Get Mystery Box with random crypto!

Pure_Christianity

የቴሌግራም ቻናል አርማ pure_christianity — Pure_Christianity P
የቴሌግራም ቻናል አርማ pure_christianity — Pure_Christianity
የሰርጥ አድራሻ: @pure_christianity
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.47K
የሰርጥ መግለጫ

@pure_Christianity
The word of Love and Grace
Visit our YouTube channel
youtube.com/@LoveandGrace73

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-27 11:58:25 ፊቴ የቆመውን ባሕር ያኔ አሳልፎኝ ነበር ዛሬስ ደግሞ ሌላው ቢገጥመኝ በየተራ ቢሰለፍብኝ ዓይኔን ማንከራተቱን ትቼ ልምታ ከበሮዬን አንስቼ የሰልፉ ጌታ ከእኔ ጋር ነው ዛሬም ጠላቴን ሊያዋርደው (፪x)
ያሻገረኝ ጌታ ያን የትላንቱን (፫x) አሁንም ይሰራል ያን ሃይሉን ሳምን (፫x) በእውነት ላመልከው ከልቤ ስነሳ (፫x) ሁሉን አሳመረው የይሁዳ አንበሳ (፫x)
አዝ ከእንግዲህማ ወስኗል ልቤ ከእንግዲህማ ምንም ላይፈራ ከእንግዲህማ ጌታ ኢየሱስ እያለ ከእኔ ጋራ ከእንግዲህማ ሌላውን አልሰማም ከእንግዲህማ ከንቱ ነውና ከእንግዲህማ እዘምራለው ከልቤ ለእርሱ ምሥጋና ከልቤ ለእርሱ ምሥጋና ከልቤ ለእርሱ ምሥጋና ኢየሱስ ጌታ ነውና ኢየሱስ ጌታ ነውና (፪x)
ፊቴ የቆመውን ባሕር ያኔ አሳልፎኝ ነበር ዛሬስ ደግሞ ሌላው ቢገጥመኝ በየተራ ቢሰለፍብኝ ዓይኔን ማንከራተቱን ትቼ ልምታ ከበሮዬን አንስቼ የሰልፉ ጌታ ከእኔ ጋር ነው ዛሬም ጠላቴን ሊያዋርደው
የቆመው ተራራ ፊቴ ተከምሮ (፪x) አይመስልም ሚታለፍ እንደሚከብድ ሆኖ (፪x) ለእኔ እንጂ ለአምላኬ መቼ አስቸገረው (፪x) በተአምራቱ ሁሉን ሜዳ አደረገው (፪x) አዝ ከእንግዲህማ ወስኗል ልቤ ከእንግዲህማ ምንም ላይፈራ ከእንግዲህማ ጌታ ኢየሱስ እያለ ከእኔ ጋራ ከእንግዲህማ ሌላውን አልሰማም ከእንግዲህማ ከንቱ ነውና ከእንግዲህማ እዘምራለው ከልቤ ለእርሱ ምሥጋና ከልቤ ለእርሱ ምሥጋና ከልቤ ለእርሱ ምሥጋና ኢየሱስ ጌታ ነውና ኢየሱስ ጌታ ነውና (፬x)

@pure_Christianity
173 viewsedited  08:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:19:06
@pure_Christianity
269 viewsedited  17:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:17:35 እምነት ማለት በአካል አለም ውስጥ ያለ ሠው በመንፈሳዊ አለም ላይ ያለውን እውነታ የሚመለከትበት አይኑ ነው።
@Pure_Christianity
246 views17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 18:15:54 የእግዚአብሔር የዘላለም እቅዱ ራሱን በሠዎች በኩል ለፍጥረት መግለጥ ነው። በሠዎች ውስጥ መኖርን ፈቀደ። ለዚህም ፈቃድ ማረጋገጫ የሚሆን ኪዳን በራሱ ደም አደረገልን። ስለዚህ አንለያይም ከከበረው ከክርስቶስ ደም የተነሳ አንድ ነን። መፅሀፍ ቅዱስ ማለት ይሄንን የዘላለም አላማ መዝግቦ የያዘ ውልና ሰነዳችን ነው።
@Pure_Christianity
2.2K viewsedited  15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 20:23:52 ስራ የሌለው እምነት የሞተ ነው። ይህ ማለት ታዲያ ደህንነትን ለማግኘት መስራት አለብህ ማለት ነው እንዴ? ያዕቆብ በፍፁም ስለ ስራ እያወራ አይደለም ይልቁኑ ስለሚሠራ እምነት እንጂ። ያዕቆብ ለማስተላለፍ የፈለገው መልዕክት ይህን ይመስላል፦ የሚያድንህ እውነተኛ እምነት ነው። እውነተኛ እምነት ማለት በስራ የሚገለጥ እምነት ነው። ለምሳሌ ፀሎት ይጠቅማል እያልክ የማትፀልይ ከሆነ ፀሎት እንደሚጠቅም አታምንም ማለት ነው ብታምን ኖሮ ትፀልይ ነበረ። አንደበትህ ይናገራል ልብህ ግን አላመነም። ስለዚህ ማድረግ ያለብህ ነገር መስራት ሳይሆን ማመን ነው ። ያዕቆብ እያለ ያለው አላመናችሁም እመኑ ነው። ያዕቆብ በስራ በኩል ለሠዎቹ ለማሳየት የፈለገው ስራን ሳይሆን እምነትን ነው። ምክንያቱም ኢየሱስ ከበሽታ እንደሚፈውስህ ታምናለህ ነገር ግን ሠዎች ሲታመሙ አትፀልይም ስለዚህ አታምንም ማለት ነው። ያዕቆብ የስራ ሳይሆን የእምነት መምህር ነው። ያዕቆብ እመን እያለህ ነው። የሚያድንህ እምነት ስለሆነ በትክክል በክርስቶስ ስራ እመን። ከዛ ይሄ እምነትህ ያራምድሀል አለቀ። ምክንያቱም አስቀድሞም ቢሆን አንተ መስራት ብትችል ማመን አይጠበቅብህም ነበረና። የተፈለገው ስራ አንተ የምትሠራው ሣይሆን ክርስቶስ ላይ ያለህ እምነትህ የሚሠራውን ስራ ነው። ፃዲቅ በእምነት በሕይወት ይኖራል።
@Pure_Christianity
@Pure_Christianity
3.4K views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 09:01:06 Watch "ፍረጃ || አዲስ አማርኛ መንፈሳዊ ትረካ @pure Christianity" on YouTube








2.5K viewsedited  06:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 19:29:02 መንፈስ ቅዱስ በእኔ ውስጥ አለ ብለህ የምታምን ሆይ ታዲያ ምነው ሀጢያት እንደሌለብህና ፍፁም ንፁህ መሆንህን ማመን ከበደህ? መይንስ መንፈስ ቅዱስ ከሀጢያት ጋር የሚስማማ ነው? አንተ በክርስቶስ ስራ ምክንያት በደሙ ፈፅሞ ንፁህና ቅዱስ ባትሆን አስቀድሞም መንፈስ ቅዱስ በአንተ ውስጥ ባላደረ ነበር። መንፈስ ቅዱስ ወደ አንተ የመጣው የክርስቶስ የመስቀል ላይ ስራ ስለተጠናቀቀ ነው። ስለዚህ አንተ ንፁህና ቅዱስ መሆንህን መንፈስ ቅዱስ አንተ ውስጥ በማደር አረጋግጦልሀልና አንተም ፍፁም የሆነ ንፅህናና ቅድስና እንዳለህ አምነህ ተቀበል። አደራህን ከየት አምጥቼው ነው እንዳትለኝ የክርስቶስ ፍፁም ንፅህናን መቀበልህንና የአንተን ሀጢያት እርሱ መውሰዱን ዘንግተህ። አንተ ንፁህና ፃዲቅ ነህ። ይህ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስን በማመንህ ብቻ ነው።
@Pure_Christianity
@Pure_Christianity
3.2K viewsedited  16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 14:10:38 አሃ ፡ አሃሃ ፡ ያኔ ፡ እንደወደደኝ
አሃ ፡ አሃሃ ፡ ዛሬም ፡ ይወደኛል
አሃ ፡ አሃሃ ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ ፍቅሩ
አሃ ፡ አሃሃ ፡ መች ፡ ቀንሶ ፡ ያውቃል

አሃሃ ፡ እርሱ ፡ ያው ፡ ነው ፡ አልተለዋወጠም
አሃሃ ፡ ምህረቱ ፡ ዛሬም ፡ አልጐደለም
አሃሃ ፡ እርሱ ፡ ያው ፡ ነው ፡ አልተቀያየረም
አሃሃ ፡ ቸርነቱ ፡ ዛሬም ፡ አልጐደለም

ያኔ ፡ በመስቀል ፡ ላይ ፡ ሆኖ ፡ ኤሎሂ ፡ ያለላት
ከሲዖል ፡ እንድትድን ፡ ወዶ ፡ የተሟገተላት
ሞቶ ፡ እስከሚቀበር ፡ ድረስ ፡ የወደዳት ፡ ነፍሴ
ትገዛለታለች ፡ ዛሬም ፡ እያለች ፡ ንጉሤ

ወዶኛልና ፡ አዳነኝ
እያለች ፡ ቅኔ ፡ ስትቀኝ
ላልተለወጠው ፡ ማንነትህ
ምሥጋናም ፡ አላት ፡ ለምህረትህ (፪x)

አዝ፦ አሃ ፡ አሃሃ ፡ ያኔ ፡ እንደወደደኝ
አሃ ፡ አሃሃ ፡ ዛሬም ፡ ይወደኛል
አሃ ፡ አሃሃ ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ ፍቅሩ
አሃ ፡ አሃሃ ፡ መች ፡ ቀንሶ ፡ ያውቃል

አሃሃ ፡ እርሱ ፡ ያው ፡ ነው ፡ አልተለዋወጠም
አሃሃ ፡ ምህረቱ ፡ ዛሬም ፡ አልጐደለም
አሃሃ ፡ እርሱ ፡ ያው ፡ ነው ፡ አልተቀያየረም
አሃሃ ፡ ቸርነቱ ፡ ዛሬም ፡ አልጐደለም

በሕይወቴ ፡ ውጣ ፡ ውረድ ፡ ባልፍም ፡ በመከራ
እርሱ ፡ ፈፅሞ ፡ አልተወኝም ፡ አለ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ
ዓመት ፡ ዘመን ፡ ቢለዋወጥ ፡ ቀንም ፡ በቀን ፡ ላይ
እንከን ፡ አላየሁበትም ፡ ውዴም ፡ ፍቅሩ ፡ ላይ

በምህረቱ ፡ ባለጠጋ
ሆኖ ፡ አየሁ ፡ ወደ ፡ እርሱ ፡ ስጠጋ
አይጨምርም ፡ አይቀንስ ፡ ፍቅሩ
እርሱ ፡ ያው ፡ ነው ፡ በዘመኑ (፪x)

@pure_Christianity
561 viewsedited  11:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 21:26:10 ዕብራውያን 9 (13-14)
የውጭ አካላቸው ይነጻ ዘንድ በረከሱ ሰዎች ላይ የሚረጨው የፍየሎችና የኮርማዎች ደም እንዲሁም የፍየሎችና የጊደር ዐመድ የሚቀድሳቸው ከሆነ፣በዘላለም መንፈስ አማካይነት ራሱን ነውር አልባ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ያቀረበው የክርስቶስ ደም ሕያው እግዚአብሔርን እንድናመልክ ኅሊናችንን ከምውት ሥራ እንዴት ይበልጥ ያነጻ ይሆን! ሀሌሉያ!

ክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ያፈሰሰው ደም ህሊናህን ፈፅሞ ሀጢያተኛ ነኝ ከሚል አስተሳሰብ ማንፃት ካልቻለ ቀራኒዮ መስቀል ላይ የቀረበው መስዋዕት በብሉይ ኪዳን ይቀርቡ ከነበሩ ከእንስሳት መስዋዕቶች የተለየ ዋጋ አልሠጠኸውም።

ዕብራውያን 9 (24-28)
ክርስቶስ የእውነተኛዪቱ ድንኳን ምሳሌ ወደ ሆነችውና በሰው እጅ ወደ ተሠራችው መቅደስ አልገባም፤ ነገር ግን አሁን ስለ እኛ በእግዚአብሔር ፊት ለመታየት፣ ወደ እርሷ ወደ ሰማይ ገባ።ሊቀ ካህናት የራሱ ያልሆነውን ደም ይዞ በየዓመቱ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን እንደሚገባ፣ #ክርስቶስ #ራሱን #ብዙ_ጊዜ_መሥዋዕት_ለማድረግ_ወደ_ሰማይ_አልገባም። እንዲህ ቢሆን ኖሮ፣ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ክርስቶስ ብዙ ጊዜ መከራን መቀበል ባስፈለገው ነበር። አሁን ግን በዘመናት መጨረሻ ራሱን መሥዋዕት በማድረግ #ኀጢአትን #ለማስወገድ #ለአንዴና #ለመጨረሻ #ጊዜ #ተገልጦአል።ሰው አንድ ጊዜ ሊሞት ከዚያም በኋላ በፍርድ ፊት ሊቆም ተወስኖበታል። #ክርስቶስ_የብዙ_ሰዎችን_ኀጢአት_ለመሸከም፣ እንዲሁ አንድ ጊዜ መሥዋዕት ሆኖአል፤ ሁለተኛ ጊዜም ይገለጣል፤ ይህም ለሚጠባበቁት ድነትን ለማምጣት #እንጂ #ኀጢአትን #ለመሸከም #አይደለም።
አሜን
ኢየሱስ መስቀል ላይ በመሞቱ የትናንት የዛሬና የነገ ሀጢያትህን አስወግዶታል። ክርስቶስን እያመንክ አሁንም ሀጢያተኛ እንደሆንክ የምታስብ ከሆነ ክርስቶስ ከእንግዲህ ወዲህ ስለሀጢያ መስዋት ሆኖ ስለማይቀርብ ታዲያ እንዴት ይሆን ከሀጢያትህ የምትድነው? ይሄንን እውነት አጥብቀህ ያዘው። ክርስቶስ ኢየሱስ ሀጢያትህን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አስወግዶታል።
@Pure_Christianity
@Pure_Christianity
2.3K viewsedited  18:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 07:23:54 ስትደክም የሚያዝንልህና የሚሳሳልህ ፀጋና ምህረትን እየሠጠ የሚደግፍህ አሸናፊ ሆነህ እንድትኖር የሚችለውን ሁሉ የሚያደርግ አባትህ እንጂ። ስትሳሳት ሊቀጣህ የተዘጋጀ ምህረት የማያውቅ በስህተትህ ሊራራልህ የማይችል ሁልጊዜ አንተን በመውቀስ ብቻ የሚኖር አባት የለህም!! ሁልጊዜም ልጄ አንተ ብርቱ ነህ ይልሀል። እኔ የሞትኩልህ አንተ በህይወት እንድትኖር ነው። የኔ አላማ አንተን ማዳን ነው እንጂ መግደል አይደለም። ሀጢያት አንተን ስለሚጎዳህ ልትሸሸው ይገባሀል በዚህ ጊዜ ደግሞ እኔ ያንተ ረዳት ነኝ። ከሀጢያት ጋር ተስማምተህ እንዳትኖር ምክንያቱም ያንተ ማንነት ፅድቅ እንጂ ሀጢያት አይደለም። አንተ የተፈጠርከው ለፅድቅ ነው። ስለዚህ እኔ ለ አንተ ጋሻህ ነኝ በዚህም ምክንያት አንተ አሸናፊ ነህ። በፍፁም ወደኔ ከመምጣት ተስፋ አትቁረጥ አንተን ማዳን የምችለው እኔ ብቻ ነኝ። የአምላክህ የልብ ንግግር ይሄን ይመስላል...አንተ የተወደድክ ነህ!
@Pure_Christianity
@Pure_Christianity
3.6K views04:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ