2021-09-25 17:49:30
የሲድቅ ( የእውነተኝነት ) ደረጃው
ሲድቅ ከላኢላሃ ኢለ ላህ ሸርጦች አንዱ ሲሆን ታላቅ የቀልብ ዒባዳ ነው ። የቀልብ ዒባዳዎች ባጠቃላይ ከሱ ነው የሚመነጩት ። የመልካም ስራ ሩሕ ነው ማለት ይቻላል ። የኢማን ባለቤቶች ከሙናፊቆች የጀነት ሰዎች ከጀሀነም ሰዎች የሚለዩት በሱ ነው ። ሲድቅ የዲን መሰረት ነው ። የእውነተኛ ሰው ደረጃ ከነብያቶች ደረጃ ቀጥሎ ነው የሚመጣው ። ይኀውም በሚቀጥለው የአላህ ቃል ማየት እንችላለን : –
" وَمَن يُطِعِ اللَّهَ وَالرَّسُولَ فَأُولَٰئِكَ مَعَ الَّذِينَ أَنْعَمَ اللَّهُ عَلَيْهِم مِّنَ النَّبِيِّينَ وَالصِّدِّيقِينَ وَالشُّهَدَاءِ وَالصَّالِحِينَ ۚ وَحَسُنَ أُولَٰئِكَ رَفِيقًا "
النساء ( 69 )
" አላህንና መልክተኛውንም የሚታዘዝ ሰው እነዚያ ከእነዚያ አላህ በእነርሱ ላይ ከለገሳቸው ከነቢያት፣ ከጻድቃንም ፣ ከሰማዕታትም፣ ከመልካሞቹ ጋር ይኾናሉ ፡፡ የእነዚያም ጓደኝነት አማረ ፡፡ "
ለዚህም ነው አላህ አማኞችን ከእውነተኞች ሁኑ ብሎ ያዘዘው ። ይህንንም በሚቀጥለው የአላህ ቃል እናገኘዋለን : –
" يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَكُونُوا مَعَ الصَّادِقِين َ"
التوبة ( 119 )
" እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ ፤ ከእውነተኞቹም ጋር ኹኑ ፡፡ "
አላህ የመልካም ስራ ባልተቤቶችን ሲነግረን መልካም ስራቸውን ዘርዝሮ ካወደሳቸው በኋላ እውነተኞች መሆናቸውን መስክሮ አላህን የሚፈሩት እነርሱ ናቸው ብሎ ነው የዘጋው ። የሚቀጥለውን አንቀፅ እንመልከት : –
" لَّيْسَ الْبِرَّ أَن تُوَلُّوا وُجُوهَكُمْ قِبَلَ الْمَشْرِقِ وَالْمَغْرِبِ وَلَٰكِنَّ الْبِرَّ مَنْ آمَنَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ وَالْمَلَائِكَةِ وَالْكِتَابِ وَالنَّبِيِّينَ وَآتَى الْمَالَ عَلَىٰ حُبِّهِ ذَوِي الْقُرْبَىٰ وَالْيَتَامَىٰ وَالْمَسَاكِينَ وَابْنَ السَّبِيلِ وَالسَّائِلِينَ وَفِي الرِّقَابِ وَأَقَامَ الصَّلَاةَ وَآتَى الزَّكَاةَ وَالْمُوفُونَ بِعَهْدِهِمْ إِذَا عَاهَدُوا ۖ وَالصَّابِرِينَ فِي الْبَأْسَاءِ وَالضَّرَّاءِ وَحِينَ الْبَأْسِ ۗ أُولَٰئِكَ الَّذِينَ صَدَقُوا ۖ وَأُولَٰئِكَ هُمُ الْمُتَّقُون َ"
البقرة ( 177 )
" መልካም ሥራ ፊቶቻችሁን ወደ ምሥራቅና ምዕራብ አቅጣጫ ማዞር አይደለም ፡፡ ግን መልካም ሥራ በአላህና በመጨረሻው ቀን ፣ በመላእክትም ፣ በመጻሕፍትም ፣ በነቢያትም፣ ያመነ ሰው ገንዘብንም ከመውደዱ ጋር ለዝምድና ባለቤቶችና ለየቲሞች ለምስኪኖችም ፣ ለመንገደኞችም ፣ ለለማኞችም ፣ ለጫንቃዎችም (ማስለቀቅ) የሰጠ ሰውና ሶላትንም ደንቡን ጠብቆ የሰገደ ፣ ዘካንም የሰጠ ፣ ቃል ኪዳንም በገቡ ጊዜ በኪዳናቸው የሞሉ (ሰዎች ሥራ) ነው ፡፡ በችግር በበሽታና በጦር ጊዜም ታጋሾችን (እናወድሳለን) ፡፡ እነዚህ እነዚያ እውነትን የያዙ ናቸው ፡፡ እነዚያም ተጠንቃቂዎቹ እነርሱ ናቸው ፡፡ "
ሸኹል ኢስላም – ረሒመሁላሁ – እንዲህ ይላል : –
" والصدق والإخلاص هما في الحقيقة تحقيق الإسلام والإيمان ، فإن المظهرين للإسلام ينقسمون إلى مؤمن ومنافق ، والفارق بين المؤمن والمنافق هو الصدق . فإن أساس النفاق يبنى عليه هو الكذب ، ولهذا إذا ذكر الله حقيفة الإيمان نعته بالصدق كما في قوله تعالى : –
" ሲድቅና ኢኽላስ የኢማንና የእስልምና ማረጋገጫ ናቸው ። እስልምናን የሚያሳዩ ሰዎች ወደ ሙእሚንና ሙናፊቅ ይከፈላሉ, በሙእሚንና በሙናፊቅ መካከል የሚለየው ሲድቅ ነው ። የንፍቅና መሰረቱና መገንቢያው ውሸት ነው ። ለዚህ ነው አላህ አውነተኛን ኢማን ሲገልፅ በሲድቅ የሚገልፀው በሚቀጥለው የአላህ ቃል እንደመጣው : –
" قَالَتِ الْأَعْرَابُ آمَنَّا ۖ قُل لَّمْ تُؤْمِنُوا وَلَٰكِن قُولُوا أَسْلَمْنَا وَلَمَّا يَدْخُلِ الْإِيمَانُ فِي قُلُوبِكُمْ ۖ وَإِن تُطِيعُوا اللَّهَ وَرَسُولَهُ لَا يَلِتْكُم مِّنْ أَعْمَالِكُمْ شَيْئًا ۚ إِنَّ اللَّهَ غَفُورٌ رَّحِيم ٌ"
الحجرات ( 14 )
የዐረብ ዘላኖች «አምነናል» አሉ ፡፡ «አላመናችሁም ፤ ግን ሰልመናል በሉ ፡፡ «እምነቱም በልቦቻችሁ ውስጥ ገና (ጠልቆ) አልገባም ፡፡ አላህንና መልክተኛውንም ብትታዘዙ ከሥራዎቻችሁ ምንንም አያጎድልባችሁም ፡፡ አላህ መሓሪ አዛኝ ነውና» በላቸው ፡፡
" إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ الَّذِينَ آمَنُوا بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ ثُمَّ لَمْ يَرْتَابُوا وَجَاهَدُوا بِأَمْوَالِهِمْ وَأَنفُسِهِمْ فِي سَبِيلِ اللَّهِ ۚ أُولَٰئِكَ هُمُ الصَّادِقُونَ "
الحجرات ( 15 )
(እውነተኛዎቹ) ምእምናን እነዚያ በአላህና በመልእከተኛው ያመኑት ከዚያም ያልተጠራጠሩት በገንዘቦቻቸውና በነፍሶ ቻቸውም በአላህ መንገድ የታገሉት ብቻ ናቸው ፡፡ እነዚያ እነሱ እውነተኞቹ ናቸው ፡፡
" لِلْفُقَرَاءِ الْمُهَاجِرِينَ الَّذِينَ أُخْرِجُوا مِن دِيَارِهِمْ وَأَمْوَالِهِمْ يَبْتَغُونَ فَضْلًا مِّنَ اللَّهِ وَرِضْوَانًا وَيَنصُرُونَ اللَّهَ وَرَسُولَهُ ۚ أُولَٰئِكَ هُمُ الصَّادِقُون َ"
الحشر ( 8 )
" ለእነዚያ የአላህን ችሮታና ውዴታውን የሚፈልጉ ፣ አላህንና መልክተኛውንም የሚረዱ ኾነው ከአገሮቻቸውና ከገንዘቦቻቸው ለተወጡት ስደተኞች ድኾች (ይስሰጣል) ፡፡ እነዚያ እነርሱ እውነተኞቹ ናቸው ፡፡"
فأخبر أن الصادقين في دعوى الإيمان هم المؤمنون الذين لم يتعقب إيمانهم ريبة وجاهدوا في سبيله بأموالهم وأنفسهم ."
التحفة العراقية ، ص ( 20 – 21 )
" አላህ በኢማናቸው እውነተኛ የሆኑት እነዚያ ኢማናቸው ጥርጣሬ ያልተከተለው በገንዘባቸውና በነፍሳቸው በአላህ መንገድ ላይ የታገሉት መሆናቸውን ተናገረ ። "
በመቀጠልም አንድ ባሪያ የቂያማ ቀን ከእሳት ቅጣት የሚጠብቀው ሲድ ብቻ መሆኑን አላህ ሲነግረን እንዲህ ይላል : –
" قَالَ اللَّهُ هَٰذَا يَوْمُ يَنفَعُ الصَّادِقِينَ صِدْقُهُمْ ۚ لَهُمْ جَنَّاتٌ تَجْرِي مِن تَحْتِهَا الْأَنْهَارُ خَالِدِينَ فِيهَا أَبَدًا ۚ رَّضِيَ اللَّهُ عَنْهُمْ وَرَضُوا عَنْهُ ۚ ذَٰلِكَ الْفَوْزُ الْعَظِيمُ "
المائدة ( 119 )
1.6K viewsانور فضلأ, 14:49