Get Mystery Box with random crypto!

የቱሪዝም ሚኒስቴር የ2015 ዕቅድ በፓርላማ ውድቅ ተደረገ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድ | ሰሌዳ | Seleda

የቱሪዝም ሚኒስቴር የ2015 ዕቅድ በፓርላማ ውድቅ ተደረገ

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ቋሚ ኮሚቴ ጥቅምት 28 ቀን 2015 ዓም. ከቱሪዝም ሚኒስቴር የቀረበለትን የ2015 ዓ.ም. የዘርፉን ዕቅድና የመጀመርያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ካዳመጠ በኋላ፣ ሁለቱንም ውደቅ አድርጓል፡፡ ሚኒስቴሩ የዓመቱን ዕቅድና የሩብ ዓመቱን አፈጻጸም ሪፖርት እንደገና አዘጋጅቶ በማኔጅመንት አፀድቆ እንዲያመጣ ታዟል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው አባላት ሚኒስቴሩ ሦስት ዓይነት የተለያዩ ግቦችን ማቅረቡና በሰነድ የቀረበው ሪፖርትና ገለጻ የተደረገው ልዩነት ስላለው ለመገምገም አስቸጋሪ እንደሆነባቸው ገልጸዋል። የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ስለሺ ግርማ ግን ሪፖርቶቹን ሲያቀርቡ፣ ሰነዶቹ ማለፍ ያለባቸውን ሁሉ ሒደቶች ያላለፉ መሆናቸውን ጠቅሰው ነበር፡፡  

via - Reporter