Get Mystery Box with random crypto!

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ፦ የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በደቡብ ክልል 6 ዞኖችና 5 ልዩ | Skyline media

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ፦

የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በደቡብ ክልል 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች በአንድ የጋራ ክልል ለመደራጀት ያካሄዱትን የህዝበ ውሳኔ ውጤት በሙሉ ድምፅ አጸድቋል።

ይህም ማለት በኢትዮጵያ 12ኛው ክልል እንዲደራጃ ይሁንታ ሰጥቷል።

በዚህም መሠረት ፦

ላለፉት 30 ዓመታት ገደማ በደቡብ ክልል ሥር ሲተዳደሩ የቆዩት ፦
የዎላይታ ፣
የጋሞ ፣
የጎፋ ፤
የኮንሶ ፣
የደቡብ ኦሞ ፣
የጌዲኦ ዞኖች እንዲሁም
የአማሮ ፣
የቡርጂ ፣
የደራሼ ፣
የአሌ እና የባስኬቶ ልዩ ወረዳዎች የፌዴራል ሪፐብሊኩ 12ኛ ክልል ሆነው " ደቡብ ኢትዮጵያ " በሚል እንዲደራጁ ምክር ቤቱ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

በሌላ በኩል ፦
የሃድያ ፣
የከንባታ ጠንባሮ ፣
የሀላባ ፣
የሥልጤ ፣
የጉራጌ ዞኖችና እና የየም ልዩ ወረዳ ራሳቸውን መልሰው በማደራጀት #በነባሩ ክልል እንዲቀጥሉ ሲል ምክር ቤቱ ወስኗል።