Get Mystery Box with random crypto!

ምስባከ ጳውሎስ (Paul's Pulpit)

የቴሌግራም ቻናል አርማ paulosfekadu — ምስባከ ጳውሎስ (Paul's Pulpit)
የቴሌግራም ቻናል አርማ paulosfekadu — ምስባከ ጳውሎስ (Paul's Pulpit)
የሰርጥ አድራሻ: @paulosfekadu
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.79K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2022-11-25 17:19:25 የሙሾ ያለህ!

“የማረኩን በዚያ [በባቢሎን] የዝማሬን ቃል ፈለጉብን፤ የወሰዱንም፦ የጽዮንን ዝማሬ ዘምሩልን አሉን። የእግዚአብሔርን ዝማሬ በባዕድ ምድር እንዴት እንዘምራለን?” (መዝ. 137፥3-4)

ይህን ክፍል ሳነብ ብዙውን ጊዜ ጥያቄ ይፈጠርብኛል። የእግዚአብሔርን መዝሙር በባዕድ ምድር መዘመር ምን ክፋት አለው? መዝሙር የሚዘመረው በእስራኤል ምድር ብቻ ነውን? በባዕድ ምድር አይዘመርም? ነቢዩ ዳንኤል በባዕድ ምድር ይጸልይ አልነበር? በምርኮ ምድር ያሉት እስራኤላውያን ስለ ባቢሎን ሰላም እንዲጸልዩ ተነግሯቸው አልነበር? ታዲያ ምርኮቹ እስራኤላውያን የጽዮንን መዝሙር እንዲዘምሩ ባቢሎናውያኑ ቢጠይቁ ምን ክፋት አለው?

አሁን እንደ ተረዳሁት ከሆነ ባቢሎናውያኑ ምን ዐይነት መዝሙር እንዲዘመር ነው የጠየቁት? የሚለውን ከተረዳን የእስራኤላውያኑን እምቢታና ሐዘን ምክንያት ለመረዳት በተሻለ ቦታ ላይ እንሆናለን። እስቲ በሌሎች ትርጉሞች እንመልከተው (የዕብራይስጡን ሐሳብ በደንብ ይገልጣሉና)፤

“የማረኩንና ሥቃይ የሚያሳዩን ሰዎች በመዘመር እንድናስደስታቸው ‘ከጽዮን መዝሙሮች አንዱን ለእኛ ዘምሩልን’ አሉን” (አዲስ ትርጉም)።

“የማረኩን በዚያ እንድንዘምርላቸው ጠየቁን፤ የሚያሠቃዩን የደስታ ዜማ ፈለጉብን፤ ደግሞም፣ ‘ከጽዮን መዝሙሮች አንዱን ዘምሩልን’ አሉን” (አመት)።

“የሚያስጨንቁን ማራኪዎቻችን ግን፣ ‘እስቲ ከጽዮን ዝማሬዎች አንዱን አሰሙን’ እያሉ የደስታ ዝማሬ እንድንዘምርላቸው አጥብቀው ወተወቱን” (ሕያው ቃል)።

በእነዚህ ትርጉሞች፣ “እንድናስደስታቸው፤ የደስታ ዜማ፤ የደስታ ዝማሬ” ከሚሉት አገላለገጦች እንደምናስተውለው ባቢሎናውያኑ ከተማራኪዎቻቸው የፈለጉት መዝሙር የደስታ መዝሙር ነው። ማራኪዎቹና አስጨናቂዎቹ ባቢሎናውያን ተማራኪዎቻቸው የደስታ መዝሙር እንዲዘምሩላቸው ነበር የፈለጉት። ይህ ደግሞ ሰው የሞተበት ሐዘንተኛ የሰርግና የድል መዝሙር እንዲዘምር ጥያቄ ከማቅረብ አይተናነስም። ባቢሎናውያኑ የእስራኤላውያኑ ሐዘን ምክንያት ናቸው፤ ነገር ግን ሐዘንተኞቹ የደስታ መዝሙር እንዲዘምሩላቸው ይፈልጋሉ። ምን ጉዶች ናቸው!?

የእግዚአብሔር ሰዎች ሐዘን ውስጥ ሆነው “አፌን ሣቅ ሞልቶታል” በማለት እንዲዘምሩ የሚጠብቁ ሰዎች ዛሬም በዙሪያችን ሊኖሩ ይችላሉ። መጽሐፈ ምሳሌ 25፥20 ለዚህ የሚሆን መልእክት አለው፤ “ለሚያዝን ልብ ዝማሬ የሚዘምር፣ ለብርድ ቀን መጎናጸፊያውን እንደሚያስወግድ፣ በቁስልም ላይ እንደ መጻጻ እንዲሁ ነው።" አዲሱ መደበኛ ትርጉም እንዲህ ይለዋል፤ “ላዘነ ልብ የሚዘምር፣ በብርድ ቀን ልብሱን እንደሚያወልቅ፣ ወይም በሶዳ ላይ እንደ ተጨመረ ሆምጣጤ ነው።" እናም ላዘነ ሰው የደስታ መዝሙር መዘመር በብርድ ሰዓት ልብስን እንደ ማውለቅ ነው። የደስታ መዝሙር ለሐዘን ወቅት አይሆንምና!

ታዲያ በእንዲህ ዐይነት ወቅት ምን ዐይነት ዝማሬ ነው የሚዘመረው? ሰቆቃወ ኤርምያስን ማንበብ ነዋ! መዝሙረ ዳዊትም ለዚህ የሚሆኑ ምዕራፎች አሉት። ለእስራኤላውያኑ የሙሾ ወቅት ነበርና የሐዘንና የዋይታ ሙሾ ነበር የሚያስፈልጋቸው። ከዚህ በፊት፣ በሰቆቃወ ኤርምያስ ላይ አንድ መልእክት ሳቀርብ አቅርቤው የነበረውን ጥያቄ ደግሜ አቀርባለሁ። አገር በጣር ውስጥ፣ በታላቅ ሐዘን ውስጥ ስታልፍ የምንዘምረው መዝሙር አለን? ሙሾ አለን? ጌታችን በመስቀል ላይ ሆኖ መዝሙር 22ን ይጠቅስ ነበር። ነቢዩ ኤርምያስ ሰቆቃወ ኤርምያስን ነበር ያዜመው፤ ይህም ሙሾ ነው።

እኛስ? እንደ ቤተሰብ፣ እንደ ቤተ ክርስቲያን፣ እንደ አገር ለሐዘን ጊዜ የሚሆን ምን ያህል ሙሾ አለን? ወይስ ሁሌም መዝሙራችን “አፌን ሣቅ ሞልቶታል” ነው?

https://t.me/PaulosFekadu
460 viewsedited  14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-20 22:51:49 የእግዚአብሔር ልጅ - ክፍል ፬
508 viewsedited  19:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-14 18:58:51 የኢዮብ መከራ ሰበብ ምንድን ነው? ራሱ ኢዮብ? የአደጋ ጣዮቹ የሳባ ሰዎችና የከለዳውያን ክፋት? የተፈጥሮ ክፋት (የዐውሎ ነፋስና የመብረቅ አደጋ አግኝተውታልና) የወረረሽኝና የበሽታ ክፋት? ሰይጣን? እግዚአብሔር? ወይስ ሁሉም መልስ ነው? ሁሉም መልስ ከሆኑ፣ ዋናው ምክንያት ምንድን ነው ታዲያ? ወይስ ሁሉም ዋና ምክንያቶች ናቸው?
640 viewsedited  15:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-13 18:50:07 የእግዚአብሔር ልጅ - ክፍል ፫
408 viewsedited  15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-12 18:15:35 https://hintset.org/forum/book-club/book-award/?fbclid=IwAR2AMo55QakCp0SfUqkfJ9pzIr_bpSxy-JeeTjZ6la5FnFQL96Fs-6DWkn4
568 views15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-11 18:20:06 ሳዖል መሓላውን ለማክበር ልጁ ዮናታን እንዲገደል ፈለገ፤ ሕዝቡ ግን በሳዖል ውሳኔ ስላልተስማማ ዮናታን ተረፈ። ዳዊት ልጁ አቤሴሎም እንዳይገደል የጦር አለቆቹን አዘዛቸው፤ ከጦር አለቆች አንዱ በዚህ ስላልተስማማ አቤሴሎም ተገደለ። ገዥዎች እየወደዱም የማይፈጸምላቸው ነገር አለ!

(እናንተ ጨምሩበት)

https://t.me/PaulosFekadu
396 viewsedited  15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-09 15:14:15 ሄሮድስ መጥምቁ ዮሐንስ እንዲገደል አልፈለገም ነበር፤ ሊያድነው ቢፍጨረጨርም ሲያቅተው አስገደለው። ጲላጦስም ጌታ ኢየሱስ እንዲገደል አልፈለገም ነበር፤ ሊያድነው ቢሟሟትም አቅቶት አስገደለው። ገዥዎችም ሳይወዱ የሚያስፈጽሙት ነገር አለ!

(እናንተ ጨምሩበት)
410 viewsedited  12:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-07 14:54:38 ብርሃን ጨለማ ነው፤ ጨለማም ብርሃን ነው!

እግዚአብሔር በጨለማው ውስጥ እኖራለሁ ማለቱን ሰለሞን ይነግረናል (1ነገ. 8፥12)፤ ሌሎች ክፍሎችም ይህን ሐሳብ ይደግፉታል (መዝ. 18፥10-11፤ ዘዳ. 4፥11-12፤ 5፥22)። ሐዋርያው ጳውሎስ ግን እግዚአብሔር የሚኖረው በብርሃን ውስጥ መሆኑን ጽፏል (1ጢሞ. 6፥16)። ታዲያ እግዚአብሔር በብርሃን ነው የሚኖረው? ወይስ በጨለማ? (ጨለማም ሆነ ብርሃን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዘይቤነት የቀረቡ ናቸው።)

ሰው የሚያየው በብርሃን ነው። ዐይን ብርሃን ነው ቢባልም፣ ዐይን ራሱ ለማየት ብርሃን ያስፈልገዋል። ያለ ብርሃን አናይም። ስለዚህ የብርሃኑ መጠን ሲቀንስ እይታችንም እየቀነሰ ይመጣልና ዙሪያ ገባው ሲጨልም ምንም አይታየንም። ስለዚህ በጨለማ ውስጥ የሚኖር አይታይም። እናም ከቶውንም እግዚአብሔርን ያየው ማንም የለም! ስለዚህ እግዚአብሔር በጨለማ ውስጥ ይኖራል ማለት አናየውም ወይም አናውቀውም ማለት ነው።

ሰው የሚያየው በብርሃን ነው። ብርሃኑ ሲቀንስ እይታችን እየቀነሰና እየወረደ በመጨረሻ ምንም ወደማናይበት ሁኔታ እንደርሳለን። የብርሃኑ መጠን እጅግ እየጨመረ ሲመጣም ውጤቱ ከዚሁ አይርቅም። የብርሃኑ መጠን ከልክ ባለፈ ቁጥር ማየት አንችልም። እንዲያውም አደገኛነቱ ይጨምራል፤ ወደ ፀሓይ እንዳናይ የምንመከረው ለዚህ ነው። ብርሃን ሲበዛ ያሳውራልና! አንድ ነገር ብርሃን በበዛበት ቁጥር እውነተኛ ቅርጹና ቀለሙ ይሰወረናል፤ በብርሃኑ አይናችን ይጥበረበራልና አናየውም። ስለማናየውም አናውቀውም። “ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ውስጥ ይኖራል፤ አንድ ሰው እንኳ አላየውም፤ ሊያይም አይቻለውም” (1ጢሞ. 6፥16)።

እግዚአብሔር በብርሃን ይኖራል። ብርሃኑ ማንም ሊቀርበው የማይቻል ነውና ማንም አያየውም። ስለዚህ እግዚአብሔር ያለው በጨለማ ነው።

ጨለማው ከእይታ የሚከልለው ግን እኛን ብቻ ነው፤ እግዚአብሔርን አይደለም። መዝሙረኛው እንደሚል፣ “በውኑ ጨለማ ትሸፍነኛለች ብል፥ ሌሊት በዙሪያዬ ብርሃን ትሆናለች። ጨለማ በአንተ ዘንድ አይጨልምምና ሌሊትም እንደ ቀን ታበራለችና” (መዝ. 139፥11-12)።

ስለዚህ እግዚአብሔር ሊያየን ሲፈልግ ጨለማው ብርሃን ነው።

እኛ እግዚአብሔርን ማየት ስንፈልግ ግን ብርሃኑ ጨለማ ነው።

https://t.me/PaulosFekadu
613 viewsedited  11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-04 13:15:11 ዕለተ ስቅለት በእምነት ዓለም ውስጥ ከሁሉ የከፋው ጨለማ ነበር። ነገር ግን እምነት የተወለደው በዚያ ጨለማ ውስጥ ነው። በኋላ በምልሰት መረዳት እንደሚቻለው በእግዚአብሔር ተትቶ የመገኘት፣ የመሠቃየትና የጽልመትለ ድባብ የሞላበት ያ ጊዜ እግዚአብሔር ያልነበረበት አልነበረም፤ እንዲያውም እግዚአብሔር በዚያ ከመገኘትም ዐልፎ ሁኔታዎችን ይከውን የነበረው እርሱ ራሱ ነበር።
389 viewsedited  10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 11:54:02 “ሰላምን ከሚጠሉ ሕዝቦች ጋር እጅግ ለረጅም ጊዜ ኖርሁ። እኔ ሰላምን እደግፋለሁ፤ ስለ ሰላም በምናገርበት ጊዜ እነርሱ ስለ ጦርነት ያወራሉ።” (መዝ. 120፥6-7፤ አዲስ ትርጉም)

“ሰላምን በሚጠሉ መካከል ለረዥም ጊዜ ኖሬያለሁ። እኔ የሰላም ሰው ነኝ፤ እኔ ስለ ሰላም ስናገር፣ እነርሱ ጦርነት ደጋፊ ሆነው ይገኛሉ።” (መዝ. 120፥6-7፤ ሕያው ቃል)

(አገሬን ባሰብሁ ጊዜ)
529 viewsedited  08:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ