Get Mystery Box with random crypto!

መኖርን ለምን መረጥክ ? የሰው ልጅ የመሞቱን ያህል መኖሩን አይፈራውም። እውነት ሳስበው ያስገርመኛ | ራስን ማግኘት!!!

መኖርን ለምን መረጥክ ?
የሰው ልጅ የመሞቱን ያህል መኖሩን አይፈራውም። እውነት ሳስበው ያስገርመኛል። መንግስተ ሰማይ እንደሚገቡ እርግጠኛ እንደሆኑ የሚሰማቸው ሰዎች እንኩዋን ሞትን አብዝተው ይፈሩታል። መኖር እኮ እንደውም ያስፈራል። ምክንያቱም መሞታችን አንዴ እኛነታችን የሚቋረጥበት ሲሆን መኖራችን ግን ሁሌም በኛነት ጥያቄ ውስጥ ተይዘን የምንባዝንበት ነው። ትልቁ ጥያቄ ታድያ ይሄ ነው፦ ከመሞት ይልቅ መኖርህን ለምን መረጥከው? ጠዋት ከእንቅልፍክ ስትነሳ ምንድነው ያስነሳህ? ምንድነው እንድትኖር ያደረገህ ?ለምንስ መኖርክ ይሄን ያህል ዋጋ ተሰጠው? አየህ ይሄንን ነው መመለስ ያለብህ። ለምን ? ስለዚህ መኖርን መርጠህ እየኖርክ እስካለህ ድረስ የተሻለውን ምርጡን እና ትልቁን ህይወት ኑር። አለበለዚያ ግን መኖርህም መሞትህም ዋጋ የለውም። የምትኖረው ኖረህ ለማለፍ ነው ወይስ ሌሎችን ለማኗኗር ነው? አብዛኛው ሰው ኗሪ ሳይሆን አኗኗሪ ነው። የህዝብ ቁጥርን ሚጨምር ብቻ አለ። ስለዚህ ስትኖር ለምን? እድሜ ሲጨመርልህ ለምን ? አለዚያ ብዙ አበርክተው መሞት ሚፈልጉ አሉ ለነሱ ቦታ መልቀቅም ፅድቅ ነው። ስለዚህ የዘመንህ ጥያቄ ይሁን። ለምን እኖራለው ? ምን ልሰራ ? ምን ላበረክት? ምን ልሰጥ ነው የምኖረው ? ብለህ እራስህን ጠይቅ። አለበለዚያ ግን ህይወት ላንተ ትርጉም የላትም ስለዚህ ሞትን አትፍራው። ምክንያቱም ለመኖር ሚያጓጓ ነገር የለህም።

https://t.me/Lemen_Lemen