Get Mystery Box with random crypto!

ሰንፔር ሚዲያ Sapphire Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ senpareadisketemafgc — ሰንፔር ሚዲያ Sapphire Media
የቴሌግራም ቻናል አርማ senpareadisketemafgc — ሰንፔር ሚዲያ Sapphire Media
የሰርጥ አድራሻ: @senpareadisketemafgc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 464
የሰርጥ መግለጫ

መንፈሳዊ መጣጥፎችን ግጥሞችን ወጎችን አጫጭር ልቦለዶች አስደናቂ ታሪኮችን ትምህርታዊ ፅሁፎችን ለማግኘት ይቀላቀሉን።
"ትውልድ ሆይ ወደ እግዚአብሔር ቃልና ወደ ተሰቀለው ክርስቶስ ተመልከቱ!!!"
https://youtu.be/KRKo3x7iYNw
http://Instagram.com/sapphiremedia4god
tiktok.com/@sapphiremedia1

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-05 05:54:48 የነፍስ ሽንቁር

"መንነህ ከበረሓ ግባ የሚያሰኝ ብዙ ነገር አለ፡፡ ርግጥ እንደ አተያይህ፣ እንደ አሰማምህ ነው፡፡ ሐሰትን እያላመጡ እውነትን በአደባባይ ማረድ፣. . . ወጣሪ ጥያቄዎችን መሸሽ፣. . . የህሊናን እሪታ፡-- በሳቅ፣ በሜም፣ በቀልድ፣ በኮሚክ፣ በሙድ፣ በሐሜት፣ ፀጥ፣ ጭጭ፣ ዝም ማሰኘት፣. . . በስውር አጉብጦ የሚያዳፋንን የሐጢያት ሸክም ያለ አንዳች መወቀስ እና ሰቀቀን አሻምኖ ተሸክሞ መኖር፣. . . ያገጠጡ ቅሌቶቻችንን በገንዘብ ሐይል ተቆጣጥሮ በሰላም መውጣት፣ በሰላም መግባት፣. . . አለመፀለይን፣ አለመቀደስን፣ ቃሉን በግል አለማንበብን ሳያቋርጡ መለማመድ፣. . . ሌላም ሌላም፡፡ ካንጀት-ላንጀት እናውራ ካልን የውድቀታችን ከረጢጥ ቢፈታ ንፍገት ያፈነው ጥፋታችን ከነጓጓላው ተቦትርፎ ይንፎለፎላል፡፡

በተለይም ደ’ሞ ብዙ ልብ ነዛሪ፣ ቅስም ሰባሪ፣ አንገት አስደፊ ውድቀቶች መሰወር [ጠብቆ] አቅቷቸው የአደባባይ ሚስጥር ይሆኑና ሳይውል ሳያድር ወዲያው በነጋታው ተዘንግተው ሕይወት ከቆመችበት የምትቀጥለው ነገር ሌላው ጨናቂ ጉዳይ ነው፡፡

ብቻ ስም ሊሰጠው የሚገባ አንድ እንግዳ የሆነ የ ‘’ክርስትና’’ ሕይወት በየአደባባዩ እያናፋ ሲሄድ ይታየኛል። ከቅዱሳት መፅሐፍት ጋር የተሳሰርንባቸውን የትምህርት ክሮች በጣጥሶ ከአንድ ሰብኮ-አዳሪ ከንፈር ስር በሚወጡ ግላዊ ሐሳቦች ላይ የእምነት ጎጆችንን እንድንቀልስ የሚያደርግ ለዘብተኛነት [Liberalism] እና አጥን-ለግለሰብ [Personality cult] ፡፡

ብዙ ያልተደፈነ የነፍስ ሽንቁር አለ። እጅን ደረት ላይ አሳርፎ "የመስቀሉን አሁንነት" እና "የድነታችንን ልበ-ምት" ማድመጥ ያስፈልጋል፡፡ ክርስቶስን በሌላው ታክሻ ላይ ተንጠልጥሎ መከተል አይቻልምና መንፈሳዊ ግለ-ግንኙነቶቻችንን እናድስ፡፡ ግድ የለም፡-- ሐሜቱም፣ ቀልዱም፣ ምድራዊ ተድላውም፣ በምላስ ቀስት መወጋጋቱንም ለጊዜው ገታ አድርገን በውስጥ ሰውነታችን እንጠንክር፡፡ በድካም ሐሞታችን የፈሰሰም ካለን፣ ግድ የለም ፡-- ጤዛ ልሰን፣ ኮሶ ቆርጥመን፣ የሙት ሙታችንን እናንሰራራ፡፡ . . . ያኔ ሁላችንም ብርሃናችን እንደ ማለዳ ጀምበር በሰው ሁሉ ፊት ያበራል፡፡ ከተመሳስሎሽነት ካቴና ወጥተን አይቀሬ ግዴታዎቻችንን በአግባቡ እንወጣ፡፡"

"ሕይወት የሚገኝበትን ትምህርት የማይታገሡበት ዘመን ይመጣልና. . . አንተ ግን ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ፣ መከራን ተቀበል፣ የወንጌል ሰባኪነትን ሥራ አድርግ፣ አገልግሎትህን ፈፅም፡፡"

ናትናኤል በቀለ
345 views02:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 22:15:29
ኢየሱስ
347 viewsedited  19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 17:14:25 “የዘመኔ ቊጭት”

አንድ በቊጭት የተዘመረ የተማፅኖ መዝሙር አለው፤ ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ። የቅዱሳን ስደትና መከራ በበዛበት ወቅት የተዘመረ ይመስላል ። በመልዕክቱም፥ ከአሳዳጆች እጅ የእግዚአብሔርን ትድግና ይጣራል። የእስራኤልን ሕዝብ ታሪክ እያነሳ መሐሪነቱን ይመሰክራል፤ ደግሞም ይታመናል።

የዝማሬው ኅይለ-ቃል የተወሰደው ከትንቢተ ኢዩኤል መጽሐፍ ነው ። ያሕዌ የኪዳን ሕዝቡን ከጠላት እንዲታደግ ካህናቱ በመሠዊያው ውስጥ እንዲማልዱበት የተነገራቸው ሙሾ ነበር ። እንዲህ ይነበባል...[2፥17] “የእግዚአብሔርም አገልጋዮች ካህናት ከወለሉና ከመሠዊያው መካከል እያለቀሱ፦ አቤቱ ፥ ለሕዝብህ ራራ፥ አሕዛብም እንዳይነቅፉአቸው ርስትህን ለማላገጫ አሳልፈህ አትስጥ ፤ ከአሕዛብ መካከል፡- 'አምላካቸው ወዴት ነው?' ስለ ምን ይላሉ? ይበሉ።”

የምናወራው የጋሽ ተስፋዬ መዝሙር አዝማቹ እንደዚህ ይላል፡-

“ርስትህን ለማላገጫ አሳልፈህ አትስጥ
የተቀደሰ መቅደስህን በጠላት አታስረግጥ”

የእስራኤልን ሕዝብ ባሪያው ሊያደርግ ለከጀለው ጨቋኙ ፈርዖን፥ ያሕዌ ሙሴን ልኮ “ሕዝቡ የእኔ ነው” ብሎ መታደጉን በአንደኛው ቊጥር ያስታውሰናል ። ምንም እንኳ እስራኤል አመፀኛ ቢሆንም ፥ በሉዐላዊ ምርጫው የእግዚአብሔር ርስት ስለሆነ ከጥፋት ታድጎታል ። መዝሙሩ አንድም የእግዚአብሔርን ማዳን ይዘክራል ፤ በሌላ በኲል “የተቀደሰ መቅደስህን በጠላት አታስረግጥ” ብሎ በቊጭት ይማፀናል። በአባቶች ዘመን ልመናቸው ተሰምቶ እግዚአብሔር ሕዝቡን ከስደት ወደ “ነጻነት” ዘመን አሻግሯቸዋል። ሃሌሉያ!

የኔ ዘመን የድኅረ ነጻነት ዘመን ነው ፤

ዐውዱም ቊጭቱም ከአባቶች ዘመን በብዙ ይለያል። ተመሳሳዩን መዝሙር ከሌላ አቅጣጫ ተረድተን እንድንዘምር ያስገድዳል ። እንዱሮው የቅዱሳን መከራና ስደት ምንጩ በዋናነት ከውጭ አይደለምና (የለም ባይባልም)። የእውነተኛ ቅዱሳን ትልቊ ስጋትም ከኋላቸው የሚያሳድዳቸው ፈርዖን ሳይሆን ፥ እቤት ውስጥ የባዕድ አምልኮን የሚያለማምደው አሮን ነው ።

ስደቱና መከራው የውስጥ ስካር ነው። ስደቱ ውስጥ ይጠነሰሳል፤ እዚያው ይብላላል ፤ ይጠመቃል፥ ይጠጣል፥ በማወቅም ባለማወቅም ብዙዎችን ያሰክራል ። ስካር አጋላጭ ነውና ለውጭ መንገደኛ ሁሉ ይታያል። ውጫዊ ምስክርነትን ያበላሻል ፤ ታላቊን ተልዕኮ ያኮላሻል።

በጸጋ ስጦታ ስም እውነትን የሚያጠለሽ ፥ ራሱን በምእመኑ ላይ የሾመ “ሰባኪ” ነው - የስደቱ ጠማቂ ። የእግዚአብሔር ቃል ብዙም ግድ የማይሰጠው ፥ ሐሰትን መስማት የማይጨንቀው ፥ ጆሮን የሚያሳክክ አስተማሪ በዙሪያው የሚያከማቸው የሰከረ መንጋ ነው - የስካሩ ውጤት። ለሁለት ጌቶች (ለመሲሑም ለገንዘብም) መገዛት የሚያምረው ፤ ትኩስ ወይም በራድ ያልሆነ ፤ የአምልኮት መልክ ኖሮት ኅይሉን የካደ - አልጠግብ ባይ ምድራዊ ልብ ነው - የስደቱ መልክ።

ይኼ ብቻ ግን አይደለም ፤

በፍቅር ስም እውነትን የሚገፋ “ሚዛናዊ አገልጋይ” ነው የቤተ ክርስቲያን - የጎን ውጋት ። በሪቫይቫል ስም ኑፋቄን ያጠመቀ “ቄስ” ፥ ሐሰተኛውን በማውገዝ ሳይሆን አባብሎ በማቀፍ እውነትን እናላምደው የሚል አኪጦፌላዊ መካሪ ነው - የቊስሉ ምርቃዜ ። እውነትን በግል ጥቅሙ ተደራድሮ የሚሸጥ ይሁዳዊ መሪ ነው - የወንጌሉ ጠላት ። ስህተቱን ለማጽደቅ ጥቅስ የሚጠቅስ ግብዝ “አስተማሪ” ነው - የስካሩ ጥግ ማሳያ ። የወንጌሉ መሰደብ ሳይሆን የነእንትና ስም በክፉ መነሣቱ ይበልጥ የሚያንገበግበው “ዐቃቤ እምነት” ነው - የጥፋቱ አትራፊ ነጋዴ ። የዘመኔ ጉድ ብዙ ነው ብቻ!

ይኼን ሁሉ ግራ መጋባት በዙሪያችን ስንመለከት፥ እንዲያው እግዚአብሔር ሕዝቡን ለማላገጫ አሳልፎ ሰጠ እንዴ? መድረኩ በሸቃጮች ሲወረር እንዴትስ ግድ አላለውም? በውዱ ልጁ መስቀል የተበሠረው የጸጋው ወንጌል በቀማኞች ሲራከስ እንዴትስ አስቻለው? ነው ወይስ እርሱም ሰልችቶት ጭራሽ ትቶን ይሁን እንዴ?...እያልን እንቆዝማለን፤ እንቆጫለን ።

በቊዘማው መሃል በርሱ ተስፋ እንደማይቆረጥ ትዝ ሲለን፣ የካህናቱን ሙሾ እናወርዳለን ፤ የመዝሙሩን ተማፅኖ እንደግማለን፤

“እግዚአብሔር ሆይ፤
ሕዝብህን አድን፤
ርስትህን በአሕዛብ መካከል መተረቻ፣
መሣቂያና መሣለቂያም አታድርግ!”

ፍጹማን ግርማ
347 views14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 02:01:09
ራስህን "ነቢይ ነኝ" ብለህ ከመሾምህ በፊት ነቢዮ ኢሳይያስ እኛ አሁን እየታነጽንበት ላለው ወንጌል በመጋዝ ሁለት ቦታ ተሰንጥቆ መሞቱን ታውቃለህ!?

ራስህን "ነቢይ ነኝ" ብለህ ከመሾምህ በፊት ለዚህ የወንጌል እውነት ሐዋሪያው ዮሐንስ በሚፈላ ዘይት በርሜል ውስጥ ተዘፍዝፎ መሞቱን እንዲሁም ሐዋሪያው ጴጥሮስ "እንደ ጌታዬ በቁሜ አልሰቀልም" ብሎ ወደታች ተዘቅዝቆ በመሰቀል መሞቱን ታውቃለህ!?

የጥንቱ ሐዋሪያት ዘመናዊ ውድ መኪና የመንዳት ዘመናዊ ቪላ የመስራት የቱርክ ሱፍና የፈረንሳይ ሽቶ የመቀባት አባዜና ጥማት አልነበረባቸውም::

የጥንቱ ሐዋሪያት በጥቁር ገበያ በተጭበረበረ ዶላር ዮሮና ፓውንድ ከድሆች መቀነት በተዘረፈ ብር ቢሊየነር የመሆን ሕልም አልነበራቸውም::

የጥንቱ ሐዋሪያት ዘይት ውኃና ጨርቃ ጨርቅ ሽጠው ባለጠጋ የመሆን ሕልም አልነበራቸውም:: ትልልቅ አዳራሾች አልገነቡም:: የተሸቃቀጠ ወንጌል ሰብከው ዝና አላካበቱም:: ሐሰትን ከእውነት ቀላቅለው እንደ ሸቀጥ ለገበያ አላቀረቡም!!

ዛሬ ዛሬ ነቢይ ሐዋሪያ ቢሾፕ እያሉ የተለያዩ ስሞችን ለራሳቸው የሚሰጡ ሰዎች የስሙን ዋጋና ክብር አላወቁም:: ስሙን የያዙ የጥንቱ እውነተኛ አገልጋዮች ስሙ የሚጠይቀውን እውነተኛ የሕይወት መስዋዕትነት እንደከፈሉ እነዚህ መክፈል አይፈልጉም!

ዛሬ ማንም ስሙን የያዘው ሰው ስሙ ለሚጣይቀው እውነት ኑሮና ሕይወት መከራ መቀበል ዋጋ መክፈል አይፈልግም:: የገዛ ምኞታቸው አገልጋይ እንደመሆናቸው መጠን እግዚአብሔርን ማገልገል ለሚያመጣው መስዋዕትነት ዝግጁ አይደሉም:: ፈቃደኛም አይሆኑም!!

የጥንቱ ነቢያትና ሐዋርያት ዓለማና ግብ ለወንጌሉ እውነት መጋደልና ነፍሳቸውን መስጠት ነው:: የዘወትር ትጋታቸው ነፍሳትን ለጌታ መመረክ: የክርስቶስ ክብር: ደቀ መዝሙራዊ ሕይወትና ተግባራዊ ክርስትና ነው!

አሌክስ ዘፀዓት
296 views23:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 15:19:53 አትደባልቁ አትደባለቁ!!

ስለ ቤተክርስቲያን ደስ ከሚለኝ ትርጉም አንዱ “ተጠርቶ የወጣ” የሚለው ነው፡፡ ለአንዳች ኮስታራ ዓላማ የተጠራ እና ደግሞ “የወጣ”፡፡

ይህን ወደ ኋላ መለስ ብለን ያየን እንደሁ እግዚአብሔር አምላክ ከግብጽ በኩር ልጁን ጠራ፡፡ እስራኤል የተጠራው ከሆነ መልክዓ ምድር ወደ ሆነ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፤ ከአንድ ዓይነት የሕይወት ስርዓት ቅዱስ እና ውብ ወደ ሆነ ስርዓትም ጭምር ነው፡፡ ስለዚህም በዘጸአት ለወጣው ሕዝብ በዘሌዋውያን ከጠሪው ጋር የመኖሪያው ቅዱስ ስርዓት ተሰጠው፡፡

በአዲሱ ኪዳንም እግዚአብሔር አምላክ ሕዝቡን ከጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን ጠርቷል፡፡ ጥሪው መዳንን የምንካፈልበት እንደመሆኑ ብርቱ ተጋድሎ የሚጠይቅ ነው፡፡ የተጋድሎው ዓይነት ብዙ ነው፡፡ ከሁሉ በላይ ግን በዚህ ጥሪ ውስጥ ተቀላቃዮች አሉ፡፡ ይሁዳ በመልእክቱ ስለዚህ ጉዳይ ሲናገር “አንዳንድ ሰዎች ሾልከው ወደ እናንተ ገብተዋልና” ይላል፡፡ ጨምሮም ሕዝቡን ከግብጽ ሲያወጣ ያላመኑትን እንዳጠፋ ላስታውሳችሁ ይላል፡፡ ይህም በመሆኑ ይሁዳ “ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ለተሠጠ እምነት ተጋደሉ” የሚል ኮምጨጭ ያለ መመሪያ ይሰጣል፡፡

ይህኛው ተጋድሎ ከፍ ያለ ወኔ የሚጠይቅ ተጋድሎ ነው፡፡ ምክንያቱም ድብልቁን የመለየት ተጋድሎ ነውና፡፡ ቀንዳሙን ሰይጣን ወይም ሽቅርቅሯን ዓለም የመዋጋትን ያህል ቀላል አይደለም (እርግጥ ነው ከድብልቅልቁ ጀርባ በልዩ ስልት ሰይጣን መኖሩን አናብልም)፡፡ አልያም ደግሞ ለየለት ያልነውን የስሕተት ትምህርት እንደመኮነን ዓይነት አይደለም፡፡

ምናልባት አንድ ቋንቋ አብሮን የሚናገረውን ነገር ግን እልፍ እልፍ እያለ ወዥበር የሚያደርገውን፣ ለቅልቅል ሐሳብ ሰለባ የሆነውን ወንድምም ሊሆን ይችላል፡፡ ምናልባት በአንድ ወቅት የእግዚአብሔር መጠቀሚያ የነበረውን፣ በጊዜ ሂደት በመጣ መራቀቅ ግን መደባለቅ የጀመረውን ቅቡዕ ሊሆን ይችላል (እንዲህ ባለው ወቅት በተቀባው ላይ እጅ አታንሳ አይሠራም፤ በዚህ ወቅት የተቀባው ቅልቅሉን ሊያጠራ የተነሳው ነውና)፡፡ ምናልባትም በረጅም አመታት የአገልግሎት ሌጋሲ የአባትነትን ካባ የደረቡ፣ በጊዜ ሂደት በመጣ ልዘባ ግን ወርቃቸውን ያገሸቡና ለርካሽ ከበሬታ ራሰቸውን የሸጡ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

እምነታችን ከማንም ሳይሆን ከጌታ የተቀበልነው ነውና ከእነዚህ ሁሉ ይበልጣል፡፡ እናም ይህን ቅዱስ ጦርነት በርትቶ መዋጋት የተገባ ነው፡፡

ይህ ወቅት በስፋት የድብልቅልቅ መስሏል፡፡ የልዩነት መስመሮች ሁሉ ደብዝዘዋል ወይም ጠፍተዋል፡፡ የአስተምህሮ መስመሮች፣ የልምምድ መስመሮች በሙሉ በእጅጉ ደብዝዘዋል፡፡ በደጅ ያሉ ሰዎች ከሚያዩት አሳፋሪ ነገር የተነሳ በጅምላ ይወቅጡናል፡፡ እኛም ጨክነን ከእኛ ወገን አይደሉም እንዳንል፣ ደብልቅልቁ ይከለክለናል፡፡

አንዳንድ መጋቢያን ባለማወቅ አልያም በየዋህነት ሲያልፍም ደግሞ ርካሽ ጥቅም ለማትረፍ ተኩሎችን እየጎተቱ በየመድረካቸው ያቆማሉ፡፡ ጉባኤያቸው መሞቁን እንጂ የምእመናን መበላት አያሳስባቸውም፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ሦስት አመት ካገለገለበት ከኤፌሶን ሲወጣ በብዙ እንባ እና ሸክም መሪዎችን ያስጠነቀቀው፣ ሾልከው ከሚገቡ እና መንጋውን ከሚያምሱ ተኩላዎች እንዲጠነቀቁ እና መንጋቸውን እንዲጠብቁ ነው፡፡

ዛሬ በርከት ያሉ መጋቢያን ለሐሰተኛ መምህራን፣ ነባያት፣ ዘማሪያን በራቸውን ወለል አድርገው ከፍተዋል (በእኛ ዘመን ሐሳዊ ዘማሪያን እንደሚበዙ ልብ እንበል፤ ዘማሪያኑ አስር ቦታ ሲዞሩ የረገጡትን ቆሻሻ እዚህም እዚያም የሚያራግፉ ኑፋቄ አመላላሾች ናቸው፡፡ መጋቢያን እንዲህ ካሉት ድምጽ እንጂ እምነት ከሌላቸው ዘማሪያን መንጋቸውን ሊጠብቁ ይገባል፡፡)

ብዙ መጋቢያን እንኳን መንጋቸውን ከተኩላ ሊጠብቁ ይቅርና፣ በበጎ ቅናት ስለ መዳናችን ተግተው ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ስለ ተሰጠው እምነት የሚጋደሉትን ጥቂት ወገኖች፣ ማጥቃትና ማበሻቀጥ ያምራቸዋል፡፡ ይህም ነው ለቅልቅሉ ምቹ መሬት ሆኖ ኑፋቄን በምድራችን ያፋፋው፡፡

መጋቢያን ሆይ እግዚአብሔር የሰጣችሁን መንጋ ከተኩላ ትጠብቁ ዘንድ ለዚህ ተጠርታችኋልና እባካችሁ አትቀላቅሉ፤ አትቀላቀሉም፡፡

Sintayehu Bekele
314 views12:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 16:59:08 ያልተባልናቸው ነገሮች!!

1. እንደህፃናት ሁኑ (child-like) እንጂ ህፃናት ሁኑ (childish) አልተባልንም!
ማቴ 18:2-3, 1ኛ ቆሮ 11:13

2. በአምሮአችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ አዕምሮአችሁን ቆልፉ አልተባልንም!
ሮሜ 12:2

3. አገልግሎታችሁ ለሰው ህሊና እና አዕምሮ የሚመች ይሁን እንጂ ለራሳችሁ የሚመች ይሁን አልተባልንም!
ሮሜ 12:1, 1ቆሮ8: 9-13

4. ዝለፍ ገስፅ ምከር ስንባል ውስጠ መነሻ ው(motive) ሰዎችንከተያዙበት ቀንበር በእግዚአብሔር መንፈስ ሃይል ማላቀቅ ከሚሄዱበት የተሳሳተ መንገድ መመለስ እንጂ የሰዎችን ቅስም መስበር ይሁን አልተባለም!

5. የጨለማን ስራ ግለጡ እንጂ የደከመውን ሰው ገመና አጋልጡ አልተባልንም!
ኤፌ 5:11-13

6. እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ እንጂ እርስ በርሳችሁ ተሽነጋገሉ አልተባልንም!
ሮሜ 12:10

7. እንደ ርግብ የዋሆች (innocent) ሁኑ እንጂ ምንም የማታመዛዝኑ ሞኞች ሁኑ አልተባልንም!
ማቴ 10:16

8. ክፉውን በክፉ ፈንታ አትመልሱ እንጂ ክፉውን አትቃወሙ አልተባልንም!
1ጴጥ 4:9

9. ሁሉን ፈትኑ እንጂ ሁሉን በጭፍን ተቃወሙም አልተባልንም!
1ኛ5:20-21

10. የሚላችሁን ሁሉ (ጌታ/ኢየሱስ/ ቃሉ/መንፈሱ) አድርጉ እንጂ የሚሉአችሁን ሁሉ (ሰዎች/የሰው ፈቃድ/ስጋና ደም) አድርጉ አልተባልንም!
ዮሐ 2:5

ተባረኩልኝ!

ዘማሪ ዶ/ር ለዓለም ጥላሁን
646 views13:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 21:36:31
346 views18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 20:51:59 "የዝማሬ አገልግሎት ወደ ክብሩ መመለስ አለበት"

‹‹… ቤተክርስቲያን ባለፉት ሁለት ሺህ አመታት መስቀሉን ማእከል ያደረገውን ወንጌል ስታበሥር ኖራለች፤ እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን (1ቆሮ 1፡23( እያለች፡፡ የመንግስቱ ወንጌል ቤዝዎታዊ እውነቱ የሚታየው በክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ በኩል ነው ነውና፡፡ ያልተዋጁ ንጉሡንም ኾነ መንግስቱን አያዩትም፡፡ ቤተክርስቲያን ከቅዱሳት መጻሕፍት ውጭ በኾነ ትምህርትና ኑሮ የመስቀሉን መልዕክት አዛብታ የተገኘችበት ወቅትም ነበረ፤ ዛሬም አለ፡፡ …… መስቀሉን ማእከል ካደረገው ወንጌል ይልቅ ቅምጥልነተን የሚያስፋፋውን ‹‹ዘመነኛውን ወንጌል›› ማስበለጣችንን›› ጋሽ ሰለሞን አበበ ገ/መድኅን ‹‹የደነበረው በቅሎ በተሰኘው መፅሃፋቸው ላይ አንስተዋል፡፡

እንደእውነቱ ከሆነ ‹‹ያለመስቀሉ ክርስትናን ማሰብ መሞከር አይታሰብም››፡፡ ዛሬ ዛሬ ላይ መስቀሉን ገሸሽ ያደረጉ ስብከቶች ወይም ትምህርቶች ላይ ብዙ ትኩረት ቢደረግም ዝማሬዎቻችንም ከዚህ በሽታ መላቀቅ አልቻሉም፡፡ የዛሬዋ ቤተክርስቲያን ትልቅዋ ችግርም ከክርስቶስ መስቀል ገለል ማለትዋ እና ለውጫዊው ገፅታዋ ትኩረት መስጠትዋ ነው፡፡

መስቀሉን ማእከል ያደረጉ ዝማሬዎች አይደመጡም መድረኮቻችን ላይም እምብዛም አይዘመሩም ከዛ ይልቅ ‹‹አቧራ የሚያስነሱ›› ዝማሬዎች መድረኩን ያጨናንቁታል፡፡ መንፈስ አልባ ዝማሬዎች እየገነኑ የዝማሬ አምልኮኣችን አቧራ ጨሰ ሆኗል፡፡ እግዚአብሔር የሌለበትን አምልኮ ለምደነዋል ክፋቱ ደሞ እግዚአብሔር እንዳለ ማሰባችን ነው፡፡ በአቧራ ውስጥ እግዚአብሔር የለም፡፡ ስሜትን በማሞቅ ውስጥ መንፈሱ የለም፡፡
በዕንባ የሚደመጡ ዝማሬዎች ነፍስን የሚያክሙ፤ ሸካራና ድንጋያማ ልብን የሚያለሰልሱ ዝማሬዎችን ሰምቶ ላገ ሰው ዛሬ ዛሬ ላይ ‹‹ላብን እንድናወጣ›› ታስበው ብቻ የሚዘመሩ ዝማሬዎችን መስማት ህመምን ይፈጥርበታል፡፡

‹‹አስይዘኝ መስቀሉን - ሁሌም አሳዝለኝ
ከመፋነን ግሳት - ሞቴ እንዲቀልልኝ፡፡››

የሚል ዝማሬ ይጨንቀናል፤ አናደምጠውም ከእንዲህ አይነት ዝማሬ ይልቅ ትከሻን ነቅነቅ የሚያደርግ ስሜትን የሚያነቃቃ ዝማሬ እንፈልጋለን፡፡ ክቡሩ በሌለበት አምልኮ ለምደናል ዘማሪው ለማስጨፈር አስቦ ስለሆነ መድረክ ላይ የሚወጣው የእግዚአብሔርን መገኘት በአብዞኛው መድረክ ላይ አናየውም፡፡ የመጨፈር ጥም እንጂ እግዚአብሔርን በዝማሬ የማምለክ ናፍቆት ተወስዶብናል፡፡ አንድ የሚያሳዝን እውነት አለ አብዛኛውን መድረክ ያጨናነቁ ዘማሪዎች ገበያ ተኮር የሆኑቱ ናቸው በጠጠሩበት ሁሉ የሚገኑ በተጠሩበት ሁሉ የማይታጡ ድምፅ እንጂ መቀላለፅ እንጂ ማድመቅ እንጂ ነፍስን የሚደርስ ዝማሬ የሌላቸው አዎ እነርሱ ናቸው ያጨናነቁን፡፡ አንዳንድ ቦታ የምንሰጣቸው በዝማሬ አገልግሎታቸው በብዙ የባረኩን ዘማሪዎችም የዚህ ሰለባ ሆነው ስናገኛቸው እናዝናለን፡፡

አዎን ዛሬም በዚህ ዘመን ዝማሬያቸው የክርስቶስን መስቀል፤ የእግዚአብሔርን ቃል ማዕከል ያደረጉ የሉም ማለት አይደለም ስለነርሱ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፡፡ ነገር ግን ዛሬ ዛሬ ላይ በቤተክርስቲያን የዝማሬ አገልግሎት ክቡርነቱን እያጣ መጥቶ የፕሮግራም ማዳመቂያ መሆኑን ማነገር ደግሞ ያስፈልጋል፡፡ … ሕይወት የሌለው ነፍስን የማይደርስ ልብን የማይፈውስ ለጭፈራ ብቻ የሚውሉ ዝማሬዎች በቤተክርስቲያን መድረክ ላይ አይለዋል፡፡ ‹‹መደነስ ካልቻልክ ከፊቴ ዞርበልልኝ …. ፕሮፌቲክ ዳንስ ደንስልኝ እየተባለ የዝማሬ አገልግሎት ከማስጨፈር ከመደነስ ጋር አያይዘውታል፡፡ የዘማሪ ትልቁ ኳሊቲ ማስጨፈር እስኪመስል ድረስ ነገሮች እየተዘበራረቁ መጥተዋል አኹን ግን በቃ ልንል ይገባል፡፡ በዝማሬ የብዙዎቻችን ሕይወት ተለውጧል ብዙዎቻችን ተገርተናል በንስሃ ፍሬ ከአምላካችን ጋር ታርቀናል ተፅናንተናል ፀንተንበታል አምላካችንን አወድሰንበታል ከፍ አድርገንበታል፡፡ አዎን ሳንጨፍር ላብ ሳይወጣን እግዚአብሔርን ከፍ አድርገንበታል፡፡ እናም አንዳንድ ሳይኾን ብዙ ዘማሪዎቻችን እረፉ ወይም ጎራችሁን ለዩ ዝማሬን አታርክሱት ዝማሬን አታኮስሱት፡፡ የዝማሬን አገልግሎት የፕሮግራም ማዳመቂያ ለማድረግ የምትጥሩ ሁላችሁም ከዚህ መንገዳችሁ ተቆጠቡ ዘማሪዎቻችን ሆይ በሰው ልብ ላይ የሚውል ዝማሬ ዘምሩ ገባያ ተኮር ብቻ ሆናችሁ ኢየሱስ የሚል ቃል ብቻ እያስገባችሁ ቀሽም ዝማሬን አትዘምሩ የዝማሬ ፀጋ ማለት የድምፅ መኖር ማለት አይደለም ድምፅ ስላላችሁ ብቻ ለመዘመር አትውጡ የዝማሬ አገልግሎትን አክብሩ፡፡ ለማስጨፈር ከሆነ ዓላማችሁ ማይኩን ልቀቁና ውረዱ ወደ እልፍኛችሁ ግቡ እግዚአብሔር የራሳችሁን ዝማሬ/መልዕክት እንዲሰጣችሁ ተማፀኑ በብዙ እንባ በብዙ ፀሎት የተወለዱ ዝማሬዎች አታበላሹ፡፡

እኛም በቤተክርስቲያን ያለን ወጣቶች አባቶች እናቶች ሴቶች ወንዶች ሆይ በቤተክርስቲያን ከሚታየው የክርስቶስን መስቀል ካስወገደው ከሰው ልማድ አንፃር ተከፍተን ከቤተክርስቲያን ከመሸሸ ይልቅ የሁሉ መመዘኛ የሆነውን ቃሉን አንስተን በርሱ ላይ በመቆምና በመታነፅ በየቤተክርስቲያናችን የሚታዩ ኢ መፅሃፍቅዱሳዊ ትምህርቶችን ሆነ ዝማሬዎችን ልንሞግት ይገባል፡፡
በየአጥቢያችን የሚገኙ መሪዎችንን እረኞችን እየሞገትን ምመኑን ፉርሽካና ገለባ ከመመገብ መግታት አለብን፡፡ ወደ ቤቱ የምንመጣው ክርስቶስን ለማየት እንጂ የሰዎችን ችሎታ አይተን ለመሄድ አይደለም፡፡ ከእግዚአብሔር ቃል በራቁ ከመስቀል በጎደሉ ዝማሬዎችና ትምህርቶች ምክንያት የቤተክርስቲያን መልክ መደብዘዝ አቅምዋ መልፈስፈስ የለበትም፡፡ ተሃድሶ ያስፈልገናል ፤ ተሃድሶውን ከአጥቢያችን እንጀምር፡፡

(((‹‹መስቀሉን ወደ ዳር/ጠርዝ ገፍተን ማዕከሉን ለማን ልንሰጠው ነው? ደግሞም ከዘመናችን ስብከቶች ፣ ትምህርቶችና ዝማሬዎች ውስጥ የመስቀሉን ምልክት ምን ሰወረው? የሚለው ጥያቄ አንገብጋቢ ነው፤ ልንነጋገርበትም ልንቆጭበትም የተገባ ይመስለኛል፡፡ የደነበረው በቅሎ 95››))) እንዳሉት ነውና ልንቆጭ ልንነጋገር የሚገባበት ጊዜ ነው፡፡

አዎን ‹‹የደነበሩ በቅሎዎች›› በየቦታው አሉና ‹‹የአስተምህሮ ልጓም ያስፈልጋቸዋል›› …የዝማሬ አገልግሎት ወደ ክብሩ መመለስ አለበት እስከመቼ የድሮ ዝማሬዎች እያልን እንቆጫለን? ለምን በእኛ ዘመንስ መስቀሉን ክርስቶስን ማዕከል ያደረጉ ዝማሬዎች አይበዙልንም?! ከእኛው እንጀምር መድረኮቻችንን በማጥራት እንጀምር፡፡

‹‹ትውልድ ሆይ ወደ እግዚአብሔር ቃልና ወደ ክርስቶስ መስቀል ተመልከቱ›› ይህ እውነት ለዝማሬ አገልግሎትም ይሰራል፡፡
887 views17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-27 21:28:24 አምላክ ሆይ የሆነብንና እየሆነብን ያለውን ነገር ተመልከት፡፡ የምታድነን አንተ ነህና አስበን፡፡ ‹‹ምህረትህ ይምጣ ከሠማይ፡፡›› በሀገራችን እየሆነ ያለውን እይ ዝም አትበለን፡፡ ምድራችን ‹‹በቁጣህ በትር ተመታ እያነከሰች›› በጉስቅልና ብዛት እየማቀቀች ከሰላም ርቃ የምትኖርበት ጊዜ ያብቃ፡፡ ዕረፍት ርቆናል፤ ሠላም ጠምቶናል፤ በጭንቅ ተይዘናል፤ የእንባ ግድባችን ፈርሶ አይናችን ሌት ተቀን ያነባል፡፡ እባክህን ማረን፡፡

‹‹ሞትን ቁም ነገር ማን ይለዋል?
ሰው እንደ እንስሳ መንገድ ወድቋል››

የሠው ነፍስ ርካሽ ሆኗል፤ የምንገዳደልበት ምክንያትና ሰበብ በዝቷል፡፡ የሚያፅናናን አጥተናልና ወዳንተ እንጮኻለን፡፡ በእርግጥ ስለ ኃጢአታችን ብዛት በትርህ ተነስቶብናልና ማረን እንልሃለን፡፡ የሀገራችን ውበት ከስሟል የሚረዳትም የለም ሁላችንም በእጆቻችን ሰይፍ ጨብጠናል አመቺ ጊዜ ስናገኝም ልንተራረድ ተሰልፈናል፡፡ ሆዳችን ቂም አርግዟል ሞትንም እየወለደ ነው፡፡ ሠውነት ረክሷል! ህሊና ሞራል አፈር በልቷል፡፡ ሁሉም በገዛ መንገዱ ወደ ጥፋት ይነጉዳል የሚመልሰውም የለም፡፡ አንተ ግን አስበን!!! ዛሬም እንደትናንቱ እናነባለን፤ ዛሬም እንደትናንቱ እንሞታለን ታዲያ ማን ሊታደገን ይችላል?

‹‹እየመሸ ነጋ እየነጋም መሸ
ዛሬም ጉስቁልና ከምድሬ አልሸሸ››

አገራችን ረክሳለች ‹‹ያከበሩአት የነበሩ ሁሉ ኀፍረተ ሥጋዋን አይተዋልና አቃለሉአት …. በድንቅ ተዋርዳለች የሚያፅናናትም የለም›› አቤቱ ተመልከተን! ፅኑ ቁጣህን መልስልን፡፡ ደክሞናል፤ አቅቶናል፤ ታክቶናል ተስፋችን ግን አንተ ነህ፡፡ እባክህን ራራልን፡፡

ኦ ኢትዮጵያ ሆይ ‹‹ስብራትሽ እንደ ባሕር ታላቅ ነውና የሚፈውስሽ ማን ነው? …. ነቢያቶችሽ ከንቱና ሐሰተኛ ራዕይ አይተውልሻል ምርኮሽንም ይመልሱ ዘንድ በደልሽን አልገለጡም ከንቱና የማይረባ ነገርንም አይተውልሻል›› አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ ካንተ ውጪ ማን ይደርስልናል? እባክህን እየን ፤ ተመልከተንና ራራልን የአንተን ማዳን ተስፋ አድርገናልና ታደገን!!!

በቃ በለን! ሠላም ስጠን! የመሪዎቻችንን አዕምሮ ፈውስ የህዝባችንን ማስተዋል መልስ አንዳችን በአንዳችን ላይ እየተነሳን እስከመቼ እንተላለቃለን? መቼ ይኾን ጉስቁልናችን የሚያበቃው?

‹‹ስትነዋወጥ ምድር ባንድ ላይ
ጎበዝ ደካማው ማንም ሳይለይ
ሁሉ ሲመታ ደዌ ሲያደቀው
ችግር ስቃዩ ሲያጠወልገው
ረዳት ፈልጎ አይኑን ቢያነሳ
ረጂው ጋር ብሶ ስቃይ አበሳ
ደጋፊም አጣ ጨላለመበት
የከፋ ጊዜ ሰው የሌለበት
ትርምስምስ ሲል ሲያይል ፈተናው
ሠው ግራ ገብቶ ጠፍቶት ሚያደርገው
ሽብር ሲነሳ በየመንደሩ
ሞት ቀላል ሲኾን ረክሶ በሀገሩ››

ተስፋችን ነህና አቤቱ ታደገን፤ የቁጣህን በትር መልስልን፡፡ ፃዲቅ ፈራጅ አምላክ ኾይ በመንበርህ አለህና ዘንበል በልልን፡፡
714 views18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-23 21:42:13 "ለኅጥአን የሚደማው ልቡ ስራውን አቆመ። የዓለም ብርሃን በሞት ጥላ ውስጥ ገባ። ወደ እግዚአብሔር መግቢያ በር የሆነው በታተመ መቃብር ገባ። የበጎች እረኛ በበጎቹ ተገደለ። ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ተገደለ። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞተ። ሞቶ ግን አልቀረም የሞትን መውጊያ ሰብሮ የሲዖልን ማስፈራራት ዝም አሰኝቶ ድል ነሳ። ሕያው ሆኖ ሕያው አደረገን። ኦ ሃሌሉያ!!!!"

ወዶኛል፤ ራሱንም ለእኔ አሳልፎ ሰጥቷል። (ገላ. 2፥20)

ትንሳኤ የነፍስ ጉዳይ ነው መልካም በዐል።
176 views18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ