Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮጵያ በይፋ የ5G ኔትወርክ አገልግሎትን አስጀመረች የተቋሙ ስራ አስፈጻሚ ወ/ት ፍሬህይወት | SMN TV1

ኢትዮጵያ በይፋ የ5G ኔትወርክ አገልግሎትን አስጀመረች

የተቋሙ ስራ አስፈጻሚ ወ/ት ፍሬህይወት ታምሩ የ5G ኔትወርክን በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል በይፋ አስጀምረዋል።

ይህ አገልግሎት ደበኞች ባንዴ ብዙ የኔትወርክ አገልግሎት የሚሰጥ እና ከመደበኛው የኔትወርክ አገልግሎት 20 እጥፍ አገልግሎት ይሰጣል። ዛሬ የተጀመረው ይህ የ5G ኔትወርክ በቻይናው ህዋዌ የቴሌኮም ኩባንያ እንደተገነባ ተገልጿል። የሰዎችን ከማሽን ጋር እንዲሁም ማሽኖችን ከሰዎች ጋር በቀላሉ በማገናኘት ምርትማነትን ያቀላጥፋል። የ5G ኔትወርክ አገልግሎት አሰራሮችን በቀላሉ እንዲቀላጠፉ የሰውን ልጅ ህይወት ቀላል ያደርጋልም ተብሏል።

የ5G ኔትወርክ ደንበኞች በሰከንድ እስከ 10 ጊጋ ባይት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲያገኙም እንደሚያደርግም ስራ አስፈጻሚዋ ተናግረዋል። ይህ አዲስ አገልግሎት በተለይም አገልግሎቶችን በርቀት በሮቦቲክስ ቴክኖሎጂ እንዲሰጡ ያደርጋሉም ተብሏል።

ይህ የ5G ኔትወርክ በአዲስ አበባ የተመረጡ ቦታዎች ለደንበኞች ክፍት የሆኑ ሲሆን በቀጣይ አንድ ዓመት ውስጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ 150 የ5G ኔትወርክ ቀጠናዎች ይከፈታሉ ሲል ወይዘሪት ፍሬህይወት ገልጸዋል።የአገልግሎቱ ተግባራዊ መሆን ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ነው በመርሐ ግብሩ የተገለጸው፡፡
@SidaamaMediaNetwork

@SidaamaMediaNetwork