#አባቴ ያ’ውና ፡ #ይታይሀል_ጀርባው ፡ እንደ አክርማ ስንጥቅ - የተከፋፈለ እንደ ባድማ መሬት - ላዩ የቆሰለ ጠኔ እንደመታው - አጥንቱ ገጠጠ የገላው ቆዳ ተራግፎ - ዕዡ ፈጠጠ የተተለተለ የስጋ - ርጋፊ ይታይሀል ፊቱ - ያረፈበት ጥፊ ፡’ የቆመበት ስፍራ - በደሙ ጨቅይቶ በልብሱ ዕጣ ላይ - ቁማራቸው ደርቶ የስድቡ ብዛት - ወርደትና ንቀት እኔን ለመፈለግ - ያደረገው ትጋት ፍቅሩን ነው ’ሚተርክ - የጀርባው ግርፋት ሁሉን የሚችለው - ያ’ውል የኔ አባታ ፡ በቃሉ ያጽናት - ምድርም ስትርቀው በመውደቅ መነሳት - ውርደት ስትንቀው ፡ #አባቴ ያ’ውና ፍቅሩ እየበረታ - ምህረቱን ያጸና መከራዬን ታግሎ - በመስቀል ላይ ሊሞት ሆሳህና ብዬ - ትናንት የሸኘሁት ቀራኒዮ ሳልደርስ - ከረቅት ያየሁት መከራውን ስገጥም ውርደቱንም ሳዜም ጭንቀቱን ስተርክ ጩኽቱንም ስሰብክ ልቤ ሳይንበረከክ ስለፍቅሩ ምለሽ ከዓለም ጋራ ስሸሽ በውርደቱ ካባ - እኔ ከበርኩበት ስራውን ስናገር - ዝና አተረፍኩበት በመስቀሉ መንገድ - ለዓለም ገነንኩበት ፡ ፍቅር ባዘለ ልብ - በዛለ ትከሻው የሞቱ ፍጻሜ - እኔ ፡ ነኝ መድረሻው ፡ ፀባዖት 5.1K views🅢🅞🅛 🅺🅸 Tsebaot, edited 11:56