2022-10-30 23:21:55
በድርድሩ ላይ የተሰሙ ጭምጭምታዎች
የኢትዮጵያ መንግስት ግጭት በአፋጣኝ ማቆም በህወሓት የቀረበውን እንደሚቀበል አሳውቆ፣ ሆኖም የትግራይ መከላከያ ሀይል (TDF) የሚባል አካል መኖር የለበትም። በአንድ ሀገር ሁለት መከላከያ ሀይል ለኢትጵያ የግዛት አንድነት አደጋ ነው።
የእርዳታ እህል የኢትዮጵያ መንግስት በራሱ መንገድ ያቀርባል። ከዚህ ቀደም ነዳጅና እርዳታ ለጦርነት መጠቀሙ ከግምት ስናስገባ አሁንም አራተኛ ዙር ጥቃት ይከፍትብናል። ባንክና ኤሌክትሪክ አገልግሎት ይቀርባል። ትህነግ ለፌዴራል ሰራተኞች ዋስትና ይስጥ።
ወልቃይት በተመለከተ የተካረረ ፀብ ቀረሽ ጭቅጭቅ ተካሂዷል።
ትህነግ ከጦርነቱ በፊት ወደነበረበት ይመለስ ስትል፣
የኢትዮጵያ መንግስት ለብሄራዊ የግዛት አንድነቴ አደጋ የሆነ ኮሪደርን አሳልፌ አልሰጥም።
ትህነግ
በህገመንግስቱ መሰረት ምዕራብ ትግራይ ነበረ። ይመለስ።
ኢትዮጵያ
ህገመንግስቱን የመይቀበል አካል ህገመንግስቱን መጥቀስ አይችልም። ከህገመንግስት ውጪ ምርጫ ያደረገ፣ የሀገር መከላከያ ያጠቃ፣ በሱዳን በኩል በተደጋጋሚ ሀገር የወረረ አካል ህገመንግስት የማንሳት ሞራል የለውም።
ወልቃይት የነሱ ቢሆን ኖሮ ማይካድራ ላይ አማራን ጨፍጭፎ አይወጣም ነበረ። ወልቃይትን ለትህነግ መስጠት ማለት በብቀላ አማራን ማስጨፍጨፍ፣ በውጪ መሳሪያ የገፍ እገዛ ኢትዮጵያን ማድማት ነው።
(በሌላ አነጋገር የግብፅ ጎሮቤት እንደ መሆን ነው)
ወያኔ
ለደረሰብን ውድመት ካሳ ያስፈልገናል
ኢትዮጵያ
የሰሜን እዝ ወታደሮች፣ የአማራና አፋር ምድርን በደም ላጨቀያችሁት ካሳ ትከፍላላችሁ
ሌሎች ነጥቦች ላይም የተካረረ ንትርክ ነበረ ተብሏል።
ምንጭ፦Muktarovich
872 views20:21