Get Mystery Box with random crypto!

ረከብኪ ቲዩብ | Rekebki Tube

የቴሌግራም ቻናል አርማ rekebkitube — ረከብኪ ቲዩብ | Rekebki Tube
የቴሌግራም ቻናል አርማ rekebkitube — ረከብኪ ቲዩብ | Rekebki Tube
የሰርጥ አድራሻ: @rekebkitube
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 436
የሰርጥ መግለጫ

"ተዘከሩ መኳንንቲክሙ ዘነገሩክሙ ቃለ እግዚአብሔር። " የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ።ዕብ ፲፫፡፯
https://youtube.com/@rekebkitube
ረከብኪ ቲዩብ
https://t.me/ VJhnnXdC4rsxYjU0

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-01-15 08:11:30

6 views05:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 13:48:09

42 views10:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 19:13:01 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ወደ ክርስትናው ከተመለሰ በኋላ ገዳም ሲሔድ ይዞት የሔደው መጽሐፍ ቅዱስን ነበር፡፡ ሌሎችም አባቶች ለመጽሐፍ ቅዱስ ልዩ ፍቅር ነበራቸው፡፡ ዛሬ እንዲህ ስማቸው ገንኖ እንዲሰማ ያደረጋቸው መፍቀሪያነ መጻሕፍት ስለ ነበሩ ነው፡፡ የሕይወታቸው ምሥጢር መጽሐፍ ቅዱስ ነበር፡፡ የሚጸልዩት መጽሐፍ ቅዱስን ነበር፤ ያውም በቃላቸው አጥንተዉት! በተለይ መዝሙረ ዳዊት እጅግ የተወደደ የጸሎት መጽሐፋቸው ነው፡፡
እነዚህ ቅዱሳን አባቶች ለመጻሕፍት የነበራቸው አመለካከት በእጅጉ የተለየ ነው፡፡ እንደ እነርሱ እያንዳንዱ ምእመን በሚገባው ቋንቋ መጻሕፍት ማንበብ አለበት፡፡ በሔዱበት አገር ፊደል ላለው በፊደሉ፣ ፊደል ለሌለው ደግሞ ፊደል ቀርጸው አስቀድመው ማንበብ እንዲችል ያስተምሩት የነበረውም ለዚህ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ደረጃ ያለውን ስንመለከተውም ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ ከፊደላችንና ከቋንቋችን አንጻር የአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን አስተዋጽኦ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ. ታሪክ በጻፉበት መጽሐፋቸው ላይ ቤተ ክርስቲያን ለአገር ምን እንዳበረከተች ሲገልጹ፡- “ሙሉ ትምህርት፣ ፍጹም ቋንቋ ከነፊደሉ፣ ሥነ ጽሑፍ ከነጠባዩ ከነሙያው” ያሉትም ይህን ፍንትው አድርጎ የሚያስረዳን ነው፡፡
ነገር ግን ከዚህ መረዳት እንደምንችለው ቤተ ክርስቲያን ይህን ያደረገችው የራሳችን ፊደል አለን፤ የራሳችን ቋንቋ አለን ብለን እንዲሁ እንድንኩራራ ሳይኾን እንድናነብ ነው - እንድናነብ!!!
79 views16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 19:12:01 ስለዚህ መንፈሳዊ ንባብ ማለት ራሳችንንም የሚሰሙንንም ለማዳን - አስተውሉ! ለማዳን - መጽሐፍ ቅዱስን ጨምሮ የአበው ድርሳናትን፣ ትርጓሜያትን፣ ምክሮችን፣ ገድሎችን፣ ታሪኮችን ማንበብ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ የማንበብ ግቡ እኛ ራሳችን እግዚአብሔርን ወደ መምሰል እንድናድግ ሌሎችንም ወደዚህ ምንድግና እንዲመጡ ማድረግ ነው ማለት ነው፡፡ ንባብ ብቻ ሳይኾን የማንኛውም መንፈሳዊ ግብር ዓላማም ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረትና አንድነት መፍጠር ነው፡፡
ከላይ ባነሣነው የቅዱስ ጳውሎስ ቃል እንደምንመለከተው አንድ ኦርቶዶክሳዊ ኹልጊዜ በመደበኛነት ሊያነብ እንደሚገባው ያስረዳል፡፡ ጢሞቴዎስ ጳጳስ ነው፡፡ ቢኾንም ግን ማንበብ - ያውም ኹልጊዜ - መጻሕፍትን መመልከት እንዳለበት ተመከረ! ቅዱስ ጢሞቴዎስ ከሴት አያቱና ከእናቱ ከልጅነቱ አንሥቶ ቅዱሳት መጻሕፍትን ሲያነብ ያደገ ነው (2ኛ ጢሞ.3፡14-15)፡፡ አሁንም ቅዱስ ጳውሎስ ተቀብሎ ይበቃሃል ሳይኾን “በማንበብ ተጠንቀቅ” አለው፡፡

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከጥንት አንሥቶ እስከ አሁን ድረስ ብዙ አበው ወእማት አሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያንም የምታስተምረን እነዚህን ቅዱሳን አበው ወእማት በሕይወታቸው፣ በትምህርታቸው እንድንመስላቸው እንጂ እንዲሁ እንድንጠቅሳቸው፣ ወይም ጽሑፋቸውን እንድናጠና ብቻ አይደለም፡፡ ቤተ ክርስቲያን የምታበረታታን እነርሱ ክርስቶስን እንደመሰሉት እኛም እነርሱን እንድንመስል ነው፡፡
ከእነዚህ ቅዱሳን ኹሉ የመጀመሪያውን ስፍራ የምትይዘውም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ካነሣነው ርእሰ ጉዳይ ጋር በተያያዘ እጅግ አንባቢ እንደ ነበረች ቅዱሳት መጻሕፍት ይመሰክሩልናል፡፡ የሉቃስ ወንጌል 1፡47-55 ያለውን ኃይለ ቃል ብናነብ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ዕውቀቷ እንደ ምን ጥልቅና ምጡቅ እንደ ነበረ መገንዘብ እንችላለን፡፡
ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ፣ ቅዱስ ጳውሎስ፣ በአራተኛው መ.ክ.ዘ. የነበሩ አባቶች ለምሳሌ እነ ቅዱስ ኤፍሬም፣ እነ ቅዱስ አትናቴዎስ፣ እነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሦስቱም የቀጰዶቅያ አባቶች፣ እነ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ መጻሕፍትን ዕለት ዕለት በማንበብ ተጠቃሾቹ መኾናቸውን እናስተውላለን፡፡ ከኢትዮጵያ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን፣ ቅዱስ ያሬድ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፣ መምህር ኤስድሮስ ዋነኞቹ ናቸው፡፡ እንዲያውም መምህር ኤስድሮስ እስከ ሦስት መቶ መጻሕፍት እንዳነበቡ የታወቀ ነው፡፡
እነዚህ ኹሉ ቅዱሳን ከተለያየ አከባቢ፣ ከተለያየ ባሕል፣ ከተለያየ ቤተ ሰብእ የተገኙ ቢኾኑም ቅሉ አንድ የሚያደርጋቸው ነገር ግን አለ፡፡ እንደየአገራቸው በዚያ ዘመን ይሰጥ የነበረውን ትምህርት ለምሳሌ ፍልስፍናን፣ ሥነ ከዋክብትን፣ ሒሳብን፣ ፊዚክስን፣ እና ይህን የመሳሰለውን የተማሩ ቢኾኑም መንፈሳውያን መጻሕፍትን በማንበብ ረገድ ግን አንድ ናቸው፡፡
68 views16:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 19:09:55
እስክመጣ ድረስ በማንበብ ተጠንቀቅ” (1ኛ ጢሞ.4፡13)፡፡


 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
እንደ መንደርደሪያ
ኃይለ ቃሉን የተናገረው በመንፈሳዊው ትምህርት ከሕግ መምህሩ ከገማልያል፣ በዚህ ዓለም ትምህርት ደግሞ በዘመኑ እጅግ ታዋቂ ከነበረው የተርሴስ ዩኒቨርሲቲ በእጅግ ከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀው ንዑድ ክቡር የሚኾን ጳውሎስ ነው፡፡ የተናገረው ደግሞ በመንፈስ ለወለደው ልጁ ለሊቀ ጳጳሱ ለቅዱስ ጢሞቴዎስ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለቅዱስ ጢሞቴዎስ፡- “እስክመጣ ድረስ በማንበብ ተጠንቀቅ፤ በማንበብ ተወስነህ ኑር” በማለት መንፈሳውያን መጻሕፍትን እንዲያነብ ሲመክረውም ምክንያቱን ነግሮታል፤ እንዲህ ሲል፡- “ይህን ብታደርግ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህ” (1ኛ ጢሞ.4፡16)፡፡
83 views16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-06 07:51:56

126 views04:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 19:39:21

145 views16:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 11:59:19

145 viewsedited  08:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-08 20:09:44 https://youtube.com/shorts/Uc4SQdGx-oQ?feature=share
277 viewsedited  17:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-06 16:48:37

275 views13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ