Get Mystery Box with random crypto!

ሰንፔር ሚዲያ Sapphire Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ senpareadisketemafgc — ሰንፔር ሚዲያ Sapphire Media
የቴሌግራም ቻናል አርማ senpareadisketemafgc — ሰንፔር ሚዲያ Sapphire Media
የሰርጥ አድራሻ: @senpareadisketemafgc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 464
የሰርጥ መግለጫ

መንፈሳዊ መጣጥፎችን ግጥሞችን ወጎችን አጫጭር ልቦለዶች አስደናቂ ታሪኮችን ትምህርታዊ ፅሁፎችን ለማግኘት ይቀላቀሉን።
"ትውልድ ሆይ ወደ እግዚአብሔር ቃልና ወደ ተሰቀለው ክርስቶስ ተመልከቱ!!!"
https://youtu.be/KRKo3x7iYNw
http://Instagram.com/sapphiremedia4god
tiktok.com/@sapphiremedia1

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-07 13:42:03 https://t.me/+SNquGIqQZ7TrnyUN
15 views10:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 22:33:49
ቅዳሜ እንገናኝ።
አይቀርም።
119 views19:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 22:32:53 መነጠል

በድጥ ጎዳና ላይ ፤ እግሬ ይራመዳል
ታጥቦ ጭቃነትን ፤ ልቤ ይላመዳል
ያገኘውን ለመዳሰስ ፤ እጄ ይፈጥናል
የሞት ፍሬን ለመቅመስ ፤ ምላሴ ይጎመጃል

ሀሳቤን በሙሉ ፤ ከምድሩ ላይ ጥዬ
ከሞት ተጣብቄአለሁ ፤ ከግንዱ ተነጥዬ

በተነሳው ወጀብ ፤ ላለመወድቅ ብጥርም
እግሬ በድጥ ላይ ነውና ፤ መሰበሬ አይቀርም።
ዕድፍ የለብኝም ፤ ብትልም ምላሴ
በታጥቦ ጭቃነት ፤ ቆሽሿል ልብሴ
ለአምላክ መሸነፌን ላሳይ ፤ እጆቼን ባነሳም
በግብዝነት እሾህ ፤ መዳፎቼ ተወግተው - ተጨማልቄአለሁ በደም

‹‹ካንደበቴ እውነት›› ፤ ከአፌ ፅድቅ ርቆ
ከሞትኹ ሰነበትኹኝ ፤ አጥንቴ ደርቆ
በዚህ ኹሉ ውድቀት ውስጥ ፤ ነፍሴ ብታልፍም
በንስሃ ለመታጠብ ፤ እንባን አላፈስም

ምክንያቱም
የእውነት ቃል ቀሎብኝ ፤ በስጋዊነት ደምቄኣለሁ
በርኩሰት ካባ ፤ በዓለም ነግሻለሁ

አንዳንድ ጊዜ
በሞኞች መንደር
በቂሎች ሰፈር
ውርደትን በክብር መለወጥ ፤ ከፅድቅ ይቆጠራል
የሞት ፍሬን ማፍራት ፤ በብዙ ያስከብራል።

ቢሆንም ቢሆንም
ይሄንን እውነት ልክደው አልሻም
ሀሳቤን በሙሉ ፤ ከምድሩ ላይ ጥዬ
ከሞት ተጣብቄአለሁ ፤ ከግንዱ ተነጥዬ፡፡
/////

ቢቶ
173 viewsedited  19:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 22:44:16 የከበሬታ ነገር!

በአገልግሎት ምክንያት ያገኘኋት አንዲት የባለቤተስኪያን ሚስት ጋር እናወራለን፡፡ ግንኙነታችን ገራም እና ደኅነኛ ስለነበር፣ በጥሩ የወዳጅት መንፈስ እናወራለን፡፡ በእኔ በኩል የመቀራረባችን ምክንያት እንደው አንዳንድ ወጣ ወጣ ያሉ ነገሮችን በመቀራረብ መግራት ይቻል እንደሁ ከሚል የዋሕነት ነበር፡፡

ልጅቱ አብዝታ አገልጋዮች ከበሬታ ይገባቸዋል የሚል ሙግት ታነሳለች፡፡ ከበሬታውም በልዩ ልዩ መንገድ መገለጥ አለበት ባይ ነች፡፡ ለምሳሌ የተመረጠው እና የተሻለው ነገር ሁሉ ለአገልጋዮች ይገባል፤ የተሻለ መኪና መንዳት፣ በተሻለ ቤት መኖር፣ የተሻለ መብላት፣ መልበስ...
ይሄ ሁሉ መሆኑ የከፋ ባልሆነ፤ ነገር ግን ይህ ሁሉ የሚሆነው በሕዝብ ጫንቃ መሆኑ ነው አሳዛኙ ትራጀዲ፡፡ ይህን መሳዮቹ አገልጋዮች ግባቸው ይኸው ስለሆነ ይህንን ለማሳካት ሁሉን ነገር ከዚህ አንጻር ይቃኙታል፡፡ ስብከቱ፣ መዝሙሩ፣ መዋቅሩ ሁሉ ከዚህ አንጻር ይገነባል፡፡

የምእመናን ስኬትም ይሁን ውድቀት ለ“አገልጋዮቹ” ካለ ከበሬታ ጋር እንደሚያያዝ አድምተው ይለፍፋሉ፡፡ ምእመናን ወጥተው የሚገቡት በእነሱ ጥላ ከለላነት እንደሆነ አድርገው ያሳምናሉ፤ ቡራኬያቸው የምእመናን ወጥቶ መግቢያ ቀለብ እንደሆነ በየምእመኖቻቸው ልብ ውስጥ አጽንተዋል፡፡

ራሳቸውን በየተከታዮቻቸው ልብ ውስጥ አግዝፈው፣ ዙፋናቸውን ዘርግተዋል፡፡ “ከመረቅሁሁ” የሚል ማበራቻ ብቻ ሳይሆን፣ “ከረገምሁህ” የሚል ማስፈራሪያም አላቸው፡፡ ምእመናን መጋቢው፣ ነቢዩ ወይም ሐዋርያው እንዳይረግመው /ቃል እንዳያወጣበት ፀጥ እና ዝግ ብሎ ይኖራል (በ“አገልጋዩ” ፊት) እግዚአብሔርን በቅጡ አያውቀውም፤ ካወቀውም አገልጋይ ተብዬው በሳለለት ልክ እንጂ የመጽሐፉን እግዚአብሔር አያውቀውም፡፡ በክርስቶስ ነጻ እንደወጣ ሰው ሳይኾን፣ ልክ በአንድ ዓይነት ባዕድ አምልኮ እንደተተበተበ ሰው ዓይነት ድንብርብሩ እየወጣ ይኖራል፡፡ የእርሱ እግዚአብሔር ሁልጊዜ በእርሱ “አገልጋይ” በኩል ብቻ የሚፈስ ነው፡፡ አገልጋይ ተብዬዎቹም ምእመናቸው ከዚህ እንቅልፉ እንዲነቃ አይፈልጉም፡፡ ቅምጥል ኑሯቸውን ባንቀላፉ ምእመናን ላይ መስርተዋል፡፡

የቸርቻቸውን ዙሪያ በገዛ ፎቷቸው ያጥራሉ፤ ቢሮው እና መድረኮቻቸው ሳይቀር በተንቆጠቆጡ ምስሎቻቸው ይሞላሉ፡፡ አንዳንዶቹ ሚስት እና ልጆቻቸውን ሳይቀር ቸርች ባሉት ይዞታቸው ላይ ይሰቅላሉ፡፡ አንዳንዶቹም ምስሎቻቸውን አትመው በየዋሌቱ እንዲያዝ ያድላሉ፡፡ በዚህም ያለ ልክ ተንሰራፍተው፣ የጌታን ጌትነት ተጋፍተው በየሰዎቻቸው ላይ ይነግሣሉ፡፡

በዚህም ያን ያነገቡትን የቅንጦት ኑሮ ይኖራሉ፡፡ “ምርጥ ምርጡን ለሕፃናት!” እንደተባለው ዓይነት በምርጥ ምርጡ ይምነሸነሻሉ፡፡ ልዕልናቸውን ያለ ልክ ከፍ አድርገው “መጡ መጡ፤ ገቡ ገቡ” ይባልላቸዋል፡፡ በማንኛውም መንገድ ልዕለ ሰብ እንደሆኑ ያውጃሉ፡፡ ተራ በሚሉት ምእመን ላይ ጢባ ጢቤ ይጫወታሉ፡፡

መቸም መከባበር ክርስቲያናዊ እሴታችን ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነት ትርፉታችንም ነው፡፡ እርስ በርስ ለመከባበርም ደግሞ የቃለ እግዚአብሔር መመሪያ አለን፡፡ ቢሆንም አገልጋዮች በተለየ መንገድ ይደግደግላቸው የሚል መመሪያ ግን ጨርሶውኑ የለንም፡፡

መሪ መምህራችን ጌታ ኢየሱስ አብዝቶ ካስተማራቸው ነገሮች መካከል ስለ ዝቅታ እና ትሕትና ያስተማረውን የሚያህል ያለ አይመስለኝም፡፡ ለተወሰኑ ጊዜያት በእኔ እበልጥ እና በፉክክር መንፈስ ይንገላቱ የነበሩትን ደቀመዛሙርቱን ደጋግሞ ገስጿል፡፡ ማገልግል በራሱ የታችኛውን ስፍራ መምረጥ ነው፡፡ ጌታችን ስለ ራሱ እንኳን ሲናገር “የሰው ልጅ ሊያገለግል፣ ነፍሱንም ስለ ብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም” ብሏል፡፡ በዚህም አገልጋይነት ባርነት መሆኑን አጽንቷል፡፡

ከዚህም ሲያልፍ መምህር እና ጌታ የሆነው እርሱ በእውነተኛ መዋረድ እና ዝቅታ ወገቡን አሸርጦ የደቀ መዛሙርቱን እግር አጥቧል፡፡ ይህም የተወሰኑ ኦኬዥኖች እየጠበቅን ለማስመሰል ድራማ እንድንሠራ ሳይሆን፤ አገልጋይነት የሁልጊዜ የሕይወት ሥርዓታችን እንዲሆን የተሰጠ ትምህርት ነው፡፡

ይህንኑ ፈለግ የተከተሉትም ደቀመዛሙርት ይህንኑ ቅኝት ጠብቀው ነበር ሲያገለግሉ የነበሩት፡፡ አገልግሎታቸውን የገዛ ፍላጎታቸው መሙያ ሲያደርጉ ለአፍታም እንኳ አናይም፡፡ በማንኛውም መንገድ ራሳቸውንም አላሻሻጡም፡፡ በገዛ ቃላቸውም “ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ እንጂ ራሳችንን አንሰብክም!” ብለው መስክረዋል፡፡ በስማቸው የተቋቋመ ቡድንንም አምርረው ኮንነዋል፡፡ አለፍ ብሎም የተለየ ከበሬታ በተዘጋጀላቸው ወቅትም በመንቀጥቀጥ ልብሳቸውን ቀደዋል፡፡
ግባቸው አንድ እና አንድ ክርስቶስ ኢየሱስ በአገልግሎታቸው እንዲገለጥ እና የሁሉን ሕይወት እንዲወርስ ብቻ ነበር፡፡ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ይህ አገልግሎት የሚጠይቀውን ዋጋ በደስታ ከፈሉ እንጂ፣ ማንንም ዋጋ አላስከፈሉም፤ ሰማይ ሙሉ ዋጋ ይዞ እንደሚጠብቃቸው ግን እርግጠኞች ነበሩ፡፡ በአገልግሎታቸውም በአንዳች ስንኳ ማሰናከያ አልሰጡም ነበር፡፡

ከበሬታን ግብ ያደረገ አገልግሎት ጨርሶውኑ ከጌታ አይደለም፡፡ የእኛ ክብር የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ የከበረ ‘ለታ ብቻ ነው፡፡ በተለያየ መንገድ ራስን ማሻሻጥ በሚመስል መልኩ እርሱን ጋርዳችሁ የደመቃችሁ ሆይ ወዮላችሁ፡፡ ምስሉን እያደበዘዛችሁ፣ ምስላችሁን በየሰዉ ልብ ለማተም የምትታትሩ ሆይ ወዮላችሁ፡፡ እራሳችሁን እያዋደዳችሁ ዙፋናችሁን ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ልትገነቡ ያማራችሁ ሆይ ወዮላችሁ፡፡ የጌታ ቤት ባላችሁት ቸርቻችሁ ላይ ደማቅ ምስላችሁን ሰቅላችሁ ራሳችሁን ያነገሣችሁ ሆይ ወዮላችሁ፡፡
ቀን ሳይጨለም ለልባችሁ ሰው መሆናችሁን ንገሩት፤ ከፍ ብላችሁ በመፋነን ፋንታ የዝቅታን አገልግሎት ምረጡ፡፡ በጌታ ዘንድ ራሱን ከፍ ከፍ ሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፤ ራሱንም የሚያዋርድ ከፍ ይላል፡፡
ጆሮ ያለው ይስማ!!

ማገናዘቢያ፡ ማቴ 20÷20-28፣ ሉቃ 14÷11፣ ዮሐ 13÷12-15፣ 2 ቆሮ 4÷5፣ 1 ጴጥ 5÷6

መጋቢ ስንታየሁ በቀለ
239 views19:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 01:30:32 ወጣቶች !!!

ሳያገቧችሁ በትዳር ብቻ ሊፈቀድ ወደሚገባው ቅርበት፣ ጥልቀትና የተጠቃሚነት ደረጃ ውስጥ ለመግባት ጥያቄ ከሚያቀርቡ ሰዎች ራሳችሁን ጠብቁ፡፡ ምንም አይነት የማሳመኛ ምክንያቶች ቢደረደሩም መልሳችሁ አሁም ሆነ ለወደፊቱም "NO" መሆኑን በግልጽ ማሳየትን አትዘንጉ፡፡

የፍቅር ግንኙነት ሂደትና እውነታ ግራ ከገባቸው ከተወሰኑት በስተቀር ሌሎቹ እንደዚህ አይነት ሰዎች እናንተን ሳይሆን የእናንተ የሆነውን ነገር ፈላጊዎች ናቸው፡፡ የሚፈልጉትን ካገኙ በኋላ ብትፈልጓቸውም አታገኟቸውም፡፡

ዶ/ር ኢዮብ ማሞ
166 views22:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 17:51:14 #ዘረኝነት_ሁላችንንም_የሚውጥ_ጨካኝ_ዘንዶ_ነው!

"በዘረኛ ማህበረሰብ ውስጥ ዘረኛ ያለ መሆን ብቻውን በቂ አይደለም:: ፀረ-ዘረኛ መሆንም አለብህ!" (Angela Davis)

ዘረኝነት እያንዳንዳችንንም የሚበላ አውሬ መሆኑን በዚህ አጭር ዘመን ተመልክተናል:: ዘረኝነት አንተ ዘረኛ ስላልሆንክ ርቆ አይቀመጥም:: ብሔርህን: ቀዬህን: ቋንቋህን ለይቶ እስከ ደጅህ ይመጣል:: ጳጳስ ስለሆንክ: ቄስ ስለሆንክ: ቢሾፕ ስለሆንክ: መጋቢ ስለሆንክ: ሼክ ስለሆንክ አይተውህም:: ቀን ጠብቆ: ቀየ ቆጥሮ አውሬው ደጅህ ይመጣል:: ከወለጋ: ከጋምቤላ: ከአፋር: ከቤንሻንጉል ስለራቅህ የምትተርፍበት ሰላማዊ ሥፍራ አይኖርህም:: ዘር ቆጥሮ የመግደል አቅም ያለው ቀን የሚጠብቅ ጨካኝ ዘረኛ ጎረቤትህ: መስሪያ ቤትህ: ስራ ቦታ: ቤተ ክርስቲያንህ: መስጊድህ ውስጥ አለልህ!!

የነፍሰ በላው ናዚ ጭፍጭፈ ካለፈ በኅላ በ1946 Martin Niemoller የተሰኘ የሉተራን ቄስ የተናዘዘው ታዋቂ አባባል አለ:: ይህ አባባል "መጀመሪያ ወደ ሶሻሊስቶች መጡ: ሶሻሊስት ስላልሆንኩኝ ምንም አልተናገርኩም ነበር:: ቀጥሎ ወደ ንግድ ማኅበር መጡ: የነጋዴዎች ማኅበር ውስጥ ስላልሆንኩኝ ምንም አልተናገርም ነበር:: ቀጥሎ ወደ አይሁዶች መጡ: አይሁድ ስላልሆንኩኝ ምንም አልተናገርም ነበር:: በመጨረሻም ወደ እኔ መጡ:: የሚጮህልኝ አንድም ሰው አልተረፈም ነበር" ይላል!!

Martin Niemoller ይህንን ያለው በናዚ ጭፍጭፋ ወቅት ምሁራን እና የቤተ ክርስቲያን ሰዎች የናዚን ጭፍጨፋ ላለመውገዝ ዝምታ በመምረጣቸው ምክንያት ነበር::

ብሔርተኛውን ሕገ መንግስት መሰረቱን ያደረገውና ላለፉት ሦስት ደርዘን አመታት ሲቀለብ ቆይቶ ኅይሉን በማፈርጠም እየበላን ያለው ዘንዶ በጊዜ ተባብረን ጮኸን ካላቆምነው እያንዳንዳችን ቤት መምጣቱ አይቀሬ ነው:: ያኔ የትምህርት ደረጃህ: የስራ ሁኔታህ: እምነትህ: የፖለቲካ አቋምህ: ስምና ዝናህ አያድንህም:: የዚያኔ በጠንካራ ግንብ የታጠረ ግቢ ውስጥ መኖርህ:: ዘመናዊ ፍጣን መኪና መንዳትህ አያድንህም!!

የሃይማኖት መሪ ነኝ:: ምሁር ነኝ:: ከተማና ገጠር ነኝ:: ሳትል በጊዜ መጮህ ያለብህ ለዚህ ነው:: ያለበለዚያ ልጆችህን: ቤተሰብህን: ዘመድ አዝማድህን: ወዳጆችህን አንተን "አልነካም" ባይን የሚበላ የዘር ዘንዶ እየመጣብህ ነው:: ቤተ መንግስት ብትሆን: ቤተ መቅደስ ብትሆን: መስጊድ ብትሆን: የባለስልጣን ቤተሰብ ብትሆን የትም ብትሆን አይምርህም!!

Alex Zetesat
303 views14:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 17:50:51
89 views14:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 14:04:49 "የመስቀሉ ስራ ዘመን ያስቆጠረ አይደለም። ለእኛ ሁለት ሺ ዘመናትን ሊያስቆጥር ቢችልም የወልድ የመስቀሉ ተግባር ለጊዜ የተከናወነ ክንውን ባለመሆኑ ምክንያት እስካሁን ድረስ ለመለኮት አለም የሰዎችን የዘላለም ሕይወት የሚቀይር እንደሆነ እንደታመነ ይኖራል።"

ኤፍሬም አባዲ
412 views11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 22:45:06 ለአገልጋዩ ወይስ ለእግዚአብሔር?

አንዳንድ ጊዜ፣ አገልጋዮች የእግዚአብሔርን ቤት ሥርዓት ሲያበላሹ፣ ውግንናችን ለማን እንደሆነ ይገለጣል።

በዘሌዋውያን 10 የተጻፈ አንድ አስገራሚ ታሪክ አለ፡፡ ለመቅደስ አገልግሎት የተለዩት የአሮን ልጆች ናዳብና አብዩድ፣ በእግዚአብሔር መሠዊያ ላይ እርሱ ያላዘዘውን እንግዳ እሳት አነደዱ፡፡ እግዚአብሔር ወዲያው ቀሰፋቸው፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ አባታቸው አሮንና ሌሎች ወንድሞቻቸው በማደሪያው ድንኳን ውስጥ አገልግሎት ላይ ነበሩ፡፡ ይህን በገዛ ቤተሰባቸው ላይ የወረደ አስደንጋጭ መቅሰፍት ሲመለከቱ፣ እዬዬያቸው ለማቅለጥ ተነሱ:: ይህን ጊዜ ሙሴ በመሐል ገባ፡፡ “ማልቀሱን እንዳታስቡት!” አላቸው፡፡ “እንዳትሞቱ፣ በሕዝቡም ላይ ቊጣ እንዳይመጣ…እንዳታለቅሱ!” (ዘሌ. 10፡6)፡፡

አሮንና በሕይወት የተረፉት ልጆቹ የገቡበት አጣብቂኝ አንድ ነው፡- ባንድ በኩል፣ በመቅደስ ለሚያገለግሉት ለእግዚአብሔር ቁጣና ፍትሕ መወገን ይጠበቅባቸዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የተቀሰፉት የሥጋ ዘመዶቻቸው ስለሆኑ ጥልቅ ሐዘንና የልብ ስብራት ገጥሟቸዋል፡፡ ስለ ወንድሞቻቸው አምርረው ማልቀስ፣ ልብሳቸውን መቅደድና ጸጉራቸውን መንጨት ፈልገዋል፡፡ ነገር ግን ይህን እንዳያደርጉ ተከለከሉ፡፡ ከድንኳኑ ወጥተው እንዲቀብሯቸው እንኳን አልተፈቀደላቸውም፡፡: ሙሉ በሙሉ ለእግዚአብሔር ቅድስና እንዲወግኑ ተጠየቁ፡፡ (የቱንም ያህል የሥጋ ዘመዶቻቸው ሞት ቢያማቸውም) እርማቸውን ውጠው ከእግዚአብሔር ፍትሕ ጋር በመስማማት እንዲቀጥሉ ተነገራቸው፡፡ የእግዚአብሔር መሠዊያ ሲረክስ፣ ቀዳሚ ተቆርቋሪነታቸው በመሠዊያው ለሚመለከው አምላክ እንጂ መሠዊያውን አርክሰው ለተቀጡት ዘመዶቻቸው አልነበረም፡፡

ዛሬም እንዲያ ነው! ከየትኛውም አካል ጋር ጥብቅ የስሜት ቁርኝት ቢኖረንም ከእግዚአብሔር ክብርና ስም አይበልጥም፡፡ እርሱ ለክብሩ ያለው ቀናኢነት በእኛም ዘንድ እንዲኖር ይፈልጋል፡፡

አንዳንዶቻችን የእግዚአብሔር ክብር ሲነካ ምንም የማይመስለን፣ የሆነ የምንወደው ሰው (አገልጋይ) ሲነካ አገር ይያዝልን የምንል ነን፡፡ ከእግዚአብሔር ቅድስና በላይ የአጥፊው ሞራል ያሳስበናል፡፡ የእግዚአብሔር ስም በገዛ መሠዊያው ላይ ሲቃለልና ሲረክስ “የዝሆን ጆሮ ይስጠኝ” ያሉ ብዙዎች፣ ያጠፉ አገልጋዮች ሲገሰጹ ከዛጎላቸው ብቅ ብቅ ይላሉ፡፡ ኢየሱስ ሲሰደብ አፉን ሸብቦ የተቀመጠ፣ ኢየሱስን በሰደቡት ላይ ጠንካራ ቃል ስትናገር አፉ ይፈታል፡፡ ሊያሸማቅቅህ ሰይፉን ስሎ ይከሰታል፡፡ የእረኞች ዐለቃ ሲዋረድ ያልቆረቆረው፣ የሆነ የሚወደው እረኛ (መጋቢ) የተዋረደ ሲመስለው ያንዘረዝረዋል፡፡

ከእግዚአብሔር ወገን ከሆንን፣ ከሰው ክብር በላይ የእርሱን ክብር አብልጠን እንውደድ፡፡ የምንቆረቆርላቸውን አገልጋዮች፣ የእውነት የምንወዳቸው ከሆነ፣ የእግዚአብሔርን ክብር ነክተው እንዳይጠፉ እንንገራቸው፡፡ ቅድስናውን ለማቃለል ዳር ዳር ሲሉ “ተው” እንበላቸው፡፡ አደባባይ የወጣ ጥፋታቸውን መደባበቅና ለእነርሱ ጥብቅና መቆም፣ ወደ ባሰ እልኸኝት ይመራቸው እንደ ሆነ እንጂ ምንም አይጠቅማቸውም፡፡
የእግዚአብሔር ክብር ይበልጣል!

አሳየኸኝ ለገሠ
510 views19:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-05 19:52:53 “ውጫዊ ተስፋ”

ከፍጥረቱ ጀምሮ ሰው ብቸኛ ተስፋው በሆነው በፈጣሪው ላይ አምጿል፤ ከብቸኛ ከለላው ሽሽቷል። በዚያው ቅጽበት ሞት ነግሦበት፥ በሞት ፍርሃት ቀንበር ውስጥ ይኖራል። ገና ከጅምሩ ኅፍረቱን በግል ጥረቱ ለመሸፈን ቅጠል አገልድሟል፤ ሕሊናውን ሊያነጻ ግን አልቻለም። ሕያው ምንጭ የሆነውን አምላኩን ትቶ፥ ውሃ መያዝ የማይችሉ ቀዳዳ ማሰሮችን ይሰበስባል። ያለ ተስፋ መንከራተት ዕጣ ክፍሉ ሆኗል።

መልካም የማሰብና የማድረግ ፈቃዱና ዐቅሙ በክፉ እስራት ስለተያዘበት፥ ቢዳክርም የውስጡን መሻት ሊያረካ አልቻለም ። በተፍጨረጨረ ቊጥር ይበልጥ ተስፋ ይቆርጣል፤ በክፋት ረግረግ ውስጥ ይሰጥማል። የቁጣና የእርግማን ልጅ ስለሆነ ፍቅርና ምህረትን፤ ጥላቻ ስላዳሸቀው ሰላምና ዕርቅን ውስጡ ክፉኛ ይናፍቃል። በውስጡ ምንም በጎነት የሌለው ምውት ስለሆነ ከውጭ የሆነ የሚቤዤው ተስፋ አስፈልጎታል!

ይኼም ተስፋ፥ ጊዜውን ጠብቈ በ“ወንጌል” በኩል ተገልጧል። ወንጌል፥ ከዑር ምድር ተጠርቶ ለወጣውና የሕዝብ አባት ለተባለው ለአብርሃም በተገባው “ዘላለማዊው ኪዳን” አማካኝነት የተበሠረ የምስራች ነው። በይስሃቅና በያዕቆብ ቤት አልፎ፥ በይሁዳ ነገድ በኩል ተሻግሮ በእሰይ ልጅ በዳዊት “የዘለዓለም ንግሥና ኪዳን” ሆኖ ጸንቷል። የኪዳኑ ተስፋ ከዛሬ ፪ሺ ዓመት በፊት በይሁዳ ቤተልሔም በተወለደው የእስራኤል መሲሕ በኩል ዕውን ሆኗል!

እርሱም [መሲሑ] በዕውቀቱ ብዙዎችን የሚያድን የተስፋውን ቃል የተሸከመ የተስፋው ዘር ነው! ሰው ፈቅዶ በትዕቢቱ አምፆ፥ እግዚአብሔር ፈቅዶ በፍቅሩ የታረቀው በርሱ በኲል ነው። በመስቀል ቤዛነቱ ዕርቅ - ሰው ተስፋውን የሚሳለምበትን ዐዲስ መንገድ በደሙ ተመርቈ ተከፈተለት። በሚገለባበጥ ኪሩቤል የተዘጋው አስፈሪው የፍርድ በር፥ በሥጋው በኩል በድፍረት የሚገባበት የምሕረት በር ኾነ። የዕብራውያን ጸሐፊ ይኼን ሲያስረግጥ እንዲህ ይላል፤ “እኛም የነፍስ መልሕቅ የሆነ ጽኑና አስተማማኝ ተስፋ አለን፤ ይህም ተስፋ ከመጋረጃው በስተ ጀርባ ወዳለው ውስጠኛ መቅደስ ይገባል።” [6:19]

በወንጌል እውነት የተገለጠው “ሕያው ተስፋ” [1ጴጥ 1፥3]፣ ሰው ከውጭ የሚቀበለው “እንግዳ” ተስፋ እንጂ ከውስጡና ከአካባቢው የሚመነጭ አይደለም። “የክብር ተስፋ” [ቆላ 1፥27] መሠረቱ በተስፋው ዘር፥ በመሲሑ ኢየሱስ ላይ እንጂ በሰው ማንነትና ሁኔታ ሊሆን አይችልም። ብዙ ተሞክሮም አልተሳካም!

ሲ.ኤስ.ሉዊስ እንደሚለው “በዚህ ዓለም የምትሻውን ነገር እንሰጥሃለን የሚሉ ብዙ ነገሮች አሉ፤ ነገር ግን አንዳቸውም የሚሉትን አይሰጡህም። ...የትኛውም ልምምድ ሊያረካው የማይችል መሻት በውስጤ ካገኘሁ፣ ሊከተል የሚችለው ማብራሪያ ለሌላ ዓለም የተሠራሁ መሆኔ ነው። ምክንያቱም ፍጡራን ማርኪያ የሌለው መሻት ይዘው አልመጡምና።”

በቅዱሳት መጻሕፍትም፥ ተስፋ አንድም ቦታ ከሰው ማንነትና ልዩ ችሎታ ጋር ተያይዞ አልተገለጸም። የእስትንፋሱ ባለቤት ከሆነው ከአምላኩ ጋር እንጂ! የሰው ውስጣዊ ማንነቱና ችሎታው ተስፋን የመስጠት ዐቅም ቢኖራቸው፥ የተስፋው ዘር [ክርስቶስ] ለድነቱ ባላስፈለገው ነበር። ከአምላክነት የከፍታ ጫፍ ወርዶ፥ የሰብዕን የዝቅታ ጫፍ ባልቀመሰም ነበር።

ከዚህ ውጭ የኾነ ለሰው ልጅ ተስፋ የሚመስል ነገር ሁሉ፤ የማይጨበጥ ጒም፣ የሚያሰጥም አሸዋ፣ የሚያዳልጥ ጭቃ ነው። እንዲያረካን ጠጥተን ጥም የሚጨምር፤ ተደግፈንበት መሰበሩ ሳያንስ ወግቶ የሚያቈስል የሸንበቆ ምርኲዝ ነው። የቤተ ክርስቲያን አባት ቅዱስ አውግስጢኖስ በኑዛዜው ስለመፍትኼው ሲናገር...“ለአንተ ፈጥረኸናልና፤ ልባችንም በአንተ እስኪያርፍ ድረስ ዕረፍት አያገኝም” ብሏል!

ለዚህም ነው፤ የሰውን ዐቅምና ልዩ ችሎታ ከሚያጎሉና ከሚያንቈለጳጵሱ መድረኮች፥ እንዲሁም ሰው ተኮር “ሰባኪያን” መራቅ የሚያስፈልገው! ጊዚያዊ ተስፋዎቻችንም ቢሆኑ እንኳ፥ ትርጉም አግኝተው ሊያረኩን የሚችሉት ከማያሳፍረው “የክብር ተስፋ” መደላድል ላይ ሲስፈነጠሩ ብቻ ነው!

መልካም እሑድ!

ፍጹማን ግርማ
407 views16:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ