር ወደማድረግ ማደግ!


@sle_hiwot @sle_hiwot
@sle_hiwot @sle_hiwot
413 views19:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-19 21:26:22 ለብር አይኖርም በብር አይኖርም

የገንዘብ ብዛት ሲመጣ የአንተም ስብዕና በቃሉ ተቃኝቶ የበሰለ ማንነትና እይታ ሲኖርህ፣ ማስተዋል ስትችል ዛሬን ብቻ ተኖሮ ምድር ላይ የማያልቅ ህይወት እንዳለህና የድንኳን ኑሮህ የሆነ ሰአት የሚያበቃ እንደሆነ ተገንዝበህ የሰማዩን አሳቢ አርቆ ተመልካች ስትሆን ጥሩ ነው

ሁሉ የጌታ እንደሆነ ካልገባህና በገንዘቡ መመካት ከጀመርክ ከሰው በላይ እንደሆንክ ከተሰማህና ከተጠንጠባረርክ መጨረሻህ አስከፊ ነው

ለገንዘብ መንገብገብ ለገንዘብ መኖር ገንዘብን ማሳደድ ክፉ በሽታ ነው ጌታን ሲጀመር ገንዘብ ፈልጎህ ይምጣ እንጂ እሱን ለመያዝ ስትሯሯጥ አመድህ መውጣት አለበት እንዴ ሆሆይ

ጌታ ያለብሰኛል ጌታ ያበላኛል ጌታ ያጠጣኛል በል በርሱ ታመን ያኔ ቅብርር ደልቀቅ አርጎ ያለስጋት ያኖርሀል ከዛ ውጪ ብር ብር ስትል ከቤቱ በረህ ጠፍተህ የብሩ ተገዢ ትሆን እንዴ አንድ ባሪያ ለሁለት ጌቶች አይገዛም ወገኔ ወደ ራዕይህ አተኩር

ሀብት ማካበት ራዕይ ሆኖ አያውቅም ገንዘብ ወዳድነት የጠላት ማጥመጃ እንጂ የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም

ለጌታ ስትኖርለት ለሱ ስትገዛለት ሁሉ ላንተ ተገዝቶልሀል ወዲያና ወዲህ መንቀላጠጥ አይጠበቅብህም ስታገለግለው ራሱ መንገዱን ይጠርጋል የሚያስፈልግህን ያዘጋጃል ሁሉን አመቻችቶ ይሰራልሀል ፍፃሜህ ይዋባል

ግን በአቋራጭ ብር ሰብስበህ ሰብስበህ ትፈነዳታለህ እንጂ ህይወት አይሆንህም የገንዘብ ብዛት አንተ ጋር ቢታጨቅ ስኬታማ የሆንክ የመሰለህ ካለህ ሞኝ ነህ ጌታን

ሲጀመር ለአማኝ ብር ብርቁ አይደለም መሆንም የለበትም! ነፍሱን የሰጠህ ጌታ አንተን ማኖር ያቅተዋል እንዴ? የምን መንቀላጠጥ ነው

ከዛም ከዚህም አግበስብሼ እበላለሁ ብትል አንቆ ይገድልሀል ሲጎረስም በመጠኑ በስርአቱ ነው ........

ጌታን እመነው ፅና ፊቱን ፈልግ ወደሱ ብቻ ተጠጋ ሁሉን ለሱ ክብር አድርገው ከዛ ታየዋለህ አባትህ ልጅ እንጂ እንጀራ ልጅ አላደረገህም የሚነፍግህ ነገር አይኖርም

ለመንጠባረርና በድሀ ላይ ለመንቦራራት ከሆነ ብሩም አንተ ጋር አይመጣም ቢመጣም አይሰነብትም ያዋርድሀል ግን ሁሉን ስትፈልግና ስትጠይቅ ለጌታ ክብር ለሰዎች ጥቅም ይሁን ያኔ የጠየከውን ጌታ ይሰጥሀል


ሉቃስ 12 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁸ እንግዲህ እግዚአብሔር ዛሬ ታይቶ ነገ ወደ እሳት የሚጣለውን የሜዳ ሣር እንዲህ የሚያለብስ ከሆነ፣ እናንተ እምነት የጐደላችሁ፣ እናንተንማ እንዴት አብልጦ አያለብሳችሁም?
²⁹ ስለዚህ ምን እንደምትበሉና ምን እንደምትጠጡ በመሻት ልባችሁ አይጨነቅ፤
³⁰ ይህንማ በዓለም ያለ ሕዝብ ሁሉ ይፈልጋል፤ አባታችሁ እኮ ይህ ሁሉ እንደሚያስፈልጋችሁ ያውቃል።
³¹ ይልቁንስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ፈልጉ፤ ይህም ሁሉ በተጨማሪ ይሰጣችኋል።

ሁለንተናችሁን ለእግዚአብሔር አሳልፋቹ የሰጣቹ የምትሆኑበት ፀጋ ይብዛላችሁ የእግዚአብሔር ሀሳብ ሀሳባችሁ ላይ ይላቅ

እወዳድዳችኋለሁ መልካም ቆይታ


@sle_hiwot @sle_hiwot
@sle_hiwot @sle_hiwot
503 views18:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-15 11:36:49 ማስመሰል ትንሽ ቀን ያማረ ቢመስል አያዘልቅም መሀል ላይ አዙሮ ይደፋል!

ቤተክርስትያን ውስጥ አስመስሎ መኖር ገለባው ከስንዴው የሚለይበት ጊዜ የመጣ ለታ የእሳት እራት መሆን ነው ትርፉ! ........

አካሄድን መመዘን ዙሪያን መቃኘት አይከፋም! ...ደና ቆዩልኝማ


@sle_hiwot @sle_hiwot
454 views08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-15 07:27:55 ያላስጀመራችሁ ሊያጨነግፋቹ ሲሞክር ጌታን ስቃችሁበት እለፋት! ማንም ቢሆን

ከኢየሱስ ጋር ጀምረህ እንደሁ ስለፍፃሜህ ስጋት አይግባህ ማንም እንቅፋት ሆኖ መንገድ ላይ አያስቆምህም።።"ኢየሱስ አስጀምሮኛል ኢየሱስ በክብር ከግብ ያደርሰኛል" በል የስንፍና ቃል ከአንተ አይሰማ!

ያላስጀመረህ አንተን ማጨንገፍ አይችልምኮ በኢየሱስ የተጀመረውን የሆነ ስልጣን ያለው ሰው ችሎ በሰዋዊ በጥበቡ ከፍፃሜው ሊያስቀረው አይችልም።

በአንዳንድ ሁኔታ ልባችን መውረድ የለበትም ህልሙን የሰጠን ጌታ እያለ በአዋካቢዎች ወይም በኛ ህልም በቀኑት አካሎች እንደቀልድ ከግባችን የምንቀር አይደለንም!

"እንዴ እኔኮ የዋዛ አይደለሁም" እንበል በያዘን ኢየሱስማ እርግጠኛ እንሁን ብቻ ምክሩን እንስማውና እንጠጋው እንደፈቃድህ እንበለው እንጂ እሱ መች ጭንገፋ ያቀውና ፣ መች መሀል መንገድ ላይ ይደክምና

ራሳቸውን፣ፈቃዳቸውን፣ኑሮአቸውን፣ዘመናቸውን ቅዱስ መስዋዕት ላደረጉለት እሱ መች ይተዋቸዋል

እሱን እሱን ተርቦ ቤቱን ቤቱን ብሎ፣ ኢየሱስ ኢየሱስ ሲል ከርሞ ከመልካም ነገር የጎደለ ሰው አላውቅም እሱ በእውነት ለሚሹት የስጋ መሻታቸውን አለምን ጥለው ክብሩን ክብሩን ላሉት ችላ ብሏቸው አላየሁም ።

እናላችሁ ትናንት ከጌታ ጋር ጀምራችሁ አሁን ሁኔታዎች ከብደዋችሁ መንገድ ላይ ልትቀሩ የመሰላችሁ ሰዎች አይዟችሁ የጠራችሁ አምላክ ታማኝ ነው። አይገርማችሁም ታላቅ አዋቂ በምትሉት ሰው በኩል ራሱ ህልማችሁ ሊናቅባችሁ ይችላል ግን ለዮሴፍ ህልም የሰጠው ጌታ አካል ሳያሲዝላችሁ አይቀርም።

በዘመናት መካከል በመጠቢቂያቸው ለጠበቁት እምቢ ለሀጢአት ፣ እምቢ ለአለም ላሉት ጌታ ከክብሩና ከሹመቱ ጥግ ሳያደርሳቸው አይቀርም ብቻ እናስቀድመው እነጂ መንገዳችን ያማረ ነው።

እንደ ዮሴፍ እግዚአብሔር ላይ ብቻ የሙጥኝ የምትሉበት ከእርሱ ውጪ ለአለም መሻች የማትነካኩ ሆናችሁ የምትፀኑበት ፀጋ ይብዛላችሁ

ጌታ ይወዳችኋል እኔም እወዳድዳችኋለሁ ደህና ቆዩልኝማ

@sle_hiwot @sle_hiwot
@sle_hiwot @sle_hiwot
441 views04:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-11 21:11:55 እኛ የድሮ ዝማሬ ብቻ ወደን የድሮ ስብከት ወደን የድሮ የድሮ ብቻ ወደን ወዴት እያመራን ነው

አስቡት እስኪ መቼስ መውለዳችን አይቀርም እኛስ ልጆቻችን ዘወር ብለው ሊያደንቁት ሊወዱት የሚችሉት ነገር ምን አስቀምጠንላቸዋል የኛ ዘመን ሲታወስ ምንድነው አብሮ የሚታወሰው ምን ያህል የተሻለ ነገር ሰሪዎች መሆን ችለናል?

እግዚአብሔር የሰጠንን የወንጌል አደራ ምን ያህል ፈፀምነው? ትውልድ ስለኢየሱስ ከኛ ዘመን ምንድነው የሚሰማው? በዚህ በተደበላለቀ ክፉ ጊዜ የኛ የእረፍት ወንጌል ምን ያህል እረፍትነቱ ለአህዛብ ታየ? ከኛ ዘንድ አለም ምንድነው የሚሰማው? የእግዚአብሔር ቤት አስፈሪነቱስ የቱ ጋር ደረሰ አንተና እኔ በቤቱ ሆነን ሀላፊነታችንን እየተወጣን ነው ወይ? ሰው እኛን አይቶ ኢየሱስን ወይስ ሌላ ነገርን አየ?

በጊዜአችን ምን ያህል ተጠቅመናል? ፌዝ ነው ወይስ የእረፍት ቃል ያስቀመጥንላቸው? ለትውልድ የምናስረክበው ወንጌል ምን ያህል የጠራ የነጣ የፈካ ነው? ምን አይነት ክርስትናን ነው እያስቀጠልን ያለነው?

የተደበላለቀ የተቀያየጠ ውሉ የጠፋበትን ህይወት ኖሮ ለቀጣይ ትውልድም እንቅፋት ከመሆን ጌታ ይጠብቀን።

የኛ ስህተት ክፋቱ እኛን ብቻ አይጎዳም ይሸጋገራል የነገውም ትውልድ የድንግዝግዝ ኑሮ ባለቤት ለምን ይሁን?እምቢ ለሃጢኣት ? እምቢ ለአለም? እምቢ ለማጭበርበር? እምቢ ለሌብነት? የሚሉ ክርስትያኖች እንሁን!

ቅዱሱን ቃል በቅዱሱ መንፈስ እየተረዳን ሌላ ሳንጨምር ከክብር ወደክብር የምናድግ ፣ በስርአት አልበኝነት ተዘፍቆ አልቅጥ ከተሳከረ የቅዠት ህይወት ወጥተን በትክክለኛው መንገድ የምንጓዝ፣የጌታን ስም በየእለት ኑሮአችን በአገልግሎታችን የማናሰድብ ስሙን የማናቀልል፣ እግዚአብሔርን የምንፈራ በቅድስናችን የማንደራደር፣ የተረጋጋን የሰላም ሰዎች፣ በወርቅ የተለበጠ ሸክላ አይነት ሳይሆን የነጠረ ህይወት ያለን እውነተኛ ክርስትያን እንሁን።

ራእይ 22
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ።


²¹ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን።
እወዳድዳችኋለሁ መልካም ቆይታ

@sle_hiwot @sle_hiwot
@sle_hiwot @sle_hiwot
433 views18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-10 21:07:45 "1ሚሊየን ብር ስጪኝና ጴንጤ እሆናለሁ" ቢለኝ ብዙ ነገር አሰብኩኝ _እውነት እንደው ማስተዋል ቢያቅተው እንጂ ስንትና ስንት ቢልዮን ዶላር ቢሰበሰብ የማይከፍለውን እዳውን ኢየሱስ ራሱን መስዋዕት አድርጎ ነፍሱን ያዳነለት ጌታ ቅራቅንቦ ብር ይቸግረዋል ብሎ ማሰቡ አይገርምም

አረ ተው ግድ የለህም ኢየሱስ በአንዳንድ ነገሮች አይጠረጠርም እሱን በገንዘብ አትተምነው ራሱን ሰጥቶህ የለ እንዴ እንኳን በአይን የሚታየውን ኮተት

ስማኝማክ ነፍሱን የሰጠህ ጌታ ፣ያኖረህ ጌታ እንዴት ሌላውን ይነፍግሀል ሁሉ በኢየሱስ እኮ ሙሉ ነው

የምድር ባለጠጎች ሀብታቸው ቢሰበሰብ የነፍሳችንን እዳ መክፈል ችሎ የዘላለም ህይወትና እረፍት አይሰጠንም ።

ማቴዎስ 6 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³¹ ስለዚህ፣ ‘ምን እንበላለን? ምን እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን?’ ብላችሁ አትጨነቁ፤
³² አሕዛብ እነዚህን ነገሮች ሁሉ ለማግኘት ይጨነቃሉና፤ የሰማዩ አባታችሁም እነዚህ ሁሉ ለእናንተ እንደሚያ ስፈልጓችሁ ያውቃል።
³³ ከሁሉ አስቀድማችሁ ግን የእግዚአብሔርን መንግሥትና ጽድቁን እሹ፤ እነዚህ ሁሉ ይጨመሩላችኋል።

አትጨናነቅ ወዳጄ ሚስጥሩን ብትረዳው ይሻልሀል

ኢየሱስን በፈቃዳችን ወደህይወታችን ስናስገባ ግን ሁሉም አለን። የጎደለ ነገር በእግዚአብሔር አለም የለም ። "ብቻ ፅድቅና መንግስቱን ፈልጉ እንጂ ሌላው ይጨመርላችኋል " ይል የለ ቅዱስ ቃሉ በቃ እሱን ብቻ ይዞ መቀጠል ነው ሌላው አያሳስብም

ግን አንድ እውነት አለ በኢየሱስ ክርስቶስ እንዲሁ በነፃ የዘላለም ህይወትን አግኝተናል ይህ ዕረፍት ለተቀበሉት ሁሉ በስሙም ለሚያምኑት እንዲሁ በነፃ ተሰጥቷል

የእግዚአብሔር ማዳን አያልቅም ኢየሱስ የሞተው ዋጋ የከፈለው ለአለም ሁሉ ነው ለኔም ላንተም ለእናንተም ኢየሱስ ሞቶልናል በትንሳኤውም ሞትን ድል አድርጎ ሲነሳ የኛን ሞት ነው የሻረው

እኛ የምንም እዳ የለብንም በሞቱ ሞትን አሸንፈናል በስጋ ስናንቀላፋ የተዘጋጀልን ያማረ ቤት በሰማይ አለ በምድርም የሚያሳስበን አንዳች ነገር የለም ሁሉም ተፈፅሟል ህይወታችን የደስታ ነው

በሚያስጨንቀው አለም ውስጥ ሆነን ግን በውስጣችን ባለው ኢየሱስ በብዙ ዕረፍትና ስኬት እንኖራለን

የጨለምተኝነት ህይወት የለንም እንደውም እናንተ የአለም ብርሀን ናችሁ ተብለናል እናበራለን እንጂ አይጨልምብንም።
ብርሀንን የሚያሸንፍ ጨለማ የለምና በአሸናፊነት እንመላለስ ዘንድ በክርስቶስ የተሰጠን ማንነት የፈካ ነው።

ጌታ ይወዳችኋል እኔም እወዳድዳችኋለሁ ደህና ቆዩልኝማ

@sle_hiwot @sle_hiwot
@sle_hiwot @sle_hiwot
415 views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-05 20:28:12 ጌታ ሰው አለው


ሰውን በሚያወዛግብ መልኩ በተነሳው ሰሞንኛ ነፋስ ኢየሱስ አይለካም ትውልድ እውነተኛ በሆነ መንገድ እውነት የሆነውን ወንጌል የሚሰማበት ጊዜ ሩቅ አይደለም.......በሀሰት ያልተለበጠ ከምንም ነገር ጋር ያልተቀያየጠ ንፁህ ወንጌል፣ መፍትሄ የሚያመጣ በወንጌል ስም ታጅቦ ግራ የማያጋባ የእረፍት ድምፅ ከሆነ አቅጣጫ ይሰማል......በምድር ላይ ኢየሱስ የሚባለው ስም የሚከብድበት ጊዜ ቅርብ ነው

እንዳትሞኙ ተስፋ እንዳትቆርጡ ግድ የላችሁም

እግዚአብሔር ልጆች አሉት ለእውነት ብቻ የጨከኑ ለስጋ ፈቃዳቸው ብለው ፈቃዱን የማይረሱ ለሱ ብቻ የተለዩ ልጆች አሉት ....በፊትም ነበሩት አሁንም አሉት ወደፊትም የተለዩ አሉት ....ብዙ ተስፋ አለኝ

ከነዛ መካከል ነኝ የሚል ጉዞውን ይቀጥላል በዚህ ዘመንማ ማገልገል ያስጠላል አይባልም እንደውም በዚህ ዘመን ነው እንጂ ማገልገልማ አንተ

ኢየሱስ የማይከብርበትን ወሬ በቃ የሚል፣ ከተከላለሰ የጡዘት መንደር እምቢ ብሎ የወጣ የክርስቶስን ክብር የሚያብለጨልጭ ፣ የእግዚአብሔርን ህዝብ በትጋት የሚያገለግል በህዝቡ ለመጠቀም ሳይሆን ህዝቡን ለመጥቀም የሚራብ፣ የዲያብሎስን መንግስት የሚያናውጥ፣ የቱም እንቅፋት ሊያቆመው የማይችል፣ የኢየሱስን ስም የማያቀልል፣ የክርስቶስን የማስፈራቱን ክብር የምናይበት መቅደሱ ላይ የማያፌዝ ቆራጥ ፣ ራሱን ለእግዚአብሔር መንግስት ሙሉ በሙሉ የሰዋ የእውነት አርበኛ እንዳለ እርግጠኛ ነኝ

ጌታ ቤቱን ያጠራል ገለባው ከፍሬው ይለያል ስሙን ያረከሰ አካል ከቤቱ ይጠረጋል መቅደሱ አይቀልልም ፣የቤተክርስቲያን ማስፈራትና ሞገሷ በሀይል ይታያል ፣ ቸርች ሲባል ጆሮ ላይ አይቀልልም፣ ጌታ ዝም ሲል በማጭበርበሩ ቀጥልበት ያለው ይመስል ሲያጭበረብር የኖረ ሁሉ ጊዜው የሚያከትምበት ጊዜ ሩቅ አይደለም
የክርስቶስ ክብር ሲገለጥ ይህ አለመሆን አይችልም ሀሰትና እውነት ይለያል

የኢየሱስ ስም የማይዘበትበት ቅዱስ ቃሉ ብቻ የሚከበርበት የሰው ሀሳብ ከገነነበት ቦታ የሚወርድበት ፣ በብልጣብልጥነት የማይኖርበት አደባባዮች ሁሉ ለስሙ የሚንቀጠቀጡበት ጊዜ ቅርብ ነው

ኤርምያስ 32 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁹ ለእነርሱና ከእነርሱም በኋላ ለልጆቻቸው መልካም እንዲሆንላቸው ዘወትር ይፈሩኝ ዘንድ፣ አንድ ልብ አንድም ሐሳብ እሰጣቸዋለሁ።
⁴⁰ መልካምን ነገር ለእነርሱ ከማድረግ እንዳልቈ ጠብና ከእኔም ፈቀቅ እንዳይሉ መፈራቴን በውስጣቸው ላኖር ከእነርሱ ጋር የዘላለም ቃል ኪዳን እገባለሁ።


እወዳድዳችኋለሁ መልካም ቆይታ


@sle_hiwot @sle_hiwot
@sle_hiwot @sle_hiwot
481 views17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-31 15:26:55 ራዕያችን ጋር ለመድርስ አሁን ጌታ እኛን እያስኬደበት ያለበትን ሁኔታና መንገድ እኛ እየተማርንበት አምነንበት እየሄድን ግን ደሞ ባናቱ ደርሶ ጉዞአችንን ከሚያንኳስስና መንፈስ ቅዱስ በነገረን አካሄድ ከሚያፌዝና በሌላ መልኩ ሊደልለን ከሚናፍቅ ሰው ጋር ድርድር የለም መራቅ ብቻ ነው መፍትሄው እናንተዬ አለዛ ሩጫችንን ሳንጨርስ ያቆረቁዘናል ወይ የአገዳ እሳት ያደርገናል የሚመክረንን የሚያወራንን መንፈስ አላስነካም ማለት መልካም ነው

እየተለየን እያስተዋልን እሺ RUN RUN ደና ቆዩልኝማ

@sle_hiwot @sle_hiwot
@sle_hiwot @sle_hiwot
461 viewsedited  12:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-25 13:16:23 እውነተኛ መሪ

እውነተኛው መሪ አቅጣጫ ጠቋሚና ትክክለኛ መንገድ ቀያሽ እግዚአብሔር ብቻ ነው የሚመክረንም በቃሉ ነው ቃሉ ደሞ ራሱ እግዚአብሔር ነው ሊል የፈለገውን ለኛ የሚያስተጋባው በቃሉ በኩል ነው .......... ቃሉን መሰረት ያላደረገ እንዲሁም ቃሉን አንሻፎ ስብከትም እምነትም ለኛ ሊያጋራን የፈለገ አካል ካለ መጠንቀቅ አለብን

ሰው የሰውን ምክር ሲሰማና ሲያደርገው ይሆንልኝ ይሆናል፣ ያስኬደኝ ይሆናል፣ መድረሻ ይሆነኝ ይሆናል ብሎ ነው ግን ደሞ የሰው ምክር ሰው ለያዘው ህልም ትክክለኛ መድረሻ መንገድን አይጠቁምም (ምናልባት በመንገዳችን የሆነ ቦታ ጌታ በሰው ይጠቀምና ሰውን ሰበብ አድርጎ የሆነ ነገር ያደርጋል)

ጌታ እሱ ሲመክር ሳይወዛገብ ሳይገምት በትክክለኛው መንገድ ነው ፣እሱ ሲመክር ከድል መድረሻችንን አውቆ ነው ፣እሱ ሲመክር እንዳንወድቅና እንቅፋት እንዳይጥለን ነው፣ ........የሚበጀንን የሚያስተምር መሄድ በሚገባን ቦታ የሚያራምደን የእግሮቻችንን እርምጃ የሚያስተካክል ወደተፈለገው የኛ መድረሻ በጊዜውና በሰአቱ የሚያደርስ እሱ የእግዚአብሔር ምክር የአምላክ መሪነት ነው።

ጌታ እየመራን ባለንበት ጉዞ "ከመሀል ወድቄ እቀር ይሆን?" የሚባል ስጋት የለም ከግባችን እንደሚያደርሰን እርግጠኛ የምንሆንበት መሪ እግዚአብሔር ብቻ ነው
እውነተኛ መሪ ኢየሱስ
ትክክለኛ መካሪ/አስተማሪ የእግዚአብሔር ቃል

እግዚአብሔር ያስጀመረውን ሰው አያስቆመውም
እግዚአብሔር ያስጀመረውን ተምችና ኩብኩባ አያጨነግፈውም ጌታ እንዳስጀመረን እርግጠኛ ከሆንን እንደሚያስጨርሰንም ምንም ጥርጥር የለንም እሱ የሚመራን ህልማችንን ሊያጨነግፍ ና መሀል ላይ ሊጥለን ሳይሆን ከግብ ሊያደርስ ነው።

“የተቤዠህ፣ የእስራኤል ቅዱስ፣ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “እኔ እግዚአብሔር አምላክህ፣ የሚበጅህ ምን እንደሆነ የማስተምርህ፣ መሄድ በሚገባህ መንገድ የምመራህ ነኝ።”
— ኢሳይያስ 48፥17 (አዲሱ መ.ት)

እና በያዘን ጌታ እርግጠኛ ሆነን እንከተለው የሚመራን እሱ የት እንደሚያደርሰንና በየት በኩል እንደሚያደርሰን ያውቃል ሩጫችሁን ቀጥሉ በርቱልኝ እላችኋለሁ የአምላኬ ፀጋ በነገር ሁሉ ያበርታችሁ

የምታገለግሉም ደስ እያላችሁ አገልግሉት በአንዳንድ ሁኔታዎች ትኩረታችሁ ከመሪያችሁ ላይ ወደሁኔታው እንዳያዘነብል አካሄዳችሁን መዝኑ

እወዳድዳችኋለሁ መልካም ቆይታ

@sle_hiwot @sle_hiwot
@sle_hiwot @sle_hiwot
536 views10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ