Get Mystery Box with random crypto!

ከመጻሕፍት ዓለም 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ rovibookben — ከመጻሕፍት ዓለም 🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ rovibookben — ከመጻሕፍት ዓለም 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @rovibookben
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 29.68K
የሰርጥ መግለጫ

Join @Rovibook
😎
<|>
/\
👢👢
መካሪ ከተገኘ ህይወት ቀላል ነው!!
ለማንኛውም ማስታወቂያ ነክ ጉዳዮች @RASNAMRUD ያናግሩን

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-06 22:27:35
7.9K views19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 22:26:58 ታሪኩ የሚጀመረው በ 2002 ዓ.ም ከቤሩት ወደ አዲስአበባ የሚበረውና ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አይር መንገድ የሆነው ቦይንግ 787 አውሮፕላን ተከስክሶ ከ90 ሰዎች ጋር ባሏ የሞተባት ሎዛ የተባለች ትንታግ ገፀ-ባህሪ የአደጋውን መንስዔ በራሷ መንገድ ለማጣራት የምታደርገውን ውጣ ውረድ በመተረክ ነው።
የሎዛ ይህ ድርጊት በኢትዮጵያና በሊባኖስ አይር መንገዶች አልተወደደላትም። እንዲያውም በግዙፉ ቦይንግ ካምፓኒ እንደ ጭራቅ እንድትታይና እሷን ማስወገድ የመጨረሻ አማራጫቸው አድርገው እንዲወስዱ አነሳሳቸው።

ሳታውቀው እንዲህ አይነት አጣብቂኝ ውስጥ የገባችው ሎዛ ገለልተኛ የአደጋው መንስኤ አጣሪ ኮሚቴ ያወጣውን ድምዳሜ ስታይ ይብሱኑ እንድትበሳጭና ነገሩን ገፍታበት ትክክለኛውን የአደጋውን መንስዔ በራሷ መንገድ ማጣራት በአደጋው ለተቀጨው ባሏ ጥልቅ ፍቅሩን የምትገልጽበት አይነተኛ ማካካሻ አድርጋ ወሰደችው።

ግን ደግሞ የውርደት ካባ ላለመከናነብ በመላው ዓለም የዕዝ ሰንሰለቱን የዘረጋው የቦይንግ ካምፓኒና ስሙ ምስጢራዊ የሆነ ድርጅት ሎዛን ለማስወገድ የመጨረሻ ካርዳቸውን መዘዋል--ግብግቡ የሚጀምረው እዚህ ጋ ነው እንግዲህ !

መጽሐፉ ልቦለዳዊ ቢሆንም የተከሰቱ እውነተኛ ሁነቶች ላይ ተንተርሶ የተጻፈ ነው(በ2002 ዓ.ም ከቤሩት አዲስአበባ በረራውን ያደረገ ቦይንግ 787 አውሮፕላን ተከስክሶ 90 ያህል ሰዎች እንደተቀጠፉ ልብ ይሏል )።

በተያያዘና ተመጋጋቢ በሆነ ሁኔታ የተማሩ የኢትዮጵያ ምሁራን ከዚህ በፊት ባልተካሄደበት መንገድ ኢትዮጵያን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ቁጥር አንድ ሀገር ለማድረግ እንቅስቃሴውን ሲያጧጥፉ መጽሐፉ ይተርካል። እነዚህ ምሁራን ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን አፍሪካን በቴክኖሎጂ ለማመንደግ የተነሳሱ ናቸው። ይህ ሁኔታ የእርዳታ ድርጓቸውን እየበተኑ ጥሬ እቃችንን በሚያጋብሱ ምዕራባውያን አልተወደደም--ሌላ ግብግብ!


በመጨረሻም ኢትዮጵያ በራሷ ባንዲራ ያጌጠች ሳታላይት ስታመነጥቅ የመጽሐፉ ሽፋን ላይ ይታያል።( ልብ በሉ! ይህን ሽፋን ይዞ መጽሐፉ የታተመው በ2008 ዓ.ም ነው)። ይህ ነገር መጽሐፉን ትንቢታዊ ያደርገዋል። ምክኒያቱም ከሁለት ዓመት በኋላ በቻይና ጀርባ አሳዝላም ቢሆን ኢትዮጵያ የራሷን ሳታላይት አመጥቃለች!


ሌላውን ከመጽሐፉ ......

መጽሐፉን በነጻ በ PDF ለማውረድ ከታች ያለውን link ተጠቀሙ!!!

ምርጥ :ልብ አንጠልጣይ
:ፍቅርን
:ስለላን
:ሳይንስን
:ትንቤትን
:መድሃኒቶችን አጠቃሎ የያዘ!!!!

*እመኑኝ.አንዴ ከከፈታችሁ ሳትጨርሱ አታቆሙም!

*ኢትዮጵያን የሚወድ ያንብበው!!!
ብርሃኑ በቀለ ሰንዶታል!!!
*NB..የፈጠራ ክህሎት ያላችሁ ምናባችሁን ስለሚያሰፋው ሳታነቡት አትለፉ!!

መልካም ንባብ
7.8K views19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 21:54:26 ድሳካር.pdf
ድሳካር.pdf


ምርጥ :ልብ አንጠልጣይ
:ፍቅርን
:ስለላን
:ሳይንስን
:ትንቤትን
:መድሃኒቶችን አጠቃሎ የያዘ!!!!

*እመኑኝ.አንዴ ከከፈታችሁ ሳትጨርሱ አታቆሙም!

*ኢትዮጵያን የሚወድ ያንብበው!!!
ብርሃኑ በቀለ ሰንዶታል!!!
*NB..የፈጠራ ክህሎት ያላችሁ ምናባችሁን ስለሚያሰፋው ሳታነቡት አትለፉ!!

*NB..ኢትዮጵያዊነት የሚያንገሸግሻችሁ አታንብቡት!!
10.6K views18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-27 22:23:53 ከመጻሕፍት ዓለም በ pinned Deleted message
19:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 22:17:23 ክፍል 2

ኡኡኡኡኡኡኡኡኡ....ከወደውጪ ድምፅ ተሰማ፡፡ አስር አለቃ ጎረቤታቸውን በዱላ አናቱን ብለው በሩ ላይ ደፍተውት ነበር፡፡

ሰይጣን አጀንዳውን ይዞ አስር አለቃ ግቢ ሲደርስ ነገር ተደበላልቆ ጠበቀው፡፡ ጉዳዩን በጥንቃቄ አጣራና አጀንዳው ላይ እንዲህ ሲል ከተበ "የአስር አለቃው ጉዳይ ከእቅድ በላይ ተፈፅሟል፡፡"

ሦስት ፖሊሶች ኮሌታቸው ጨምድደው ወደያዟቸው አስር አለቃ ጆሮ ጠጋ አለና "አንተ ሸፋፋ! ስማ..! አሁን በግድያ ሙከራ ዘብጥያ ትወርዳለህ የተበደረው ጎረቤትህ ተሽሎት ወደ ቤቱ ይመለሳል..፡፡ ያች አንቋራሪ ልጅህም የትም ስታንቋር

ር ስለምትውል ቤትህ ሰው የለም፡፡ ሚስትህና ጎረቤትህ ብቻቸውን እዚህ ሰፊ ግቢ ራስህ አልጋ ላይ...ሂሂሂሂሂሂ ቂቂቂቂቂቂ አይ ሸፋፋው!!

ይልቅ ሚስትህን ዓይንህ እያየ ከምትወሰድ አንዱን ፖሊስ በካራቴ ድፋውና አምልጥ...ወታደር አይደለህ...? አስር አለቃ አይደለህ?.... ኮማንዶ ነኘ እያልክ በየጠላ ቤቱ ስታወራ አልነበር...? ወይስ ዝም ብለህ ስትወሽክ ነው...፡፡"

አስር አለቃ ቀስ ብለው ከጎናቸው የቆመውን ፖሊስ ተመለከቱት፡፡ክስት ያለ ነው...በዛ ላይ የያዘው መሳሪያ የከበደው ይመስላል፡፡ ሁለቱም ፖሊሶች ቢሆኑ ያን ያህል የሚስፈሩ አይደሉም ቀድረ ቀላል ነገር ናቸው፡፡ " ይሔኔንንስ መሣሪያውንም መንጠቅ አያቅተኘ " ሲሉ አሰቡ፡፡ ፖሊሶቹ አስር አለቃን እያጣደፉ ወደ ጣቢያ ወሰዷቸው፡፡

ዷ....! ዷ............መንደርተኛው ከሩቅ የተኩስ ድምፅ ሰማ

"ምንድነው....?"

"እስረኛ ሊያመልጥ ሞክሮ.....ፖሊሶቹ እግሩን ሰንክለው አቆሙት.....!

ሰይጣን በሳቅ ፍርስ አለ፡፡ እናም አጀንዳው ላይ እንዲህ ሲል ፃፈ "የእግሩ ጉዳይ አልቋል አሁን ነፍሱን ማንሻፈፍ ይቀረኛል!!"

ከዛም ሰይጣን ቀይ እስኪሪቢቶ አወጣና እየተፍነከነከ እንዲህ ሲል ፃፈ

"አስር አለቃ አምሳ አለቃ መቶ አለቃ ሻለቃ ጄነራል ሚኒስተር ...ጠቅላይ ሚኒስተር ሁሉም እግር አላቸው፡፡ እንኳን እነርሱ አገርም እግር አላት ስንፈልግ እናንሻፍፋታለን!!!"

ደራሲ #አሌክስ_አብርሃም
#ዙቤይዳ ከሚለው መፅሐፍ

#እግር_በእግር
ለንባብ እንዲመች ተደርጎ የተወሰደ

@jahABP ነኘ አስተያየታችሁን አድርሱኘ

@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
33.8K views19:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 18:07:05
AB PHOTOGRAPHY


r.....for reflection

ምስሉን ተጭነው ይመልከቱ ቴክኖ ስፓርክ kb ወንድሜ ስልክህን እንዳነሳበት ስለሰጠኸኘ አመሰግናለሁ

@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
21.0K views15:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 18:04:50 AB PHOTOGRAPHY & GRAPHIC DESIGN

#እግር_በእግር

አንድ ቀን ሰይጣን በመንደሩ ወደሚፈሩት እና ወደ ሚከበሩት አስር አለቃ ደባልቄ ግዛው ቤት ሔደና ቀዳሚሚ ተከታይም ሳያደርግ "ደባልቄ!!" ብሎ በስማቸው ጠራቸው፡፡

አስር አለቃ ፊታቸውን በቁጣና በግርምት አኮማትረው ድምፁን ወደሰሙበት ዞር ቢሉ በአካባቢው ሰው የሚባል የለም፡፡ እዚህ ሰፈር አንድም ሰው የአስር አለቅነትን ማዕረጋቸው ሳያስቀድም የአባቻቸውን ስም ሳያስከትል እንዲህ ንፋስ እንዳነሳው ፌስታል ስማቸውን ለብቻው አንጠልጥሎ የሚነሳ ሰው የለም፡፡

እንኳን ሰው የዚህ ሰፈር ሰይጣን ቢሆን ራሱ እንደዚህ አስር አለቃን አቃሎ እና አበሻቅጦ ይጠራቸዋል ተብሎ አይታሰብም፡፡ እንዴት ሆኖ! ምን ሲደረግ...!

እንግዲህ አስር አለቃ የተጣሉ ባልና ሚስት አስታርቀው ገና መመለሳቸው ነበር፡፡ ልክ በራቸው ላይ ሲደርሱ ነው ሰይጣን የጠራቸው፡፡ ምን ይጠራቸዋል ያዋረዳቸው እንጂ! ቢሆንም 'ጆሮዬ ነው' ብለው ወደ ቤታቸው ግቢ ሊገቡ ርምጃ ሲጀምሩ፣

"አንተ ደባልቄ ! የሚደባልቅ ይደባልቅህ! ሲጠሩ አትሰማም!? ደንቆሮ!!" ብሏቸው እርፍ፡፡ በዚህ ቢበቃማ ጥሩ ነበር "ምን ያራሩጥሃል? ያቺ መንሽ እግር ሚስትህ እንደሆነች የትም አትሔድብህ ተወዝፋ ነው የምትጠብቅህ" ሲል ዘለፋቸው፡፡

አስር አለቃ መጀመሪያ በተናጋሪው ድፍረት ግርርርርርርርርምምምምምም አላቸው ቀጥሎ የንግግሩ ትርጉም አዕምሮአቸው ውስጥ ሲተረጎም ደማቸው ፈላ፡፡ ላለፉት አርባ ዓመታት እንዲህ ተንቀውም እንዲህ ደማቸው ፈልቶም አያውቅም፡፡ ከዘራቸውን ጠበቅ አድርገው ጨበጡና ድምፁን ወደሰሙበት ፎክረው ዞሩ፡፡

"ያንበሳው ግልገል!" በአካባቢው የሰው ዘር የለም!!

"እንኳን ፊቴ ያላገኘሁት ደመ ከልብ አድርጌው ዘብጥያ መውረዴ ነበር፡፡" አሉና ከዘራቸውን ወደ ግራ እጃቸው አጋብቸው ከዘራ በያዙበት እጃቸው አማተቡ፡፡

"ሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂ..." የሰይጣን የሚያበሳጭ እና የሚሰቀጥጥ ሳቅ ጆሮአቸው ሥር ተቅለጨለጨ.......

" ድሮም ከእግዜራችሁ በፊት ዱላችሁ ነው ትዝ የሚላችሁ....ነውጠኛ ሁሉ.... #የምትዠልጠው_ስታጣ_ታማትባለህ? አይሸፋፋው አስር አለቃ....ሂሂሂሂሂ ሁሁሁሁ ቂቂቂቂቂ..." አለ ሰይጣን ግቢ ግቢያቸው ውስጥ ቀድሞ ገብቶ #ካሉበት_አርባ_ክንድ_ርቆ ከቆመ በኀላ፡፡

አስር አለቃ ግራ ተጋቡ፡፡ ንዴታቸውን ዋጥ አድርገው እየተጣደፉ በቁጣ ወደ ቤታቸው በር ገሰገሱ፡፡

አስር አለቃ አቋማቸው እንደሰምበሌጥ ቀጥ ያለ ስፖርተኛ አቋም ነው፡፡ ሰው ሁሉ "አቤት ቁመና!!" ይላቸው፡፡ ሰይጣን ግን ወደ ቤታቸው ሲጣደፉ የሚያበሽቅ ንግግር

"ሸፋፋ ..ሸፋፋ ትላለህ! ሲራመዱ አይተህ...ደግሞ ወታደር ነኘ ይላል እንዴ? ይሄን ደጋን የመሰለ እግር ይዞ ሂሂሂሂሂሂ...እንኳን አገር ልትጠብቅ በዚህ ሸፋፋ እግርህ ሚስትህንም አትጠብቅ ተመልከት የእግርህን ክፍተት በልጅነትህ ፀሐይ አላሞቀችልህም ያቺ ጨብራራ እናትህ!!! ኪኪኪኪኪ..."

አስር አለቃ ከሳቸው አልፎ እናታቸው ማዋረዱ ቢያንገበግባቸውም የተናጋሪው ማንነት ስለገባቸው እንደገና አማተቡና

"የማርያምን ብቅል ፈጭቻለሁ ቱ! ቱ! ቱ! አንተ ፖለቲከኛ ሰይጣን!" ብለው ወደ መሬት አንዴ ወደሰማይ ትፍ! ትፍ! ቀጠል አድርገውም " አንተ ክፋ አውቄኻለው እንዲ አቅልሎ የሚጠራኘ እንዳንተ ያለው ቀላል እንጂ ሌላ እንደማይሆን መች አጣሁት?" ካሉ በኀላ ቆይ ላግኘህ ሚመስል ዛቻ ከዘራቸውን ነቀነቁና ነጠቅ ነጠቅ ብለው በመራመድ ወደቤታቸው ገቡ፡፡

ሰይጣንም አጀንዳውን ከፍቶ "አስር አለቃ ደባልቄ" በሚለው ፊት ለፊት በቀይ እስኪሪቢቶ 'ራይት' አደረገ፡፡ መንገዱንም ቀጠለ! እየሳቀ እና እያፏጨ...! ይሄ ሸፋፋ ለዛሬ ይበቃዋል ሲበሳጭ ይደር፡፡ ነገ ደሞ በተመቸኘ ሰዓት ብቅ ብዬ ነጅሼው እሔዳለሁ፡፡ አለና እየሳቀ መንገዱን ቀጠለ፡፡

አስር አለቃ ቤት ግራና ቀኘ ባሉት ጫት ቤቶች ተኮልኩለው ጫት የሚቅሙትን ወጣቶች በኩራት እየተመለከተ
"ርስቴ እየተስፋፋ ነው!" ብሎ እየኮራ ቁልቁቅል ወደ ወንዙ!

በእርግጥም ሰይጣን እንዳሰበው አስር አለቃ ሌሊቱን እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር ነበር ያደረው፡፡ እንደዛ ያበሻቀጣቸው ሰይጣን ነው ለማለት ጥርጣሬ ገባቸው "እኔ የትኛው ቅድስና ኖሮኘ ሊፈትነኘ ይመጣል?"
አሉ ለራሳቸው፡፡ እንደውም አንዱ ጎረቤታቸው ተደብቆ እንደሰደባቸው ጠረጠሩ፡፡ "ማን ሊሆን ይችላል? ሌሊቱን ሙሉ ተብሰለሰሉ ፡፡

"ይች ጎረቤቴ የትነበርሽ ትሆን እንዴ? የለም ድምፁ የወንድ ነው፡፡ ግንበኛው አሰፋ መሆን አለበት እሱ ለካ ለሥራ ክፍለሃገር ከሄደ ሁለት ወሩ... እና ማናባቱ ነው...፡፡" ወደ ንጋቱ ላይ አንድ ሃሳብ ብልጭ አለላቸው፡፡ አረጋ!! ድንበር እየገፋ የበጠበጣቸው ጎረቤታቸው!! አረጋ! እሱስ ሚስታቸውን በምኞት ዓይኑ የሚቃኘ ጥጋበኛ ነው ድምፁ መጣላቸው ራሱ ነው!

"አገኘሁት ብለው ዘለው ከአልጋቸው ተነሱ፡፡ ሚስታቸው እማማ የውብዳር በአስር አለቃ አነሳስ ደንግጠው

"በስማም ምን ሆኑ? ሲሉ ጠየቁ

"ዝም በይ ሸፋፋ!" ሲሉ ሚስታቸውን ሰደቧቸው ከሰይጣን በተዋሷት ያደረች ስድብ፡፡ አስር አለቃ ከዛ በፊት ሚስታቸው ሰድበው አያውቁም ነበር፡፡ ልብሳቸውን ለባብሰው እየተጣደፉ ሲወጡ ሚስታቸው አልጋው ላይ ሆነው አሰቡ

"ይሔን ሁሉ ዘመን ዓይቶት የማያውቀውን የእግሬን መንሻፈፍ ዛሬ እንዴት ታየው? ምናልባት ወጣት ሴት ዓይቶ ይሆን? ማን ያውቃል ...? ባላቸውን ካገቧቸው ጀምሮ ዛሬ ገና ተጠራጠሩ፡፡

ልጃቸው ስንቄ እንደ ሁልጊዜው ከመኘታዋ ተነስታ እያንጎራገረች ነበር፡፡ ለሙዚቃ ከፍተኛ ፍቅር ያላት ስንቄ በተለይ የአስቴርን አወቀን ዘፈኖች ስትዘፍን ታስደምማለች፡፡ ዛሬ ግን እናቷ ድንገት አንባረቁባት

"ወዲያ ዝም በይ! ምን በጧቱ ታንቋርሪብኛለሽ!"

ስንቄ በእናቷ ንግግር ክፉኛ ተበሳጨች፡፡ እስከዛሬ ሲያንቋርር ነበር "የኔ ልጅ ድምጿ ብቻ የወፍ ዘር የሚያረግፍ..." እያሉ ዛሬ ታዲያ ምን ነካቸው? ስታምሰለስል ድንገት ጓደኛዋ ሊበን ደወለ፡፡

ዛሬ "ሰርፕራይዝ" ሊያደርጋት ጓደኞቹን አዘጋጅቶ እየጠበቃት ነው፡፡ እንድታገባው ሊጠይቃት ወስኗል ጓደኞቹ ጋር ቤቱ ቅልብጭ ያለ ፕሮግራም አዘጋችቶ ድንገት ሊነግራት የቃል ኪዳን ቀለበቱን አዘጋጅቶ በጉጉት እየጠበቃት ነው፡፡

"ሄሎ!" አለች እንደከፋት

"ሄሎ...! ምነው ድምፅሽ?" አላት እንባ ተናንቋት ስለተናገረች ድምጿ በእርግጥም ድክም ብሎ ነበር፡፡

"ድምፄ ምን ሆነ? ስትል ጠየቀችው፡፡

"ተንቋረረ ልበል?" አላት ፈገግ ብሎ፡፡ ስልኩን ጆሮው ላይ ጠረቀመችበት፡፡

ዘፋኘነትም ከዚህ በኀላ ዋጋ እንደሌለው ገባት፡፡ አርፋ የፀሀፊነት ሥራዋን ለመስራት ወሰነች፡፡ "አንቋራሪ ድምፅ " ያውም በእናቷና በምቶደው ፍቅረኛዋ የተመሰከረበት...፡፡ እስከዛሬ ሰው ፊት 'ስታንቋርር' ሁሌም ሲታዘባት በሹክሹክታ ሲቀልድባት እነንደኖረች ተሰማትና አፈረች!!

###
ኡኡኡኡኡኡኡኡኡ....ከወደውጪ ድምፅ ተሰማ...........

ክፍል ሁለት ይቀጥላል

#ካሉበት_አርባ_ክንድ_ርቆ ከቆመ በኀላ፡፡ እኔ እንደጨመርኩበት ልብ ይሏል

@jahABP ነኘ አስተያየታችሁን አድርሱኘ
19.2K views15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-27 21:35:24 AB PHOTOGRAPHY & GRAPHIC DESIGN

" #የተበላሸ_ማሞቂያ

ጨርሰው የማይሰሩ አሳሳቢ አይደሉም አይሰሩምና ብልሽት ያለባቸው ማሞቂያዎች ግን ሰውየው ሲሞክራቸው ይሰራሉ ልብሱን አውልቆ ሲገባ ያረጥባሉ፡፡ ዓይኑን መግለጥ ከመታጠቢያው መውጣት በማይችልበት ሰዓት ሙቀታቸቅን መስጠት ያቆማሉ፡፡

ሰውየው በአይኑ ሳሙና ገብቷልና ልብሱን ለመልበስ እንኳን ከውሃ ያለፈ ገላውም ሳሙና ብቻ ነውና ማሞቂያው ስለተበላሸ የፈራውን ቅዝቃዜ የፈራውን እንቅጥቅጥ በግድ ይጋፈጣል፡፡ በሙቀት ጀምሮ በቅዝቃዜ በመጨረሱ ይንቀጠቀጣል፡፡

የተበላሸ ማሞቂያ ሲገጥመን ሁል ጊዜ የወረት ያስታውሰናል በሙቀት ጀምሮ በቅዝቃዜ መጨረስ የዚህ ዓለም መገለጫ ሆኗል፡፡ በኡኡታ ሠርግ በግልግል ማሬ የሚለው ቃል እሬቴ በሚል....ይለወጣል፡፡

ጨርሰው ጨካኘ ፈጽመው ክፉ የሆኑትነ አንሞክራቸውም አንቀርባቸውም ብንቀርባቸውም ተጠንቅቀን ነውና አይጎዱንም፡፡

እነደተበላሸው ማሞቂያ በሙቀት ጀምረው በቅዝቃዜ የሚጨርሱ አረጋግተው ቀጥል የሚያንቀጠቅጡን ስሜት አልባ አድርገው ቀጥለው የሚያሳምሙ አስደስተው ቀጥሎ እትትትትት.....የሚያሰኙ ብዙዎች ናቸው፡፡


ፍፁም እስክንራቆት ያባበሉን ሌላ ማየት እስከማንችል ያወሩን በማይዘልቀው ሙቀታቸው ያታለሉን የትም መሄድ እንደማንችል ሲረዱ ይለዋወጣሉ፡፡ በረዶአቸውን ማዝነብ ይጀምራሉ፡፡

ስለተለወጡብን ሰዎች ከማሰብ ስለተለወጥንባቸው ማሰብ የተሻለ ነው፡፡ በሞቀው ሰላምታ ጀምረን ያኮረፍናቸው ፍፁም ሚስጥራቸውን ከሰማን በኀላ ገሸሽ ያልናቸው ሌላ ማየት ሲያቅታቸው አውረን የተለየናቸው አውላላ ሜዳ ላይ መሪ ፈልገው ሲንከራተቱ የሳቅንባቸው ሊኖሩ ይችላሉ፡፡

ምናልባት ዛሬ ሰው የማይወጣልን ሰው ገፍተን ሊሆን ይችላል፡፡ የዛሬውን የሚመጥነን ቅጣት ነውና በሚደርስብን ልንደሰት ይገባል፡፡

ትላንትን መልሰን መኖር ቢያቅተን በንሰሐ ማደስ እንችላለን፡፡ እነዚያንም ሰዎች መካስ እንችላለን፡፡
የንሰሐ የይቅርታ ዘመን ዕድል ነውና ሊያልፈን አይገባም፡፡

#ዛሬም_ከተለዋዋጭ_ማንነት_እንጠበቅ፡፡

#ሰው_እንጂ_አካባቢውን_የምንመስል_እስስት_አይደለንም፡፡

ጌታ ሆይ እውነተኛ ፍቅርን እንዳንገፋ እባክህን እርዳን፡፡ "

@jahABP ነኘ አስተያየታችሁን አድርሱኘ
መልካም ምሽት

@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
19.2K views18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-19 23:53:42 AB PHOTOGRAPHY & GRAPHIC DESIGN

" #አትድገሙ

ክፉ ነገር በማሰብ ይጀምራል፡፡ በማድረግ ይደመደማል፡፡ ማሰብ ለክፋት ፅንሰቱ ማድረግ ልደቱ ነው፡፡ ክፉ ነገር በማድረግ እየተገለጠ ይመጣል፡፡ ክፉ ነገርን የጦር ኀይል የፍርድ ጽናት የቅጣት ብዛት አያስቆመውም፡፡ክፉ ማሰብ ባለቤቱን ይበክላል ክፉ መናገር የጎረቤትን ሰላም ያናጋል አዕምሮን ያቆሽሻል ክፉ ማድረግ ማድረግ ማህበረሰብን ይጎዳል ያፈናቅላል፡፡ ክፉን መድገም ያደነድናል፡፡

#ያለመውደቅን_ያህል_ወድቆ_መነሳት_ክብር_ነው፡፡

የማይወድቅ የለም መልዐክ ካልሆነ የማፀፀት የለም ሰይጣን ካልሆነ፡፡

መድገም ማስተጋባት ነው፡፡ የሌሎችን ክፋት ማወደስ ለክፋት በነፃ ማስታወቂያ መስራት ነው፡፡ ሳይከፍሉን በቅዱስ አደባባይ ርኩስ ማስታወቂያ መስራት ነው፡፡ አንድ ጊዜ ክፉ ነገርን ከሚፈፅሙለት ይልቅ ደግመው በሚያወሩለት ሰይጣን ይደሰታል፡፡ ኃጢያት በተግባር ከሚፈፅሙ በምኞትና በትዝታ የሚጨልጡ ይበዙለታል፡፡

ሰው ነንና ክፉ ነገር እናስብ ይሆናል አለመናገር መልካም ነው፡፡ ሰው ነንና ተናግረን ይሆናል አለማድረግ ግን የተሻለ ነው ሰው ነንና አድርገን ይሆናል አለመድገም ግን መልካም ነው፡፡ መድገም መስራት ብቻ ሳይሆን ማስተዋወቅም ነው፡፡ ነገሩን ደግሞ ማውራት አይገባም፡፡

አዝረከርካለው ያልነውን ጉዳይ አንሰራፍተነው ሊሆን ይችላል፡፡ መድገም ብዙ ደቀመዝሙርትን ያፈራል፡፡ "ክፉ ነገርን አትናገሩ ደግማችሁም አታውሩ" ለምን ስንል፡- ያደረገ ካለ ይደፍራል ያሰበ ካለይፈፅማል የጀመረ ካለ ብቻዬን አይደለሁም ይላል የፈራ ካለ ልብ ያገኛል አደራረጉ የጠፋው ካለ ስልቱን ያገኛል፡፡

ክፋ ነገርን እግዚአብሔር ይገስፅህ በማለት መቅበር ያስፈልጋል፡፡
ዝርዝር ማውራት ለሴጣን ስፖንሰር መሆን ነው፡፡ ይህን ለመገንዘብ መንፈሳዊ ሰው ብቻ ሳይሆን ጨዋ አስተዳደግም በቂ ነው፡፡

#እጅግ_ግልፅነት_እብደት_ነው፡፡

ሰይጣን ዋንኛ ስራ ጆሮን ማስለመድ ነው፡፡ ጆሮን ማስለመድ የፖለቲካ ትልቅ ስልት ነው፡፡ የክፉዎች ትልቅ መንገድ ነው፡፡ ጆሮ ከለመደው አፈፃፀሙ ቀላል ነው፡፡ የምንናገረውን ሰዎች ይለማመዱታል ማስደንበርን ነው የምንፈራው ከዛም የተለየ ነገር አለ፡፡

ብዙ ክፉ ድርጊቶች ሲወሩ ይብሳሉ፡፡
ዝርዝር የሚወራው የእግዚአብሔር ፍቅር ነው፡፡ ዛሬ ግን አጋንትን እያስለፈለፉ ትምህርት እንሰጣለን እየተባለ ነው፡፡ የሐሰት አባት ከተባለው የእውነት መረጃ እየተፈለገ ነው፡፡ ስብከት ሲያልቅብን ወደዚህ መግባታችን ያሳዝናል፡፡"

"መጥፎን ነገር እንደምንጠላ የሚያረጋግጥልን ስራችን ብቻ ነው" እና ከክፉ እንራቅ መልካምነትን እንዝራ እላለሁ

@jahABP ነኘ አሰተያየታችሁን አድርሱኘ መልካም ጊዜ ተመኘሁ፡፡


@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
17.7K views20:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-09 22:10:52 AB PHOTOGRAPHY & GRAPHIC DESIGN

#ስውር_አይን

የመርሐ ግብሩ መሪ እኒያን ሊቅ ሲያስተዋውቅ "በአይነ ሥውር አቅማቸው ይህን ሁሉ ትምህርት ተምረው ይህም ያህል ደቀ መዛሙርት አፍርተው.....እያለ በእርሱ አመለካከት ማድነቅ ያለውን ነገር አወረደው፡፡

ሊቁ ግን ሲነሱ:- "ይህ ወንድሜ ያለውን ሰምቻለሁ ፡፡ በዓይነ ስውር አቅማቸው.......ብሏል፡፡ ወንድሜ #አምፑል ተቃጠለ ማለት መብራት ሄደ ማለት አይደለም ዓይነ ስውር ማለት የሳሎኑን መብራት አጥፍቶ የጓዳውን አብርቶ የተቀመጠ ነው ብለዋል፡፡...."፡፡በእርግጥም ሊቅ ናቸው፡፡

የሚንከባለል ዓይን ያለው አብዛኛው ሰው የጓዳውን አጥፍቶ የሳሎኑን አብርቶ የተቀመጠ ነው፡፡

የላይኛው ዓይን አምፑል ነው፡፡ አምፑል የሚሰራው በራሱ አይደለም ዓይንም ያለ ልብ ከኃይል ምንጩ እንደተለያየ አምፑል ነው፡፡ ማስተዋል ከሌለ የላይኛው ዓይን ከጌጥነት አያልፍም፡፡ እግዚአብሔር የሠራውን ለማድነቅ የወደቁ ሰዎችን ለማንሳት ወዳጆችን በፍቅር ለመመልከት.....የሚያገለግለው የውስጥ ዓይን እንጂ የውጭ አይን አይደለም፡፡

ጌታችን ወደዚህ ዓለም የመጣው እያዩ የማያዩትን እናያለን እያሉ የማያስተውሉትን ሳያዩ እንመራለን የሚሉትን ለመውቀስ ነው፡፡ እግዚአብሔር የሚታየው እውነት የሚገኘው በውስጥ ዓይን እንጂ በላይ ዓይን አይደለም፡፡


ወደ ተመስጦ ስንገባ ዓይናችንን እንጨፍናለን፡፡ የላይኛው ዓይን ባካና ያደርጋል፡፡ ለኅሊና የቤት ስራ እየያዘ ይመጣል፡፡

የቀደሙት አባቶች የቋንቋ እውቀታቸው ይደንቃል፡፡ ሲሰይሙ "ዓይነ ስውር" ብለዋል፡፡ ሥውር አይን ያለው ማለት ነው፡፡ አንዱ የግልፅ አንዱ የውስጥ ዓይን ተደርጎለታል ማለት ነው፡፡ የላይኛው ዓይን ማጣት ሳይከለክላቸው ብዙ ታላላቅ ሥራ የሠሩ ሊቃውንትን ይቺህ ዓለም አስተናግዳለች፡፡

የላይኛውን ብርሃን ማጣት ኃጢያት አይደለም፡፡ በውስጥ ጨለማ ተዝናትቶ መቀመጥ ግን ሀጢያት ነው፡፡ የላይኛው በተዓምራት ይወገዳል የውስጥ ጨለማ ግን ያለትምህርትና እምነት አይወገድም፡፡

ዓይን ተመልሳ እራሷን አይታ አታውቅም፡፡ ሌሎችን ታያለች ራሷን ግን አታይም፡፡ ሌሎች ያጎደሉት ትገመግማለች የራሷን ግን አታውቀውም፡፡ የላኘኛዋ ዓይን ለሌሎች የሆነውን እያየች #ቅንዓትን የሌሎችን ሰላም እያየች #ምቀኘነት የሌሎችን መውደቅ እያየች #ፍርድን የሌሎች ርኩሰት እያየች #ውድቀትን ይዛ ትመጣለች፡፡

#በላይኛው_አይን_ብቻ_ማልቀስ_አይቻልም

በመንገድ ላይ እናቶቻችን "እያዩኘ ሰላም ሳችሉኘ አለፉ" ስንላቸው የተለመደ መልስ ይሰጣሉ፡- "አይ ልጄ የሚያየው ልብ እንጂ ዓይን መሰለህ?" ይላሉ፡፡

ትልቁ ብርሃን ያለው ልብ ላይ ነው፡፡ የልብ ብርሃን ከጨለመ የላይኛው አይቶ #መርገጥ አይቶ #መጠንቀቅ አይቶ #ማዘን አይችልም፡፡

ሥውር ዓይን ያስፈልጋል፡፡ ሥውር ዓይን ሲኖረን:-

✿ ያለንን እናውቃለን፡፡ ስለጎደለን የምንጨነቀው ያለንን በትክክል ስላላወቅን ነው፡፡

✿እግዚአብሔር ዛሬም በሥራ ላይ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ስለዚህ ተስፋችን ይታደሳል፡፡

✿ በአሁኑ ሁኔታ ሕይወትን አንመዝን፡፡ አሁን ያለው ደግም ይሁን ክፉ እርሱ መጨረሻችን አይደለም፡፡ #የሚመጣው_የሚልቀው_ነው፡፡

✿ ለጎዱን ሳይቀር በችግራቸው እንገኛለን፡፡

✿ በተገፉት ላይ አንጨክንም፡፡ ዓለም ተራ መሆኑ ይገባናል፡፡

✿ ለሌሎች ማካፈል አንረሳም፡፡ ሌሎች እኛ ጋ ድርሻ አላቸው፡፡

✿ አንደበታችንን እንገዛለን፡፡ መልካሙን ቀን ለማየት አንደበትን መቆጣጠር ያስፈልጋልና፡፡

እርሱ ሥውር አይን ይፍጠርልን


@jahABP ነኘ ሳነብ ካገኘሁት መልካም ሰዎችን ይገልፃል ብዬ አሰብኩና እንዲህ አቀረብኩት፡፡

ክብር ይስጥልኘ

አስተያየታችሁን አድርሱኘ፡፡

@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
19.3K views19:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ