ሰማሺኝ አለሜ ? መሄድ እሚሉት ቃል ፥ ከሀገር የሰፋ የትርጉም ኩታንኩት ፥ ጉንጭን እሚያለፋ መሄድ ሲሉ ሰምተሽ ! እንደ ያሬድ ዜማ ፥ እንደ እግዜር ያለ እረፍት እንደ ቀን ቅዳሴ ፥ እንደ ሌት ማህሌት የ 6 ቀን እድሜ ፥ በ 60 አመት ሀሳብ ያንድ ቅፅበት ቀመር ፥ እንደ ህያው ጥበብ ያነፅነውን ፍቅር ! ባንድ የስልክ ጩኸት ፥ ባልፈልግህም ቃል ፍቅርሽን ገፈሺኝ ፥ እኔነቴ ወልቋል የመውደድ ግርማዬ ፥ በሀፍረት ተራቁቷል ። ሰማሺኝ አለሜ ? መሄድ የሚሉት ቃል ፥ የማጣት ታላቁ የክፋቱ ክፋት ፥ ከኔ አንቺን ማራቁ ባንቺ 1 መሄድ ውስጥ ፥ ሺ ጥሎኝ የሄደ ክንድሽ ያረፈበት ፥ ጎኔ እየነደደ አቅሜ እንዳለልነበርሽ ዛሬ አቅም ቢከዳኝ አካሌ እየራደ መሄድሽን ረግማለሁ ! ደግሞ እጠይቃለሁ ? በቅተኸኛል ያልሺን ፥ በባዶ ሀሳቤ በተጎሳቆለው ፥ በድኩም ምናቤ ቢመላለስብኝ ልክ እንደ እግዚኦታ ፥ እንደ ቤተስኪያን ደውል፥ አንገቴን ደፋለሁ አፍጦ ከሚያየኝ አቧራ መሬት ላይ ፥ መልስ እጠብቃለሁ ሰማሺኝ አለሜ ባንቺ መሳቅ ቀኔ በርቶ ፥ በሀዘንሽ ሲጠፋብኝ እውር ልቤ ባንቺነትሽ ፥ እንደሚያይ ሰው ሲዘልብኝ ተዚያ ተቤተስኪን ፥ ከመላዕክት መቅደስ ፦ ከእግዜሩ ደጃፍ እነኛን ጥዑም ቀን ፥ በመዋደድ ቅኔ ፥ አብረን ስናሳልፍ እጅሽ እጄን ይዞ ፥ የተባባልነው ቃል የልጆቻችን ስም ፥ ማን ትባል ማን ይባል እንዳልነተረኩሽ ፥ እንዳልጨቀጨቅሺኝ ዛሬ ግን የለሽም ፥ ብቻዬን ከ እግዜር ጋ ፥ ሄደሻል ጥለሺኝ ! ሰማሺኝ አለሜ ? መሄዱንስ ሂጂ ፥ ብርሀን ይነጠፍልሽ ይቃናልሽ መንገድ ፥ ክንፈ መላዕክት ይጠብቅሽ ደግሜ ልሻለሁ ፥ ይቅናልሽ መንገዱ ሊያገኝሽ ይጋደል ፥ ይሙትልሽ ወንዱ ሌሊቱ እንዲረዝም ፥ እያልኩኝ ባልነጋ እኔ ግን አለሁኝ ፥ ተኝቼ እየቃዠሁ በትዝታሽ አልጋ ሰርክ እየደነገጥኩ ፥ ሰርክ እየባነንኩኝ የመሄድሽን ህልም ፥ ልትመጣ ነው በሚል ፥ እየተረጎምኩኝ እኔ ግን አለሁኝ በትዝታሽ አልጋ ፥ ላልነቃ ተኝቼ መሄድሽን ላልወቅስ ፥ ስላንቺ ልሸነፍ ፥ ምዬ ተገዝቼ 35.3K views04:52