Get Mystery Box with random crypto!

' ኢቫንጀሊካል ቲቪ ' የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ኢቫንጀሊካል ቲቪ  | Agape Love❤

" ኢቫንጀሊካል ቲቪ "

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ኢቫንጀሊካል ቲቪ  ነሃሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም የሙከራ ስርጭት እንደሚጀምር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መልዕክት አሳውቋል።

የቴሌቪዥን ጣቢያው በቄስ ዶክተር ገመቺስ ደሰታ ባለቤትነት ስር የነበረ ሲሆን በቅርቡ ለኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብተክርስቲያናት ካውንስል ተበርክቷል።

ለ4 አመታት ያህል የስርጭት ላይ ቆይቶ የነበረው ጣቢያው ለ1 አመት ያህል ስርጭቱ ተቋርጦ ከቆየ በኃላ ወደ አየር ተመልሶ ነሃሴ 26/2014 ዓ.ም የሙከራ ስርጭቱን እንደሚጀምር ተገልጿል።

መስከረም 15 ቀን 2015 ዓ.ም ደግሞ መደበኛ ስርጭቱን ይጀምራልም ተብሏል።

ኢቫንጀሊካል ቲቪ መደበኛ ስርጭቱን ሲጀምር ልዩ ልዩ ትምህርቶች፥ ስብከቶች፥ ወቅታዊ ዝግጀቶች፥ ቶክ ሾዎች፥ እለታዊ ዜናዎችን ጨምሮ የተለያዩ አስተማሪና ገንቢ ዝግጅቶችን ለተመልካቾቹ እንደሚያቀርብ ለቲክቫህ በላከው መልዕክት ገልጿል።

የጣቢያው ስርጭት በኢትዮ ሳት- Frequency  11105  - Symbol rate 45000 - Polarization Horizontal እንደሚተላለፍም ተጠቁሟል።

@tikvahethiopia