#ችሎት
ዮናስ ከእስር ቢፈታም "ለዳግም ጥያቄ ትፈልጋለህ?" ተብሎ ድጋሚ መታሰሩ ተነገረ
የጉማ አዋርድ መሥራችና አዘጋጅ ፤ ዳይሬክተር ዮናስ ብርሃነ መዋ ትናንት " በ9ኛው የጉማ አዋርድ ዝግጅት ተጠናቆ ሳለ ፤ ... ለጥያቄ እፈልገዋለን " በማለት ቦሌ ትራፊክ መምሪያ በተለምዶ ስሙ "አንበሳ ጋራዥ" አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ታሰሮ ነበር።
ዛሬ ፣ ከቀኑ 5:00 ሰዓት ላይ 24 (ኮከብ አዳራሽ) በሚገኘው ፍርድ ቤት ቀርቦ ነበር። ፍ/ቤቱ በ 5,000 (በአምስት ሺህ ብር) ዋስትና ለቆት ነበር።
ይሁን እንጂ ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ ከፖሊስ ጣቢያ እንደወጣ ፤ "ለዳግም ጥያቄ ትፈልጋለህ?" ተብሎ ወደ ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ መወሰዱን እንዲሁም ሰኞ ፍ/ቤት እንደሚቀረብ ከቤተሰቡ ያገኘሁት መረጃ ይጠቁማል፡፡