መነጠል በድጥ ጎዳና ላይ ፤ እግሬ ይራመዳል ታጥቦ ጭቃነትን ፤ ልቤ ይላመዳል ያገኘውን ለመዳሰስ ፤ እጄ ይፈጥናል የሞት ፍሬን ለመቅመስ ፤ ምላሴ ይጎመጃል ሀሳቤን በሙሉ ፤ ከምድሩ ላይ ጥዬ ከሞት ተጣብቄአለሁ ፤ ከግንዱ ተነጥዬ በተነሳው ወጀብ ፤ ላለመወድቅ ብጥርም እግሬ በድጥ ላይ ነውና ፤ መሰበሬ አይቀርም። ዕድፍ የለብኝም ፤ ብትልም ምላሴ በታጥቦ ጭቃነት ፤ ቆሽሿል ልብሴ ለአምላክ መሸነፌን ላሳይ ፤ እጆቼን ባነሳም በግብዝነት እሾህ ፤ መዳፎቼ ተወግተው - ተጨማልቄአለሁ በደም ‹‹ካንደበቴ እውነት›› ፤ ከአፌ ፅድቅ ርቆ ከሞትኹ ሰነበትኹኝ ፤ አጥንቴ ደርቆ በዚህ ኹሉ ውድቀት ውስጥ ፤ ነፍሴ ብታልፍም በንስሃ ለመታጠብ ፤ እንባን አላፈስም ምክንያቱም የእውነት ቃል ቀሎብኝ ፤ በስጋዊነት ደምቄኣለሁ በርኩሰት ካባ ፤ በዓለም ነግሻለሁ አንዳንድ ጊዜ በሞኞች መንደር በቂሎች ሰፈር ውርደትን በክብር መለወጥ ፤ ከፅድቅ ይቆጠራል የሞት ፍሬን ማፍራት ፤ በብዙ ያስከብራል። ቢሆንም ቢሆንም ይሄንን እውነት ልክደው አልሻም ሀሳቤን በሙሉ ፤ ከምድሩ ላይ ጥዬ ከሞት ተጣብቄአለሁ ፤ ከግንዱ ተነጥዬ፡፡ ///// ቢቶ 173 viewsedited 19:32