ሰኞ ነሐሴ ፲፮ ፳፻፲፬ ዓ.ም ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ መልክሽ ፥ ከመልኮች ይልቃል አቅጣጫ ነው እንጂ ውበት እንዳልሆነ ፥ አሳምሮ ያውቃል የጠፋበትን ቦታ እንደሚጠቁም ካርታ ግራ ሲገባኝ አካሄዴ ሲፋለስብኝ መንገዴ መልክሽን ፥ አምጡ ስል ግልፅ ነው ፥ የዕድሌ ምስል ወደፍቅር መንገድ ወደናፍቆት መንገድ ወደራስሽ መንገድ ፥ ወደራሴ መውደድ። መንገዴን ፥ መልክሽ መራኝ መች እመለሳለሁ ፥ ሞት እንኳን ቢጠራኝ አልቆጥርም እርምጃ በአንቺ የሄድኩትንም ፥ አላውቀውም እንጃ መንገድን ፍለጋ ፥ የሚኳትን ከንቱ አላደረግሽኝም እቱ ቆሜያለሁ ከአውደምህረቱ ደርሻለሁ ፥ ከህይወት ሰገነት ወደው የሄዱት መንገድ ፥ በምን ያንሳል ከገነት። ┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈ ኤልያስ ሽታኹን ╰══•••┈ ርእስ የለውም ┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈ ፳፻፲፫ ዓ.ም ለመቀላቀል @poemandquote አስተያየት @poemandquotebot ┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓ ❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘ ┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ 814 viewsመከበር, 03:00