በባለፈው ጦርነት የወሎን ህዝብ ያክል መስዋዕትነት የከፈለ መከራና ስቃይ ያየ የለም ። በዚህኛውም ጦርነት የጦርነቱ አውድማ እንዲሆን የተመረጠው ወሎ ነው ። ወሎ የኢትዮጵያን መከራ እንዲሸከም የተፈጠረ እስኪመስል ድረስ እየተነባበረ ህዝባችንን እያመሰቃቀለው ነው ።
የአማራ ክልል መንግስት እንደሆነ ለወሎ ብዙም ደንታ እንደሌለው ትላንትም አይተነዋል ዛሬም እያየነው ነው ።
መሆን ያለበት የወሎ ህዝብ ማንንም ሳይጠብቅ ከመከላከያ ሀይላችን ጎን ተሰልፎ ደጀንና ጋሻ ሆኖ ወራሪውን ሀይል እስከመጨረሻ መታገል ነው ። ህዝባችን ከባለፈው ስብራት ሳያገግም ዛሬም እንደገና ሌላ ስብራት መጥቶበታል ። በመሆኑም ሳንሰበር እንታገል ።
ስንታገል ከምንከፍለው መስዋዕትነት በላይ ሳንታገል የምንከለው ዋጋ በእጅጉ ይከፋልና አሁንም ከሰራዊታችን ጎን ሆኑን እንታገል !
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial